Get Mystery Box with random crypto!

ATC NEWS

የሰርጥ አድራሻ: @atc_news
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 116.41K
የሰርጥ መግለጫ

#ADDIS_ABABA : ETHIOPIA
ለመልዕክት 👇🏻
@mujaabot
For Advertisement👇🏿
@atcads

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2024-04-01 13:15:02
ለልዩ ፍላጎት ትምህርት የሚረዱ 14 የድጋፍ መስጫ ማዕከላት ወደ ሥራ ገብተዋል
**********

የልዩ ፍላጎት ትምህርትን ለማጠናከር የሚረዱ 14 የድጋፍ መስጫ ማዕከላት በመገንባት ወደ አገልግሎት ማስገባቱን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የልዩ ፍላጎት አካቶ ትምህርት እና መደበኛ ትምህርት ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል አስራት ለኢፕድ እንደገለጹት፤ የልዩ ፍላጎት ትምህርት በመዲናዋ ተደራሽ እንዲሆን ቢሮው የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

ቀደም ብሎ በከተማዋ 72 የድጋፍ መስጫ ማዕከላት የነበሩ ሲሆን፤ አሁን ላይ አስራ አራት ማዕከላት ተገንብተው ወደ አገልግሎት እንዲገቡ መደረጋቸውን ጠቁመዋል።

(ኢ.ፕ.ድ)
ሙሉውን ለማንበብ
https://press.et/?p=124724

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
16.4K viewsMuJa. M, 10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-01 13:13:46 Safari English Academyዎች ነን በonline ለሁለት ወር ያክል እንግሊዘኛ የመናገር ችሎታችሁን ለማሳደግ ሁለተኛ ዙር ምዝገባ ጀምረናል።

መሉ በሙሉ online በመሆኑ በቤታችሁ ሆናችሁ መማር ትችላላችሁ

ጥቂት ተማሪዎችን ብቻ ስለምንፈልግ ምዝገባው የምቆየው ለ4 ቀን ስሆን በመጀመሪያዎቹ 2 ቀናት ለሚመዘገቡ የ50% ቅናሽ አለው።

ለመመዝገብ @Private_Airport

Telegram Channel: safarienglish

https://t.me/+RBn3SqI-LTkwODdk
16.8K viewsMuJa. M, 10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-31 22:28:42 በተማሪ ምገባ ትምህርታቸውን አቋርጠው የነበሩ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታ መመለስ መቻሉን የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር አስታወቀ።

በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ከ15 ሺህ በላይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ተገድደዋል።

ይሁን እንጂ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ድርቅ ለተከሰተባቸው አካባቢዎች አልሚ ምግቦች በመላክ ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ ማድረጉን የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ትምህርት መምሪያ ገልጿል።

ተማሪ ልእልት ብርሃኑ በአበርገሌ ወረዳ ማዓርነት ትምህርት ቤት ተማሪ ናት። በወረዳው በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ፍየሎችን ለመጠበቅ ከትምህርት ገበታ ርቃ እንደነበረ ገልጻለች። የተማሪ ምገባ በመጀመሩ ወደ ትምህርቷ እንድትመለስ እንዳገዛት ተናግራለች።

ተማሪ ናትናኤል ሹመት በርካታ ተማሪዎች የዕለት ምግብ በማጣታቸው ምግብ ለመፈለግ ከትምህርት ገበታ ርቀው ነበር ብሏል።

አንድ ክፍል ላይ ከ20 ያልበለጡ ተማሪዎች ይገኙ እንደነበርም ነው ያስረዳው። አሁን ግን በአንድ ክፍል ከ50 በላይ ተማሪዎች ይማራሉ ብሏል። መንግሥት የጀመረውን ድጋፍ እስከ ሰኔ እንዲቀጥል እንደሚፈልጉም አስረድቷል።

የአበርገሌ ወረዳ ኒየረ አቑ ከተማ ነዋሪ እና የትምህርት ቤቱ የወመህ አባል አቶ ወርቁ አየነው "ከችግሮች ሁሉ ክፉው ልጅህን የምታበላው ማጣት ነው፤ አሁን ግን ተመሥገን ልጆቻችን ወደ ትምህርት ገበታቸው በመመለሳቸው ደስተኞች ነን” ብለዋል።

የመዓርነት አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምክትል ርእሰ መምህር ሲሳይ ታደሰ በትምህርት ቤቱ ከሁለተኛው ወሰነ ትምህርት ጀምሮ ምገባ እንደተጀመረ ገልጸዋል።

የተመዘገቡ ሁሉም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ ተመልሰዋል ያሉት ምክትል ርእሰ መምህሩ በምገባ ሥራው ለሦስት ሥራ አጥ ወጣቶችም የሥራ እድል መፍጠር ተችሏል ብለዋል። የተማሪዎች የመማር ፍላጎትም በእጥፍ ጨምሯል ነው ያሉት።

የአበርገሌ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ገብረሃና ኪሮስ በበኩላቸው በወረዳው በ12 ትምህርት ቤት ምገባው የተጀመረ ሲኾን ከ6ሺህ በላይ ተማሪዎች የምገባው ተጠቃሚ ስለመኾናቸው አብራርተዋል።

በሁለተኛው ወሰነ ትምህርት ያቋረጡ ከአንድ ሺህ 150 በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ ተመልሰዋል ነው ያሉት፡፡

የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ፍታለሽ ምህረቴ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ባደረገው ድጋፍ በዞኑ 64 ትምህርት ቤቶች የምገባ ተጠቃሚ እንደኾኑ ገልጸዋል።

በዚህም ከ30 ሺህ በላይ ተማሪዎች የምገባው ተጠቃሚ እንደኾኑ የገለጹት ምክትል ኀላፊዋ ምገባው እስከ ትምህርት ዓመቱ መገባደጃ ድረስ የሚቀጥል ነው ብለዋል።

የተማሪ ምገባ በብሔረሰብ አሥተዳደሩ መከፈቱ ሁለንተናዊ ፋይዳው የጎላ እንደኾነም ነው ያስገነዘቡት፡፡ መምሪያ ኀላፊዋ በምገባ ሥራው ከ200 በላይ ሥራ አጥ ወጣቶች ጊዜያዊ የሥራ እድል እንደተፈጠረላቸው ነው ያስገነዘቡት፡፡ ተማሪዎችም ትምህርታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

[ዘገባው የአሚኮ ነው]
ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
19.2K viewsMuJa. M, 19:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-31 22:28:23
በተማሪ ምገባ ትምህርታቸውን አቋርጠው የነበሩ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታ መመለስ መቻሉን የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር አስታወቀ።
17.9K viewsMuJa. M, 19:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-31 13:25:02 ከሥራ አጥነት ወደ ቀጣሪነት የተሸጋገሩ የቸሃ ወጣት አርሶአደሮች

ከተንጣለለው የቃሪያ ማሳ ደርሰናል። በስተቀኝ ደግሞ ሽንኩርት፣ ኪያር፣ ጥቅል ጎመን፣ ዝኩኒና ሌሎችም የጓሮ አትክልቶች በስፋት ተተክለው ይታያሉ። በቅርብ ርቀት ደግሞ በርከት ያሉ ሴቶችና ወጣቶች የቀሩ ምርቶችን በመሰብሰብ ሥራ ተጠምደዋል። ይህ ከ30 ሄክታር በላይ የሚልቀው ማሳ ታዲያ ከዓመታት በፊት ከባህር ዛፍ ውጪ ምንም አገልግሎት የማይሰጥ ሜዳ እንደነበር ከአካባቢው አርሶ አደሮች ነግረውናል።

ወጣት ዳንኤል ሽፈታ እዚሁ ቸሃ ወረዳ ወድሮ ቀበሌ ላይ ነው ተወልዶ ያደገው። ከሰመራ ዩኒቨርሲቲ በሆርቲካቸር ትምህርት ዘርፍ ተመርቆ በእርሻ ሥራ ለመሰማራት ከአራት ጓደኞቹ ጋር ይመክራል፤ የራሳቸውን ሥራ ለመጀመር የሚያግዛቸውን 70 ሺ ብር ከቆጠቡ በኋላ ከቸሃ ወረዳ 28 ሺ ብር ብድር፣ ምርጥ ዘርና እንደ የውሃ ፓምፕ የመሳሰሉ ግብዓቶችን በማግኘት በአንደኛው ጓደኛቸው አባት ጓሮም ሽንኩርትና ሌሎች አትክልቶችን ማልማት ይጀምራሉ።

ከአንድ ሄክታር በማይልቀው መሬት ላይ አልምተው 70 ሺ ብር ሲያገኙ ልባቸው የበለጠ ለማልማት ተነሳሳ፤ እናም ከአንድ ሄክታር ወደ ሁለት፤ ከሁለት ወደ ሦስት ሄክታር መሬት አሰፉ። የምርት አይነታቸውንም ከዚህ ቀደም በአካባቢው ኅብረተሰብ ብዙም ያልተለመዱ ግን ደግሞ በከተሞችና በውጭ ገበያ ተፈላጊ የሆኑ እንደ አበባ ጎመን፣ ብሮኮሊና ኪያር ያሉ የጓሮ አትክልቶችን እንዲያለሙ ወረዳው ሰባት ሄክታር መሬት አመቻቸላቸው። እነዚህ ብርቱ ወጣቶች ታዲያ ሳይታክቱ ማልማታቸውን ቀጠሉና እድገታቸውን ጨመሩ። ይህን ያየው የወረዳው አስተዳደርም የብድር አቅርቦቱን ወደ 300 ሺ ብር ከፍ አደረገላቸውና አቅማቸውን አጎለበቱ።

‹‹በአሁኑ ጊዜ የእርሻ መሬታችን 30 ሄክታር ሲሆን በዚህም ጎመን፣ ቲማቲም፣ ሽንኩርት፣ ብሮኮሊ፣ አበባ ጎመን፣ ሃብሃብና ሌሎችም ተፈላጊ ምርቶችን በስፋት በማልማት ለገበያ እናቀርባለን›› የሚለው ወጣት ዳንኤል፤ በተለይም በወረዳው አማካኝነት በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር በመጠቀም ያለ ብዙ ድካምና እንግልት ምርታቸውን ወደ ተጠቃሚው እንደሚያደርሱ ይገልጻል። በአሁኑ ወቅት ካፒታላቸውን ወደ አስር ሚሊዮን ብር ማድረሳቸውን አመልክቶ፤ ከ100 በላይ ለሚልቁ የአካባቢው ወጣቶች በቋሚነት የሥራ እድል መፍጠራቸውን ያመለክታል።

በተጨማሪም በየቀኑ ከ100 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በእርሻው ላይ በጊዜያዊነት ተቀጥረው የሚሰሩበት ሁኔታ የተመቻቸላቸው መሆኑንም ይጠቅሳል።
ወጣት ዳንኤል እንደሚገልጸው፤ ምርቶቻቸውን አጎራባች ወረዳዎችና የክልሉ ዞኖች በስፋት ከማቅረብ በዘለለ፤ በኢትዮጵያም ሆነ በውጭ ገበያ ተወዳዳሪ ሆነው ለመቅረብ ተግተው እየሠሩ ነው። በአሁኑ ወቅትም ጥሩና ምርታማ ዘሮችን በማባዛት ለአዳዲስ ማህበራትና አርሶአደሮች ያሰራጫሉ፤ ይህንንም ዘር የማባዛት ሥራቸውን በማጠናከር ክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጎለብት የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ ነው ያሉት።

በተጓዳኝም የእርሻ ተረፈ ምርታቸውን በማቀነባበርና መኖ በማዘጋጀት ከብቶችን የማደለብና የወተት ልማት ሥራ ለመሥራት ማቀዳቸውን ወጣቱ አርሶአደር ይናገራል። ውጥናቸው መሳካት ግን አሁን ያለው የብድር መጠን ሊሻሻል እንደሚገባ ሳይጠቁም አላለፈም። በሌላ በኩል ደግሞ ከተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመርቀው ቁጭ ያሉ ወጣቶች ከተስፋ መቁረጥ ውስጥ ወጥተው እንደእነሱ መንግሥት ያመቻቸውን ምቹ እድል እንዲጠቀሙ ነው የመከረው።
የጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አክሊሉ ካሳ እንደሚናገሩት፤ ዞኑ በዋናነትም በበጋ መስኖ ልማት ከ30 ሺ ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ ሰብሎችን እያመረተ ይገኛል።

ከዚህም ውስጥ ወደ 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታን ምርት መሰብሰብ ችሏል። ዞኑ በስሩ ባሉ የወረዳና ቀበሌ መዋቅሮች የሚገኙ አርሶአደሮችን የመደገፍ ሥራ እያከናወነ ነው። በተጨማሪም እንደእነ ዳንኤል ድህነትን ታሪክ የሚያደርጉ በርካታ ወጣቶችን በመፍጠር የአካባቢውን ብሎም እንደሀገርም በምግብ እህል ራስን የመቻል እንቅስቃሴ ከግብ እንዲደርስ እየተሠራ ነው።

አዲስ ዘመን

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
13.4K viewsMuJa. M, edited  10:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-31 13:24:01 Safari English Academyዎች ነን በonline ለሁለት ወር ያክል እንግሊዘኛ የመናገር ችሎታችሁን ለማሳደግ ሁለተኛ ዙር ምዝገባ ጀምረናል።

መሉ በሙሉ online በመሆኑ በቤታችሁ ሆናችሁ መማር ትችላላችሁ

ጥቂት ተማሪዎችን ብቻ ስለምንፈልግ ምዝገባው የምቆየው ለ4 ቀን ስሆን በመጀመሪያዎቹ 2 ቀናት ለሚመዘገቡ የ50% ቅናሽ አለው።

ለመመዝገብ @Private_Airport

Telegram Channel: safarienglish

https://t.me/+RBn3SqI-LTkwODdk
13.0K viewsMuJa. M, 10:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-31 09:51:56
ዶክተር ከአንድ ቤተሰብ

የአንድ ቤተሰብ አባላት ናቸው፣ የገበሬ ልጆች ናቸው የተወለዱት በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሃባቦ ጉዱሩ ወረዳ ነው። የአቶ ሚሬሳ ልጆች አምስት ወንዶች እና ሁለት ሴቶች ሜዲስን ነው የተማሩት። አምስቱ በስራ ላይ ሲገኙ ሁለቱ በትምህርት ላይ ናቸው።

ሰባቱ የሚሬሳ ዶክተር ልጆች ባሻና ሚሬሳ፣ ሲሜራ ሚሬሳ፣ ገመቹ ሚሬሳ፣ ሸጊቱ ሚሬሳ፣ ፉፋ ሚሬሳ፣ ገለታ ሚሬሳ፣ ካዮ ሚሬሳ ይባላሉ።

#fastmereja
ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
16.4K viewsMuJa. M, 06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-30 21:09:52
ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወሰዱትን ገንዘብ ወደ አቋማሪ ድርጅቶች ያዘዋወሩ ተመራቂ ተማሪዎች ገንዘቡን መመለስ ባለመቻላቸዉ አጣብቂኝ ውስጥ ገብተዋል ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወሰዱትን ገንዘብ ወደ አቋማሪ ድርጅቶች ያዘዋወሩ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች በተሰጣቸው ማስጠንቀቂያ መሠረት መመለስ ባለመቻላቸው አጣብቂኝ ውስጥ ገብተዋል። ተማሪዎቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቴሌ ብር አማካኝነት በአቋማሪ…
20.4K viewsMuJa. M, edited  18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-30 19:08:50
ለፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ የህይወት ዘመን አገልግሎት ዕውቅና ተሰጠ
*
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ እና ኮምፒዩቴሽናል ሳይንስ ኮሌጅ ለረጅም አመታት በማስተማር፣ በምርምር እና በመሪነት ያገለገሉትን የፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላን የሕይወት ዘመን አገልግሎት ለማክበር መርሐ ግብር ያካሄደ ሲሆን በመርሐ ግብሩ ላይ ፕሮፌሰር ሽብሩ የሥነ-ሕይወት ትምህርት ክፍል መጠናከር ያረጉትን ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዲሁም በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ምሥረታ ላይ የተጫወቱት ጉልህ ሚናም ተጠቅሷል።

ከተማሩበት፣ ካስተማሩት፣ ብዙ የምርምር ሥራ እና ሕትመት ካደረጉበት የሳይንስ ዘርፍ ባሻገር ፕሮፌሰሩ በሚፅፏቸው የሥነ-ፅሁፍ ውጤቶችም ይታወቃሉ።

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
18.7K viewsMuJa. M, 16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-30 13:15:49
ከአንድ ወጣት ሆድ ዉስጥ ሚስማር፣ መርፌ፣ ሽቦና የጥርስ መፋቂያን ጨምሮ 15 ባዕድ ነገሮች በህክምና ወጣለት

የወሊሶ አጠቃላይ ሆስፒታል ከአንድ የ28 አመት ወጣት ሆድ ዉስጥ ሚስማር፣ መርፌ፣ ሽቦና የጥርስ መፋቂያን ጨምሮ 15 ባዕድ ነገሮችን በቀዶ ህክምና ማዉጣቱን ገለጸ።

የቀዶ ህክምናዉ ቡድን መሪ ዶ/ር ኤሊያስ ሰኝ እንደተናገሩት ከታካሚዉ የሆድ ክፍል 3 ሚስማሮች፣ 2 ቀጫጭን ሽቦዎች፣ አንድ መርፌ፣ 9 የእንጨት ጥርስ መፋቂያዎችና ሌሎች ባዕዳን ነገሮች አንድ ሰአት በፈጀ ቀዶ ህክምና ሊወጣ ችሏል።

ታካሚዉ በአዕምሮ ህመም ምክንያት የህክምና ክትትል ሲያደርግና መድሃኒት ሲጠቀም እንደነበረ የሆስፒታሉ ስፔሻሊስት ሃኪም ዶ/ር ኤሊያስ ሰኝ አብራርተዋል።

ነዋሪነቱን በደቡብ ምዕራብ ሸዋ አመያ ወረዳ ያደረገዉ ይህ ታካሚ በፊት በአዕምሮ ህመም ምክንያት ሲከታተል የነበረዉን ህክምናና መድሃኒት አቋርጧል።

ታካሚዉ ክትትሉን ከማቋረጡም በላይ አሁን በቀዶ ህክምና ከሆዱ የወጣዉ ባዕድ ነገር ይኖራል ብሎ ያሰበም ሆነ ተገቢዉን ምርመራ ያደረ አካል አለመኖሩን ነዉ የገለጹት።

እንደ ኦቢኤን ዘገባ፤ ዶ/ር ኤሊያስ ሰኝ እንደተናገሩት መሠል ክስተቶች ሊፈጠሩ ስለሚችሉ ማህበረሰቡ የአእምሮ ህመም ያለባቸዉን ግለሰቦች ከተለመደዉ ክትትል በዘለለ በጤና ተቋማትና በሰለጠነ ባለሙያ ድጋፍ ሊያደርጉላቸዉ እንደሚገባ መክረዋል።

ምንጭ - ኦቢኤን
ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
19.9K viewsMuJa. M, 10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ