Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Education Bureau

የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau A
የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau
የሰርጥ አድራሻ: @anrse
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.56K
የሰርጥ መግለጫ

Quality Education

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-04 20:36:49
5.1K views17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 20:36:39 የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ከነገ ጀምሮ እንደሚሰጥ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ሰኔ 27/2015 ዓ.ም (ትምህርት ቢሮ) በአማራ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎቸ ከነገ ጀምሮ በክልል ደረጃ የተዘጋጀውን ሞዴል ፈተና እምደሚወስዱ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ እየሩስ መንግስቱ ተናግረዋል፡፡ ሞዴል ፈተናው ከሰኔ 28 እስከ 30/2015 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን በብሔራዊ ፈተና የሚፈተኗቸውን የትምህርት አይነቶች እንደሚፈተኑ ታውቋል፡፡
ተማሪዎች ለፈተናው በቂ ዝግጅት እያደረጉ ሲሆን በክልል ደረጃ የተዘጋጀው ሞዴል ፈተና በቀጣይ ለሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ዝግጅት ያግዛቸዋል ተብሏል፡፡
የተማሪዎች የዝግጅት ስራ እስከ ፈተናው ጊዜ እንደሚቀጥል የተናገሩት ወ/ሮ እየሩስ ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት ለተማሪዎች ውጤታማነት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡
የትምህርት ዘመኑ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሐምሌ 19-30/2015 ዓ.ም በክልሉ በሚገኙ 10 ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡ በክልሉ በ574 አስፈታኝ ትምህርት ቤቶች ከ215ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀመጡ ተገልጿል፡፡
በዩኒቨርሲቲ የሚሰጠው ፈተና ውጤታማ ይሆን ዘንድ አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተሰራ መሆኑን የተናገሩት ም/ኃላፊዋ ከሐምሌ አጋማሽ ጀምሮ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደሚጓጓዙ አክለው ገልፀዋል፡፡
ባለፈው አመት የታዩትን አንዳንድ ችግሮች በዚህ አመት እንዳይደገሙ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየሰራነው ብለዋል፡፡
ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጡ የአካባቢያቸው አንባሳደር መሆናቸውን ተገንዝበው የአካባቢያቸውን ባህልና ወግ የሚያሳዩ ሊሆን ይገባል ፡፡የወላጆቻቸውንና የመምህራንን ውለታ የሚከፍሉበት እና ለሀገራቸው ኩራት የሚሆኑበት ጊዜ መሆኑን አስበው ወደ ዩኒቨርሲቲ ሊመጡ ይገባል ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
5.3K views17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 13:42:02 በየትኛውም የኢትዮጵያ ጫፍ የተማራችሁ ሁሉ የተማራችሁባቸው ትምህርት ቤቶች ዛሬ የናንተን ድጋፍ ይሻሉ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ
................................................................................

ሰኔ 25/2015 (የትምህርት ሚኒስቴር) በየትኛውም የኢትዮጵያ ጫፍ የተማራችሁ ሁሉ ትናንት የተማራችሁባቸው ትምህርት ቤቶች ዛሬ የናንተን ድጋፍ ይሻሉ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጥሪ አቀረቡ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሁሉም ዜጎችና ተቋማት ተሳትፎ የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሻሻል የተዘጋጀውን ሀገር አቀፍ “ትምህርት ለትውልድ” ንቅናቄን አስጀምረዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ንቅናቄውን ባስጀመሩበት ወቅት ባደረጉት ንግግር÷ በየትኛውም የኢትዮጵያ ጫፍ የተማራችሁ ሁሉ ትናንት የተማራችሁባቸው ትምህርት ቤቶች ዛሬ የናንተን ድጋፍ ይሻሉ ብለዋል፡፡

ያለትምህርት መስፋፋት በመጪው ዓለም ተወዳዳሪ መሆን ስለማንችል ስለትምህርት ዛሬ የሚጠበቅብንን ልንወጣ ይገባልም ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ድጋፋችንን በተግባር ለማሳየት ሁላችንም በሐሳብ፣ በገንዘብ፣ በጉልበት እንዲሁም ያለንን ሁሉ ለትምህርት ቤቶች ለማዋል የሚያስችለንን "ትምህርት ለትውልድ" ሀገራዊ ንቅናቄ አስጀምረናል ነው ያሉት።

የላቀች ኢትዮጵያን ለመገንባት፤ ቀድመን የላቁ ትምህርት ቤቶችን አብረን እንገንባ ሲሉም በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡

ንቅናቄው÷ የቀድሞ ተማሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ ባለሃብቶች እንዲሁም ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች በትውልድ ቦታቸው በተማሩበት ቦታ እና በሚሠሩበት አካባቢ የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሟላት አስተዋጽኦ የሚያደርጉበት መሆኑ ተገልጿል፡፡

የግልና የመንግስት ተቋማት እንዲሁም የልማት አጋሮች÷ በሚሰሩባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሟላት ዐሻራቸውን የሚሳርፉበት መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

ንቅናቄው በዋናነት ያስፈለገው÷ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ በርካታ ትምህርት ቤቶች ከደረጃ በታች በመሆናቸው ነው ተብሏል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ እንዳመላከ÷ በኢትዮጵያ ከሚገኙ አጠቃላይ ትምህርት ቤቶች 86 በመቶ የአንደኛና የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመማር ማስተማር ሥራ አስፈላጊ የሆኑ የመሠረተ ልማት እጥረቶች አሉባቸው፡፡

እንዲሁም ከ71 በመቶ በላይ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተመሳሳይ መሰረተ ልማት አልተሟሉላቸውም ነው የተባለው፡፡

በትምህርት ቤቶቹ ከሚስተዋሉ የመሰረተ ልማት ችግሮች መካከልም÷ የንጹህ መጠጥ ውኃ አገልግሎት፣ የመጸዳጃ ቤት፣ ኤሌክትሪክ እንዲሁም የትምህርት ግብዓት እጥረት በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር
2.1K views10:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 13:41:43
1.9K views10:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 13:23:27
1.8K views10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 13:23:27 አሁን ያለውን የትምህርት ስርዓት መቀየር ካልቻልን በቀጣዩ አለም ተወዳዳሪ ሀገርና ትውልድ መፍጠር አንችልም¬- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ

ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ማሻሻል ላይ ያተኮር ህዝባዊ ንቅናቄ ለማካሄድ ያለመ የማስጀመሪያ ሀገር አቀፍ መድረክ ዛሬ አካሂዷል፡፡
..................................................//.............................

ሰኔ 25/2015 ዓ.ም (የትምህርት ሚኒስቴር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሁሉም ዜጎችና ተቋማት ተሳትፎ የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሻሻል“ትምህርት ለትውልድ” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን ሀገር አቀፍ ህዝባዊ ንቅናቄን አስጀምረዋል፡፡

ዛሬ የተገናኘነው ትናንት ያሰተማረን ማህብረሰብ እዳ ስላለብን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒሰትሩ በየትኛውም የኢትዮጵያ ጫፍ የተማራችሁ ሁሉ የተማራችሁባቸው ትምህርት ቤቶች ዛሬ የናንተን ድጋፍ ይሻሉ ብልዋል፡፡

12ኛ ክፍል ሲደርሱ ተማሪዎችን ሰብስቦ መፈተን ብቻ ሳይሆን ከታች መሰረቱ ላይ መስራት ይጠበቃል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሁን ያለውን የትምህርት ቤት ሁኔታ ለመቀየር በገንዘብ፣ በጉልበት እንዲሁም በዕውቀት ተባብረን የላቀች ኢትዮጵያን ለመገንባት፤ ቀድመን የላቁ ትምህርት ቤቶችን አብረን እንገንባ!ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው በተለያየ ጊዜ ትምህርትን ተደራሽ ለማድረግ የተሄደው ርቀት ጥራትን ከማረጋገጥ አንጻር የራሱ አሉታዊ ተጽዕኖ ነበረው ብለዋል፡፡

ለተማሪዎች ትምህርት መቀበል ዋናው ነገር የትምህርት መሰረተ ልማት ቢሆንም አሁን ካሉት ትምህርት ቤቶች ውስጥ 86 ከመቶ የሚሆኑት ከደረጃ በታች ናቸው ብለዋል፡፡

በመሆኑም እነዚህን ትምህርት ቤቶች በመንግስት አቅም ብቻ መገንባት የማይቻል በመሆኑ ሁሉንም ገንዘቡ፣ እውቀቱ እና ጉልበቱ ያላቸውን ማሳተፍ በማስፈለጉ ይህ ንቅናቄ ማስጀመሪያ መድረክ ተዘጋጅቷል ብለዋል፡፡

ትምህርት ቤቶች ላይ ያለውን ችግር ለነገ ልንተወው የሚገባ ባለመሆኑ ፊት ለፊት ልንጋፈጠው ይገባል ያሉት የትምህርት ሚኒስትሩ ይህ የትውልድና የሀገር ጥሪ መሆኑን አውቃችሁ ልትደግፉ ይገባል በማለት ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ኢትዮጵያውን ከተባበርን የማናስተካክለው ነገር የለም በዚህም በሚመጡት አምስት ዓመታት የኢትዮጵያን ትምህርት ቤቶች ችግር ሙሉ በሙሉ እንፈታለንም ብለዋል፡፡

በትምህርት ቤቶቹ ከሚስተዋሉ የመሰረተ ልማት ችግሮች መካከልም የመማሪያ ክፍል ፣ የንጹህ መጠጥ ውኃ አገልግሎት፣ የመጸዳጃ ቤት፣ ኤሌክትሪክ እንዲሁም የትምህርት ግብዓት እጥረት በዋናነት ይጠቀሳሉም ተብሏል፡፡

ይህ የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ በቀጣይም በየደረጃው በሁሉም ክልሎች በተዋረድ እንደሚካሄድ በመደረኩ ተገልጿል፡፡

በመድረኩም የሁሉም ክልል ርዕሰ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ባለሀብቶች፣አጋር ድርጅቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
2.0K views10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-02 12:26:06
የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ26__27/2015 ባሉት ቀናት ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ስራው መጠናቀቁ ተገለፀ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ26_27/2015 ባሉት ቀናት መስጠት የሚያስችለውን ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል(ሰኔ 25/2015-ትምህርት ቢሮ) ። ለፈተናው አገልግሎት የሚውሉ  ቁሳቁሶች ወደ ትምህርት ቤቶች  የማጓጓዝ ስራው ያለምንም ችግር የተጠናቀቁ ሲሆን በአስፈታኝ ትምህርት ቤቶች ለፈተና አስፈፃሚዎች እና ተፈታኝ ተማሪዎች  ኦሬንቴሽን የመስጠት ስራው ከሰኔ 24/2015 ጀምሮ እየተከናወነ ይገኛል።
በአማራ ክልል 347,966 ተማሪዎች በ5752 ትምህርት ቤቶች ፈተናው የሚሰጥ ሲሆን ፈተናው ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ በሁሉም አካባቢዎች የትምህርት ማህበረሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር ተቀናጅተው  እየሰሩ ይገኛሉ።
መልካም ዕድል ለተፈታኝ ተማሪዎቻችን!!
4.2K views09:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-29 21:12:09
6.3K views18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-29 21:02:10
6.2K views18:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 21:18:50 የ2015 ለ 2016 ዝውውር መረጃ
መልካም እድል
4.6K viewsedited  18:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ