Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Education Bureau

የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau A
የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau
የሰርጥ አድራሻ: @anrse
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.56K
የሰርጥ መግለጫ

Quality Education

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-04-02 10:21:54
1.3K views07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-02 10:21:18 ለ8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች እየተደረገ ያለው ድጋፍ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል። የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ማተብ ታፈረ
============================
ክልላዊ የ8ኛ ክፍል ፈተና ለሚወስዱና ሀገር አቀፍ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ለሚፈተኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የተለየ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የጋራ መግባባት ተፈጥሮ እየተሰራ ነው።

በየዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች ለተፈታኝ ተማሪዎች እተደረጉ ያሉ ድጋፍና ክትትልን የተመለከተ ሪፖርት ቀርቦ ተገምግሟል።

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ማተብ ታፈረ ተፈታኞች በስነ ልቦና እንዲዘጋጁ በማድረግ፣ የቀሩ የትምህርት ይዘቶች በመሸፈን፣ ከዚህ በፊት የነበሩ ፈተናዎችን እየሰሩ እንዲለማመዱ በማድረግ ፣ ተማሪዎች እንዲያነቡ በማበረታታትና ከወላጆች ጋር በጋራ መስራት ላይ እየተሰሩ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

በተለያዩ የክፍል ደረጃዎች እየተካሄዱ የሚገኙ የጥያቄና መልስ ውድድሮች ተማሪዎችና ወላጆችን የሚያነሳሳ በመሆኑ መቀጠል እንደሚገባቸውም ኃላፊው ገልጸዋል።


ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
1.3K views07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 17:27:16
1.7K views14:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 17:26:30 የክልሉ ትምህርት ዘርፍ የቀጣይ 10 ዓመት የለውጥ ፍኖተ ካርታ መነሻ ሁኔታዎች ላይ ውይይት ተካሄደ።
===========================
መጋቢት 23/2015 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የክልሉን ትምህርት ችግሮች በመለየትና የመፍትሔ ሃሳብ በማመንጨት የለውጥ ፍኖተ ካርታ የሚያዘጋጅ ቡድን አቋቋሞ ለአንድ አመት ሲያስጠና ቆይቷል።
የጥናት ቡድኑም በጥናቱ በክልሉ ትምህርት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመለየት የችግሮች መፍቻ መንገዶችን ያመላከተበትን ሰነድ ለቢሮው አመራሮች ፣ የማኔጅመንት አባላት፣ የዞንና ከተማ አስተዳደር ትምህርት አመራሮች በተገኙበት በጎንደር ከተማ አቅርቧል።

የአማራ ክልል ምክር ቤት የሰው ሀብትና ቱሪዝም ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወይዘሮ አበራሽ ታደሰ በትምህርት ሴክተሩ ያሉ ችግሮች በጥናት መለየታቸውና አማራጭ የመፍትሔ ሃሳቦች መቅረባቸው የክልሉን ትምህርት ለመለወጥ ሁሉም ህብረተሰብ እንዲሳተፍ እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ማተብ ታፈረ ቢሮው በጥናት የተለዩ ችግሮችና የመፍትሔ ሀሳቦችን በምክር ቤት ካስጸደቀ በኋላ ሰነዱን ለሁሉም ህብረተሰብ ተደራሽ በማድረግ የመፍትሄ አካል ለማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል።


ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
1.8K views14:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 15:03:54
ወ/ሮ እየሩስ መንግስቴ የአማራ ብሄራዊ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሆነው ተሹመዋል፡፡
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ለወ/ሮ እየሩስ መንግስቴ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸው ይመኛል፡፡
181 views12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 13:50:08
759 views10:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 13:50:08 "የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ በሁሉም ትምህርት ቤቶች በበይነ መረብ ብቻ ይካሔዳል"የአብክመ ትምህርት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት እና ጽሕፈት ቤት ኅላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን
----------------------------//-----------------------
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ ከመጋቢት 20/2015 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 15/2015 ዓ.ም እንደሚካሄድ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል፡፡ በክልሉ ከ288 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የመልቀቂያ ፈተና ምዝገባ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ በትምሕርት ቤቶች በበይነ መረብ ብቻ ይካሄዳል ያሉት የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት እና ጽሕፈት ቤት ኅላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን፤ ምዝገባውን በተሳካ ሁኔታ ለማጠናቀቅ የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተደርገዋል ብለዋል፡፡

የአስፈታኝ ትምህርት ቤቶች ርእሳነ መምህራን እና የአይሲቲ ባለሙያዎች በቂ ሥልጠናዎችን እየወሰዱ እንደሆነም በተለይም ለአሚኮ ተናግረዋል፡፡

የተፈታኝ ተማሪዎች ትክክለኛ ቁጥር የሚታወቀው ከምዝገባ በኋላ ነው ያሉት የጽሕፈት ቤት ኅላፊው በመደበኛ የትምሕርት መርሐ ግብር ከ177 ሺህ በላይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን እየወሰዱ ነው ተብሏል፡፡ በማታው መርሐ ግብር 1 ሺህ 867 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እየወሰዱ እንደሆነም ተገልጿል፡፡

በትምህርት ዓመቱ በግል ትምህርት ቤቶች ከ48 ሺህ በላይ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ነው፡፡ በክልሉ 127 ዐይነ ስውራን ተማሪዎች አሉ ያሉት አቶ ጌታቸው ቢያዝን በአጠቃላይ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ288 ሺህ በላይ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል ነው ያሉት፡፡

የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ በትምሕርት ቤቶች ውስጥ በበይነ መረብ ብቻ እንደሚካሄድ የገለጹት አቶ ጌታቸው፤ ተማሪዎች በአካል በመገኘት ምዝገባቸውን ያደርጋሉ ብለዋል፡፡ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተናን በድጋሚ የሚወስዱ ተፈታኞች ምዝገባም በተመረጡ ትምህርት ቤቶች እንደሚካሄድ ነግረውናል፡፡ ድጋሜ ተፈታኞች ከዚህ ቀደም የተፈተኑበትን የትምህርት ማስረጃ በመያዝ በአካል መገኘት አለባቸው ብለዋል፡፡ በምዝገባ ወቅት ሁሉም ተማሪዎች ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ አለባቸው፡፡

በዘንድሮው ዓመት የፈተና ምዝገባ ያለፉት ዓመታት ችግሮች እንዳይደገሙ በቂ ጥንቃቄ ይደረጋል ያሉት አቶ ጌታቸው፤ የመብራት እና የኢንተርኔት ችግሮች እንዳይፈጠሩ ወረዳዎች ከትምሕርት ጽሕፈት ቤቶች ጋር በቅርበት ይሠራሉ ብለዋል፡፡ በምዝገባ ሂደቱ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆች እና የትምሕርት ባለድርሻ አካላት ትብብር እንደሚያስፈልግ አቶ ጌታቸው ገልጸዋል። ምዝገባውን ያላካሄደ ተማሪ ፈተናውን አይወስድም ነው ያሉት፡፡

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና በከፍተኛ ትምሕርት ተቋማት (ዩኒቨርሲቲዎች) ውስጥ የሚሰጥ ይሆናል። የፈተና ጊዜ በቀጣይ የሚገለጽ ነው ተብሏል፡፡
መረጃው የአሚኮ ነው
811 views10:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 10:00:26
1.5K views07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 09:59:48 የጎንደር ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ "የትምህርት ጀግኖችን እንፍጠር" በሚል መሪ ቃል በ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ከተማ አቀፍ የጥያቄና መልስ ውድድር አካሄደ።
============================================
የጎንደር ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳንዔል ውበት በውድድሩ መክፈቻ ባደረጉት ንግግር በትምህርት ስርዓታችን ያጋጠመን የትምህርት ጥራት ችግር ለመቅረፍ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገለፀው በሥነ-ምግባር የታነፀ፣ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን የማፍራት ግባችንን ለማሳካት መሰል ጥያቄና መልስ ውድድሮች አዎንታዊ ተፅእኖ እንደሚኖራችው ገልጸዋል፡፡ ቀና የፉክክር መንፈስ ያላቸው ውድድሮች በትምህርት ቤቶች በዘላቂነት ሊቀጥሉ እንደሚገባ ኃላፊው አሳስበዋል። በየጉድኝቱ አሸናፊ በመሆን ለውድድር የመጡ ተማሪዎች በ8ኛና በ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተናዎች ከሌሎች የክፍል አጋሮቻቸው ጋር በመሆን በርትተው በመስራት በውጤታማነት ትምህርት ቤታቸውንና አካባቢያቸውን ማስጠራት እንደሚገባቸው ገልጸዋል ።

በጥያቄና መልስ ውድድሩ 1ኛ ተማሪ ሰላም አርዓያ ከዋሊያ ትምህርት ቤት ፤ 2ኛ ተማሪ ቤዛዊት ደጀን ከደብረሰላም ትምህርት ቤት፤ 3ኛ ተማሪ ታምራት ፍቃዱ ከአርባባ ትምህርት ቤት አሸንፈዋል፡፡ የጥያቄና መልስ ውድድሮች በ1ኛ፣ በ6ኛ እና በ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል በቀጣይ እንደሚካሄድ የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት መመሪያ አሳውቋል።

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
1.6K views06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 17:11:43
2.1K views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ