Get Mystery Box with random crypto!

ATC NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ atc_news — ATC NEWS
ርዕሶች ከሰርጥ:
Dambidollouniversity
Dv
Scamalert
Fastmereja
የሰርጥ አድራሻ: @atc_news
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 116.34K
የሰርጥ መግለጫ

#ADDIS_ABABA : ETHIOPIA
ለመልዕክት 👇🏻
@mujaabot
For Advertisement👇🏿
@atcads

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2024-04-04 13:10:15
  100%  የተረጋገጠ ልዩ እድል! 

Full ስኮላርሽፕ እና ቪዛ የተረጋገጠ በቻይና የባችለር ማስተርስና ፒኤችዲ ትምህርት መከታተል ለሚፈልጉ ደንበኞቻችን በሙሉ  ያለምንም ቅድመ ክፍያ ከሙሉ የማማከር አገልገሎት ጋር ከግሬስ ኤዱኬሽናል እና ቪዛ ኮንሰልታንሲ ብቻ ያገኛሉ።

12ኛ ክፍል ውጤት ያልመጣላቸው ተማሪዎች አድሉን መጠቀም ይችላሉ።  

አዲስ አበባ: ደንበል ቢትወደድ ባህሩ ህንፃ 8ተኛ ፎቅ

  0934146000/0933099990

➘ ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ
  https://t.me/graceconsultancy

➙ https://www.tiktok.com/@grace_consultancy?_t=8lCQX0wm8pi&_r=1
15.6K viewsMuJa. M, 10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-03 21:29:15
የአሜሪካ ኤምባሲ የትምህርት ስኮላር ሺፕ አውጥቷል።

#ይሞክሩ_ሼር_ያድርጉ

Application for the U.S. Embassy’s EducationUSA Scholars Program (ESP) 2024 is now open!

ESP is a four-week training program that helps academically strong high school students apply to U.S. colleges and universities, with the goal of producing skilled and well-educated leaders to build tomorrow’s Ethiopia.

Eligibility Requirements

Visit this link for more about ESP and to submit your application:
https://sites.google.com/amspaceseth.net/educationusa-esp2024

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
21.6K viewsMuJa. M, edited  18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-03 19:14:49 ዩኒቨርሲቲዎች ለተለያዩ ግለሰቦች የሚሰጡት የክብር ዶክትሬት በሜዳይ፣ ኒሻንና ሽልማት ረቂቅ አዋጅ የማይካተት መሆኑን ፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከምክር ቤቱ ለዝርዝር እይታ ለቀረበለት የሜዳይ፣ ኒሻንና ሽልማት ረቂቅ አዋጅ ላይ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ከፍትህ ሚኒስትር ጋር ያዘጋጁት የሜዳይ፣ ኒሻንና ሽልማት ረቂቅ አዋጅ ትውልዱ ለሀገራቸው በጎ ስራ ካበረከቱና ምስጋና ከተሰጣቸው ግለሰቦች ልምድ እንዲቀስምና ለህዝብ ጠቃሚ ነገር ለመስራት ተነሳሽነት እንዲኖረው ያስችላል ተብሏል።

ቋሚ ኮሚቴው ከተቋማቱ ለመጡ ተወካዮች በረቂቅ አዋጁ ላይ ግልፅነት ይጎድላቸዋል ያላቸውን ጥያቄዎች በማንሳት ውይይት አድርጓል።

ከተነሱ ጥያቄዎች መካከል ዩኒቨርስቲዎች የሚሰጡት የክብር ዶክትሬት ከረቂቅ አዋጁ ጋር ግንኙነት አለው ወይ? የሚለው ይገኝበታል።

የፍትህ ሚኒስቴር የህግ ጥናትና ማርቀቅ ዳይሬክተር አዲስ ጌትነት፤ ዩኒቨርሲቲዎች ለተለያዩ ግለሰቦች የሚሰጡት የክብር ዶክትሬት በራሳቸው አሰራርና መስፈርት የሚተገበር መሆኑን አመልክተዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት የሚሰጡበት የራሳቸው ግብና አላማ ያላቸው መሆኑን በማንሳት በጉዳዩ ላይ የሚታየውን ወጣ ገባ አካሄድ የሚመለከታቸው ተቋማት ሊያስተካክሉት ይገባል ብለዋል።

በፌዴራልና በክልሎች የሜዳይ፣ ኒሻንና ሽልማት ድግግሞሽ እንዳይኖር ክልሎች በተለያዩ ዘርፎች ዕውቅና የሚሰጧቸው ግለሰቦች በሀገር አቀፍ ደረጃ ያላቸውን አበርክቶ ግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ የፌዴራል መንግስትም ሊሸልማቸው እንደሚችል በረቂቂ መመላከቱን የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የህግ አማካሪው አለምአንተ አግደው ተናግረዋል።

የውጭ ግንኙነትና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር) በረቂቅ አዋጁ ላይ ከአስረጂዎች በቂ ግብዓት የተገኘ በመሆኑ ከሌሎች ቋሚ ኮሚቴዎች ጋር በመሆን ግብዓት ተጨምሮበት ለምክር ቤቱ ይቀርባል ብለዋል።

ለውይይቱ ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ተብለው በደብዳቤ ጥሪ ከተደረገላቸው ከ10 በላይ ተቋማት ውስጥ የተገኙት ሶስቱ ብቻ መሆናቸው እንደተጠቆመ ኢዜአ ዘግቧል።

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
18.4K viewsMuJa. M, edited  16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 19:10:30 በኢትዮጵያ ለተማሪዎች ዉጤት መቀነስ ምክንያቱ ‹‹ከፍተኛ የሙቀት መጠን ነዉ›› ሲል የዓለም ባንክ ገለጸ፡፡

የዓለም ባንክ አደረግኩት ባለዉ ጥናት በኢትዮጵያ ለተማሪዎች ዉጤት መቀነስ ምክንያቱ ከፍተኛ የሙቀት መጠን መጨመር ነዉ ብሏል፡፡

ከፈረንጆቹ 2003-2019 በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና የወሰዱ ወደ 2.5 ሚሊየን የሚጠጉ ተማሪዎችን ዳታ ሰብስቦ ያገኘዉ ዉጤት መሆኑን ነዉ ይፋ ያደረገዉ፡፡

በትምህርት ዓመቱ ለከፍተኛ ሙቀት የተዳረጉ በተለይ ደግሞ በፈተና ወቅት ከባድ ሙቀት የሚያገኛቸዉ ተማሪዎች ፤ቀዝቃዛ አየር ባለባቸዉ ስፍራዎች ከሚማሩ ተማሪዎች ጋር ሲወዳደር ዉጤታቸዉ በእጅጉ ቀንሶ ተገኝቷል ነዉ ያለዉ፡፡

እንደዚህ ዓይነት ተጽዕኖ በተለይ በሰብ-ሰሃራ አፍሪካ አገራት ላይ የበረታ ነዉ የተባለ ሲሆን፤ የአየር ንብረት ለዉጡን ለመቋቋም የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች በስፋት አለመኖራቸዉ ሁኔታዉን እንደሚያባብሰዉም ነዉ የተገለጸዉ፡፡

የጥናቱ መሰረታዊ ግኝት የሆነዉ በትምህርት ዘመኑ ከፍተኛ ሙቀት የሚስተናገድባቸዉ ቀናት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸዉ እንዲቀሩ የሚያደርግ መሆኑን ነዉ፡፡

ይህም በኮሌጅ መግቢያ ፈተናዎች ላይ ወደ 2.28 በመቶ ዝቅ ያለ ዉጤት እንዲመዘገብ እንደሚያደርግ ነዉ፡፡

በጥናቱ ይፋ እንደሆነዉ ግልጽ የሆነ ምክንያት ባይቀመጥለትም ወንዶች ከሴቶች በበለጠ በሙቀት መጨመሩ ምክንያት የፈተና ዉጤታቸዉ ዝቅ ያለ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

ከወንዶች ጋር ሲነጻጸሩም ሴቶች በተሻለ መልኩ በትምህርት ገበታቸዉ ላይ የሚገኙ እና ለትምህርታቸዉም ከፍተኛ ቦታ ያላቸዉ ሆነዉ ተገኝተዋል፡፡

አሁን ላይ በተለያዩ የአለማችን አገራት ለተማሪዎች ዉጤት መቀነስ የሙቀት መጨመር ምክንያት መሆኑን ማስረጃ አለን ሲሉ በዓለም ባንክ የሪሰርቸሮች ግሩፕ ዋና ተመራማሪ ፓትሪክ ቤህረር ተናግረዋል፡፡

ፓትሪክ ጨምረዉም ከፍተኛ ሙቀት ከተማሪዎቹ በተጨማሪ በመምህራን የስራ እንቅስቃሴ ላይም የራሱ ተጽዕኖ ይኖረዋል ነዉ ያሉት፡፡

ፖሊሲ አዉጪዎች ይህንን ጉዳይ በደንብ ትኩረት ሊሰጡት ይገባል ያሉት ተመራማሪዉ ፤በመማሪያ ክፍሎች ዉስጥ ያለዉን የሙቀት መጠን በማስተካከል ለተማሪዎች ምቹ የመማሪያ ስፍራን መፍጠር አለባቸዉ ብለዋል፡፡

የተሻለዉ አማራጭ እንደየአከባቢዉ የሚለያይ ቢሆንም ግን አንድ ነገር ግልጽ ነዉ ሲሉ የሚጨምሩት ተመራማሪዉ ፤ይህም ተማሪዎች ለከፍተኛ ሙቀት ያልተጋለጡ አከባቢዎች ላይ እጅግ በተሻለ ሁኔታ መማር እንደሚችሉ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በ2022 ዘ ጋርዲያን ይዞት በወጣዉ አንድ ጽሁፍ ከፍተኛ የሙቀት መጨመር በጥራት እንዳናስብ በማድረግ ፣ የማሰላሰል እና የማመዛዘን ችሎታችን ላይ ተጽዕኖ ስለሚኖረዉ ስህተት የመስራት ዕድላችንን ከፍ ያደርገዋል ሲል አስታዉቆ ነበር፡፡

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
14.8K viewsMuJa. M, edited  16:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 19:08:30
#GTSTv1_Round_6

"Geez tech Ethical Hacking course" በ6ተኛ ዙር ተመልሷል!!!

አሁኑኑ ተመዝገቡ!!!
እንዲሁም SHARE አድርጉት

ለ 100 ሰው ቦታ ነው ያለዉ
ትምህርት መጋቢት 30 ይጀመራል

ለበለጠ መረጃ + Registration

LINK: https://forms.gle/ebDiZ9ab8hr8gT1X7

For contact: @geeztechsupport
#geeztech #gtstv1 @geeztechgroup
13.2K viewsMuJa. M, 16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 16:08:21
በጭንቅላታቸው የተጣበቁ መንትዮች ተወለዱ

በአክሱም ዩንቨርስቲ ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት በሪፈራል የመጣች እናት በድምሩ 5 ኪሎ ግራም የሚመዝኑ ሁለት የተጣበቁ ሴት መንትዮች የወለደች ሲሆን እናት እና ህፃናቱ በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኛሉ ተብሏል።

እናትየው በአካባቢው ጤና ጣቢያ የእርግዝና ክትትል ብታደርግም የአልትራሳውንድ ምርመራ ያላደረገች በመሆኗ ምክንያት ክስተቱ ልጆችን በወለደችበት አጋጣሚ መታወቁ ተሰምቷል።

እንዲህ ዓይነቱ ክስተት በዓለም ዙሪያ ከ 189ሺ አንድ አዲስ የተወለዱ ላይ ህፃናት ይከሰታል የተባለ ሲሆን አብዛኛዎቹ ተጣብቀው የሚወለዱ መንትዮች በማህፀን ውስጥ የሚሞቱ ሲሆን በህይወት ከሚወለዱት መካከል ግማሽ ያህሉ ደግሞ ከ 24 ሰዓታት በላይ በህይወት አይቆዩም።

ከ24 ሰዓታት በላይ የመኖር እድል ያላቸው ተጣብቀው የተወለዱ መንትዮች ደግሞ 18 በመቶዎቹ ብቻ ናቸው።


ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
14.1K viewsMuJa. M, edited  13:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 13:07:32
2,000,000 ብር እድለኛ የዩኒቨርሲቲ መምህር

የደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት አበበ ፍሬው በዝሆን ሎተሪ የ2,000,000 ብር / ሁለት ሚሊዮን / ዕድለኛ ሆነዋል ፡፡ መምህር አበበ ፍሬው ከመማር ማስተማር ስራቸው ጎን ለጎን ሎተሪን የመቁረጥ ልምድ አላቸውና በቆረጡት የ2016 የዝሆን ሎተሪ የ 2 ሚሊዮን ብር ዕድለኛ በመሆን ቼካቸውን ከአስተዳደሩ ተረክበዋል ፡፡

በደረሳቸውም ገንዘብ ከማስተማር ስራቸው በተጨማሪ የከፈቱትን የእንጨትና የብየዳ ሥራ እንደሚያስፋፉበት ገልጿል።

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
15.4K viewsMuJa. M, 10:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 13:06:36 Safari English Academyዎች ነን በonline ለሁለት ወር ያክል እንግሊዘኛ የመናገር ችሎታችሁን ለማሳደግ ሁለተኛ ዙር ምዝገባ ጀምረናል።

መሉ በሙሉ online በመሆኑ በቤታችሁ ሆናችሁ መማር ትችላላችሁ

ጥቂት ተማሪዎችን ብቻ ስለምንፈልግ ምዝገባው የምቆየው ለ4 ቀን ስሆን በመጀመሪያዎቹ 2 ቀናት ለሚመዘገቡ የ50% ቅናሽ አለው።

ለመመዝገብ @Private_Airport

Telegram Channel: safarienglish

https://t.me/+RBn3SqI-LTkwODdk
14.4K viewsMuJa. M, 10:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 11:55:02 #ቴሌግራም # አራት_ቀን_ቀረው የቴሌግራም አዲሱን ኖትኮይን መቼም ያልሰማ የለም። ሁሉም tab tab እያደረገ መሆኑ ያያቹ ወይንም የሰማቹህ ይመስለኛል። የቢትኮይን ዋጋ እየጨመረ እየጨመረ መሄድ ያሳሰባቸው የምስራቁ ሰዎች የቴሌግራሙ መስራች ወንድማማቾች ፓቬል ዱሮቭ ከትልቁ የዲጂታል ሳንቲም አቀናባሪ TON COIN ጋር ከዚ በፊት የገባውን ስምምነት ከወራት በፊት NOTCOIN በማለት እየተንቀሳቀሰበት…
15.5K viewsMuJa. M, 08:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 11:04:01
ራያ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በከፍተኛ ትምህርት መረጃ አስተዳደር እና አሰባሰብ ስርዓት (HEIMS) ከፍተኛ ደረጃን ይዟል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ላለፉት ሶስት ዓመታት በክልሉ በነበረው ጦርነት ትልቅ የመረጃ እና መገናኛ ቴክኖሎጂ (ICT) መሰረተ ልማት ችግሮች ቢያጋጥሙትም ከጦርነቱ በኃላ ባደረገው እና እያደረገ ባለው ሁለንታዊ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በከፍተኛ ትምህርት መረጃ አስተዳደር እና አሰባሰብ ስርዓት (HEIMS) 4ኛደረጃን ይዟል፡፡

ይህ ትልቅ ስኬት በመመዝገቡ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት በተለይም በመረጃ እና መገናኛ ቴክኖሎጂ (ICT) ዘርፍ ዩኒቨርሲቲው የላቀ ደረጃ ለመድረስ ትልቅ አስተዋፅኦ አለው፡፡

የዩኒቨርሲቲው አመራሮች እና የከፍተኛ ትምህርት መረጃ አስተዳደር ስርዓት (HEIMS) ቡድን አባላት ባደረጉት ትጋት እና ቁርጠኛ ውሳኔ የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያለው የአካዳሚክ መረጃን ወደ ከፍተኛ ትምህርት መረጃ አስተዳደር ስርዓት (HEIMS) በተሳካ ሁኔታ በማስገባት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የመረጃ ጥራት አያያዝን ለማሳደግ፣ አስፈላጊ መረጃዎችን ለማስገባት፣ በመረጃ ላይ የተመሰረቱ ውሳኔ ለመስጠት እና ጠንካራ የዲጂታላይዜሽን ስርዓት ለመፍጠር ወሳኝ ስራ መሰራቱን ዩንቨርሲቲው ገልጿል።

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
15.3K viewsMuJa. M, 08:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ