Get Mystery Box with random crypto!

ከአንድ ወጣት ሆድ ዉስጥ ሚስማር፣ መርፌ፣ ሽቦና የጥርስ መፋቂያን ጨምሮ 15 ባዕድ ነገሮች በህክ | ATC NEWS

ከአንድ ወጣት ሆድ ዉስጥ ሚስማር፣ መርፌ፣ ሽቦና የጥርስ መፋቂያን ጨምሮ 15 ባዕድ ነገሮች በህክምና ወጣለት

የወሊሶ አጠቃላይ ሆስፒታል ከአንድ የ28 አመት ወጣት ሆድ ዉስጥ ሚስማር፣ መርፌ፣ ሽቦና የጥርስ መፋቂያን ጨምሮ 15 ባዕድ ነገሮችን በቀዶ ህክምና ማዉጣቱን ገለጸ።

የቀዶ ህክምናዉ ቡድን መሪ ዶ/ር ኤሊያስ ሰኝ እንደተናገሩት ከታካሚዉ የሆድ ክፍል 3 ሚስማሮች፣ 2 ቀጫጭን ሽቦዎች፣ አንድ መርፌ፣ 9 የእንጨት ጥርስ መፋቂያዎችና ሌሎች ባዕዳን ነገሮች አንድ ሰአት በፈጀ ቀዶ ህክምና ሊወጣ ችሏል።

ታካሚዉ በአዕምሮ ህመም ምክንያት የህክምና ክትትል ሲያደርግና መድሃኒት ሲጠቀም እንደነበረ የሆስፒታሉ ስፔሻሊስት ሃኪም ዶ/ር ኤሊያስ ሰኝ አብራርተዋል።

ነዋሪነቱን በደቡብ ምዕራብ ሸዋ አመያ ወረዳ ያደረገዉ ይህ ታካሚ በፊት በአዕምሮ ህመም ምክንያት ሲከታተል የነበረዉን ህክምናና መድሃኒት አቋርጧል።

ታካሚዉ ክትትሉን ከማቋረጡም በላይ አሁን በቀዶ ህክምና ከሆዱ የወጣዉ ባዕድ ነገር ይኖራል ብሎ ያሰበም ሆነ ተገቢዉን ምርመራ ያደረ አካል አለመኖሩን ነዉ የገለጹት።

እንደ ኦቢኤን ዘገባ፤ ዶ/ር ኤሊያስ ሰኝ እንደተናገሩት መሠል ክስተቶች ሊፈጠሩ ስለሚችሉ ማህበረሰቡ የአእምሮ ህመም ያለባቸዉን ግለሰቦች ከተለመደዉ ክትትል በዘለለ በጤና ተቋማትና በሰለጠነ ባለሙያ ድጋፍ ሊያደርጉላቸዉ እንደሚገባ መክረዋል።

ምንጭ - ኦቢኤን
ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news