Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Education Bureau

የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau A
የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau
የሰርጥ አድራሻ: @anrse
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.56K
የሰርጥ መግለጫ

Quality Education

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 26

2022-08-30 12:08:11 ህፃናትን ወደ ትምህርት ገበታ በመላክ ሀገራችንን ወደ ነበረችበት ክብር ልንመልሳት ይገባል ሲሉ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ገለፀ።
****
ነሐሴ 24/2014 ዓ.ም
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ማተብ ታፈረ የ2015 ዓ.ም የአማራ ክልል የአንድ ጀንበር የተማሪዎች ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ በምስራቅ ጐጃም ዞን ጐንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ላይ ተገኝተው የምዝገባ ኘሮግራሙን ባስጀመሩበት ወቅት እንደተናገሩት ትምህርት የአንድ ሀገር እድገት ቁልፍ መሳሪያ በመሆኑ ሁሉም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህፃናትን ወደ ትምህርት ቤት በመላክ የተሻለ እውቀት ገብይተው ቀጣይነት ያለው የሀገር ዕድገትን የሚያስመዘግቡና ወደ ነበርንበት ክብር ሊመልሱ የሚቻሉ ዜጐችን ልናፈራ ይገባል፤

የተማሪ ምዝገባ ብቻውን ግብ አይደለም እስከ መጨረሻው ይዞ መዝለቅና ለጥሩ ውጤት ማብቃት ነው እንጅ ያሉት ዶ/ር ማተብ አሁን በምንሰራው የትምህርት ስራ ትውልዶች ስለሚወስኑ ሁሉም ሀገሩን እወዳለሁ የሚል ዜጋ በተማሪዎች ምዝገባና ውጤት ላይ ሊረባረብ ይገባል፤ የሀገራችን ብሎም የአማራ ህዝብ ከፍታ የሚረጋገጠው በተማረ ቁልፍ የሰው ሀይል በመሆኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ የመጣውን የክልሉን የተማሪዎች ምዝገባ ቁጥር በመቀልበስ ለእድገታችንና ለህልውልናችን ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት በአለም አቀፍ ደረጃ ያልተማረ ሰው ቦታ የለውም ያሉት የምስራቅ ጐጃም ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መንበሩ ዘውዴ ተዳክሞና ተቀዛቅዞ የነበረውን የተማሪዎች ምዝገባ በማነቃቃት ሁሉም እድሜው ለትምህርት የደረሰን ህፃን ወደ ትምህርት ቤት በማምጣት ማስመዝገብ ግድ ይላል ብለዋል፡፡ የሰው ሀብት ልማት ላይ ቅድሚያ ካልሰራን እድገታችን ሊረጋገጥ አይችልም ያሉት አቶ መንበሩ ከተማሪ ምዝገባ ጀምሮ እስከ ውጤት ድረስ አመራሩ፣ መምህሩ፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ባለድርሻ አካላት ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡

የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጌታሁን ፈንቴ በበኩላቸው በዞኑ በ5 ቀናት ውስጥ ከነሐሴ 23 እስከ ነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም ከ560 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ የተሻለ የቅድመ ዝግጅትተሰርቷል፤ በዚህም በዞናችን ውስጥ ብዛት ያላቸው ወረዳዎች በአንድ ጀምበር ብቻ ሁሉንም ተማሪ መዝግበው አጠናቅቀዋል ብለዋል፡፡ በዞኑ በተማሪዎች ምዝገባና ውጤት ላይ ያጣነውን ውጤት ወደ ነበረበት ከፍታ እንመልሰዋለን፡፡ ያሉት መምሪያ ሐላፊው የተሻለና ለሀገር የሚጠቅም ዜጋ ለመፍጠር በሚደረገው እንቅስቃሴ ሁሉም ሀገር ወዳድ አካል የበኩልን አስተዋፆኦ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል፡፡

ተማሪዎችን በአንድ ጀምበር ማስመዝገብ የሚባክን ጊዜና ጉልበትን ከመቆጠቡ ባለፈ ተማሪን ለማብቃትና ትምህርት ቤትና ማህበረሰቡን በማቀራረብ ረገድከፍተኛ ጠቀሜታ አለው ያሉት የጐንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ሸጋዬ ደሴ አመሪሩንና ህብረተሰቡን በማሳተፍ በአንድ ጀበር ከ39 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በ83 ትምህርት ቤቶች እየመዘገብን ነው፤ ተማሪዎችን እስከ መጨረሻው ይዞ በመዘለቅና ጥሩ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡

በአማራ ክልል በነሀሴ 23 እስከ ዻጉሜ 4 ን 2014 ዓ.ም ከ6 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ መደበኛ ተማሪዎች እንደሚመዘገቡ ከትምህርት ቢሮው የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡
3.8K views09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 07:33:26
4.4K views04:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 07:33:03 የጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ የአንድ ጀንበር የተማሪ ምዝገባ ፕሮግራም በስኬት ተጠናቀቀ።
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2015 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ ከነሃሴ 23 እስከ ጳጉሜ 4/2014 ዓ.ም በወጣው ፕሮግራም መሰረት በክልሉ ሁሉም ትምህርት ቤቶች ምዝገባውን በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
በምስራቅ ጎጃም ዞን የጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ የተማሪ ምዝገባን ባንድ ጀንበር ለማጠናቀቅ የቅድመ ዝግጅት ስራውን አጠናቆ ነሐሴ 23/2014 የክልል፣የዞንና የወረዳ አመራሮችና የአካባቢው ማህበረሰብ በተሳተፉበት የአንድ ጀንበር ምዝገባውን በስኬት አጠናቋል፡፡
ምዝገባውን በቦታው ተገኝተው የተከታተሉት የምስራቅ ጎጃም ዞን ም/አስተዳዳሪ አቶ መንበሩ ዘውዴ የምስራቅ ጎጃም ዞን ትምህርትን ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት በጋራ በመስራት የዞኑን ትምህርት ወደ ነበረበት ለመመለስ በቁርጠኝነት ስራ ጀምረናል ብለዋል፡፡ የጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ የአንድ ጀንበር የተማሪ ምዝገባ ጥሩ ማሳያ ነው ያሉት ም/አስተዳዳሪው የተመዘገቡ ተማሪዎች ሳያቋርጡ ውጤታማ እንዲሆኑ ከሁሉም በላይ ትኩረት ሰጥተን እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ትምህርት ለሁሉም ልማታችን መሰረት በመሆኑ በትምህርት ስራችን ላይ ምንም አይነት ድርድር ሳናደርግ በዞን ደረጃ ነሃሴ 27/2014 ዓ.ም ምዝገባ በማጠናቀቅ ለቀጣይ መማር ማስተማር ሂደት የምንዘጋጅበት ጊዜ ይሆናል ብለዋል፡፡
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ማተብ ታፈረ (ዶክተር) በበኩላቸው በወረዳ ደረጃ የተካሄደውን የአንድ ቀን ምዝገባ በስኬት መጠናቀቁ የማይቻል የሚመስለው የተቻለበት ነው፡፡ ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካል ተናበውና ተግባብተው ሲሰሩ ተመልክቻለሁ ያሉት ቢሮ ኃላፊው በምዝገባው ለተሳተፉ አካላት ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ትምህርት መታጠፊያችን መሆኑን በመረዳት የክልላችን የትምህርት ሽፋን እየቀነሰ በመምጣቱ ችግር ከማውራት ወጥተን እንደ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ የአንድ ጀንበር የተማሪ ምዝገባ በውጤት በመፈፀም ለህዝባችን ተገቢ መልስ ልንሰጥ ይገባል ብለዋል፡፡
ልጆቻቸውን ሲያስመዘግቡ ለተገኙ ወላጆችም ጀግኖች ሲሉ አወድሰዋቸዋል፡፡ሀገሩን የሚወድ ወላጅ ልጁን ወደ ትምህርት ቤት ይላክ ያሉት ቢሮ ኃላፊው ልጁን ወደ ትምህርት ቤት የማይልክ ወላጅ ሀገሩን የማይወድ ነው ብለዋ፡፡
ለምዝገባው ውጤታማነት የመምህራን ሚና የጎላ ነው ያሉት ቢሮ ኃላፊው መምህራን በአልተመቸ ሁኔታ ውስጥ ሆናችሁ ለሀገራችሁ የምትከፍሉት መስዋትነት ውለታውን ሀገራችሁ ትከፍላችኋለች ሲሉ ተናግረዋል፡፡
4.5K views04:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 07:07:26 ለ2015 የትምህርት ዘመን የተማሪ ምዝገባ ከነሐሴ 23-ፃጉሜ 4/2014ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት ይካሄዳል።
ልጆችን ማስተማር የዜግነት ግዴታን መወጣት መሆኑን በመረዳት ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህፃናትን ወደ ትምህርት ቤት ልከው ዛሬውኑ ያስመዝግቡ!!
።።። የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ።።።።።
6.8K views04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 12:22:41
11.4K views09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 12:22:40 ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናትን ሙሉ በሙሉ ወደ ትምህርት ገበታ ለማምጣትና ባለፈው የትምህርት ዘመንም የደረሰውን የትምህርት ብክነትን ለማካካስ በ2015 ዓ.ም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር አሳሰበ፡፡

ኮምቦልቻ-ነሐሴ 18/2014 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን)
በደቡብ ወሎ ዞን በ2014 ዓ.ም በአጠቃላይ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ለመማር ከተመዘገቡት ከ389 ሽህ 355 ተማሪዎች ውስጥ 361 ሽህ960 ተማሪዎች ለፈተና ተቀምጠዋል። 27 ሽህ395 ተማሪዎች በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታቸውን አቋርጠዋል፡፡ ለፈተና ከተቀመጡት ውስጥ ደግሞ 26 ሽህ 252 የሚሆኑት ተማሪዎች የሚጠበቅባቸውን የማለፊያ ውጤት ባለማምጣታቸው ከክፍል ክፍል አልተዛወሩም፡፡

በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ደግሞ 102 ሽህ 321 ተማሪዎች ለመማር ተመዝግበው 16 ሽህ 992 የሚሆኑት ፈተና ላይ አልተቀመጡም፡፡ ለፈተና ከተቀመጡት ውስጥ ደግሞ 12 ሽህ 992 የሚሆኑት ከክፍል ክፍል አልተዛወሩም፡፡

በ1ኛ ደረጃም ሆነ በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ቁጥር ከዓመት ዓመት እየቀነሰ መምጣቱን የደቡብ ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ መረጃ ያመላክታል፡፡

ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 442 ሽህ 596 ተማሪዎችን በአጠቃላይ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መዝግቦ ለማስተማር ዕቅድ ተይዟል፡፡ ከነዚህም ውስጥ 92 ሽህ 90 የሚሆኑት ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ናቸው፡፡ 133 ሽህ 601 ተማሪዎችን ደግሞ በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መዝግቦ ለማስተማር የዞኑ ምህርት መምሪያ ዕቅድ ይዟል፡፡

በ2014 ዓ.ም የተከሰተውን የትምህርት ብክነት ወደነበረበት ለመመለስ እንዲያስችለውም የደቡብ ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ የዞኑን አጠቃላይ አመራሮች ጨምሮ ከሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የዕቅድ ትውውቅና የተማሪዎች ምዝገባ ንቅናቄ መድረክ በኮምቦልቻ ከተማ አካሂዷል፡፡

የደቡብ ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ደረጀ አማረ ከጦርነቱ በኋላ ተማሪዎች ከያሉበት በማሰባሰብ ወደ ትምህረት ገበታ እንዲመጡ በማድረግና የትምህርት ቁሳቁስና ግብዓት በሌለበት ሁኔታ የመማር ማስተማሩን ሥራ በአጭር ጊዜ በማስጀመር ዓመቱን ሙሉ ለማስተማር መምህራንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ያደረጉት ጥረት የሚመሰገን ተግባር ነው ብለዋል፡፡

ይሁንና በ2014 ዓ.ም ጦርነቱ ካሳደረው ተጽዕኖ ጋር በተያያዘና በሌሎችም ምክንያቶች መማር የሚገባቸው ተማሪዎች አለመመዝገባቸው እንዳለ ሆኖ አቋራጭ ተማሪዎች እንዲሁም የደጋሚ ተማሪዎች ምጣኔ ከሚጠበቀው በላይ በመሆኑ ቀላል የማይባል የትምህርት ብክነት ደርሷል ብለዋል፡፡

በ2015 ዓ.ም ከባለፈው የትምህርት ዘመን የነበረውን ችግር በመቅረፍ በትምህርት ዘርፉ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እየተከናወኑ ስለመሆኑ መምሪያ ኃላፊው አንስተዋል፡፡ ከነዚህም ዋናው በሕዝብ ንቅናቄ የሚፈፀመው የተማሪዎች ምዝገባ በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ዕቅዱን ተገንዝበው የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

በዚህም ከነሐሴ 26/2014 ዓ.ም ጀምሮ በተከታታይ ለአምስት ቀናት የተማሪዎችን ምዝገባ ለማጠናቀቅ የታቀደ በመሆኑ ለስኬታማነቱ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ሊያደርጉ እንደሚገባም ነው መምሪያ ኃላፊው ደረጀ አማረ ያስገነዘቡት፡፡

የመሃል ሳይንት ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ እንዳለ ተመስገን እና የደሴ ዙሪያ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ ጀማል ኢብራሂም ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሽፋንና በትምህርት ጥራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ከወዲሁ የቅድመ ዝግጅት ሥራውን በትኩረት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የደቡብ ወሎ ዞን ም/ አስተዳዳሪ ተስፋ ዳኛው በጦርነቱ በተለይም በትምህርት ተቋማት ላይ ከፍተኛ ውድመት የደረሰ ቢሆንም በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፣ የትምህርት ባለሙያዎችና መምህራን የደረሰውን የሥነ ልቦና ጫና ተቋቁመው ፈጥኖ ትምህርት እንዲጀመር በማድረግ የትምህርት ዘመኑን ማጠናቀቅ መቻል ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል፡፡

በ2014 ዓ.ም የደረሰውን የትምህርት ብክነት ለማካካስ ለ2015 ዓ.ም ለመማር ማስተማር ስኬታማነት በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ከተማሪዎች ምዝገባ ጀምሮ በአጠቃላይ በትምህርት ሥራ ውስጥ ግብዓት በማሟላትና በሌሎች ተግባራት የበኩላቸውን ኃላፊነት መወጣት ይገባቸዋል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

በ2014 ዓ.ም በአጠቃላይ ትምህርት መቅደላ፣ መሃል ሳይንትና ተንታ ወረዳዎች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃን በመያዝ እውቅና ተችሯቸዋል፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ጃማ፣ ቦረናና ደላንታ ወረዳዎች ዝቅተኛ ደረጃን ይዘዋል፡፡
10.3K views09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 13:32:53
9.0K views10:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 13:32:52 መጭውን 2015 የትምህርት ዘመን ስኬታማ ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ መሆነን የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ትምህረት መምሪያ ገለፀ።
***
ነሐሴ 18/2014 (ምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን):የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ የ2014 የትምህርት ዘመን እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2015 የትምህርት ዘመን እቅድ ትውውቅ የንቅናቄ መድረክ በማካሄድ ላይ ነው።

የደብረ ማርቆስ ትምህርት መምሪያ ኀላፊ አቶ አበባው ግዛቸው በ2014 የትምህርት ዘመን የነበሩ መልካም ተሞክሮዎችን የበለጠ ለማስፋትና የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል እንዲሁም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በተያዘው 2015 የትምህርት ዘመን ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ብለዋል።

የ2015 የትምህርት ዘመንን በስኬታማነት ለመፈፀም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የተናገሩት መምሪያ ኀላፊው በከተማ አስተዳደሩ በመጭው መስከረም ወር የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ 2 ሽህ 155 ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት ተማሪዎችን ለፈተና ዝግጁ የማድረግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል።

በንቅናቄ መድረኩ የተለያዩ የስራ ኀላፊዎችና ባለሙያዎች እንዳሁም የተለያየ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሣታፊ ሆነዋል።
7.5K views10:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 07:19:13
7.5K views04:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 07:19:04 ከትምህርት አመራርና ባለሙያዎች ጋር ውይይት ተካሄደ
************
የአብክመ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት በምዕራብ ጎንደር ዞን የሚገኙ ተማሪዎች የልደት የምስክር ወረቀት አሰጣጥ ዙሪያ በየደረጃው ከሚገኙ የትምህርት አመራርና ባለሙያዎች ጋር ነሃሴ 17/2014 ዓ.ም በጎንደር ከተማ ውይይት አካሄደ።

በመድረኩ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ፅንሰ ሃሳብና የህግ ማዕቀፎች በትምህርት ስልጠናና ስርጸት ዳይሬክቶሬት አማካኝነት፣ ከ5 ዓመት በታች የህጻናት ልደት ምዝገባ ማስፈፀሚያ ሰነድ በዕቅድና በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት በኩል ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የምዕራብ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ም/ኃላፊ አቶ ስዩም ታደሰ እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት ዞኑ በተለያዩ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ችግር ውስጥ የቆየ ቢሆንም አሁን አንፃራዊ ሰላም ያለ በመሆኑ ተግባሩን እንድሌሎች ተግባራት በቼክሊስታችን በማካተት እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸው የ2015 ዓ.ም ትምህርት ተመዝጋቢዎችንና ከ5 ዓመት በታች ያሉ ህፃናትንም አጋርና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ በፓይለትነት የተሰጠንን ተግባር በብቃት መፈፀም እንደሚገባ ያሳሰቡ ሲሆን ተሳታፊዎችም በዞናችን ባሉ ሁሉም ቀበሌዎች የምዝገባ ስራውን እናሳካለን የሚል ይሁንታ ሰጠዋል።

የአብክመ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት ም/ኃላፊ አቶ ሞላ ትዕዛዙ በበኩላቸው ዞኑ ካለበት ዝቅተኛ የምዝገባ አፈፃፃም በፍጥነት ወጦ ወደ ፊት ከተቀመጡት ተራ ለመመደብ ከዞን እስከ ቀበሌ ድረስ ያለ አመራርና ባለድርሻ አካል የተለየ ርብርብ በማድረግ በዞኑ የሚከሰቱ ኩነቶችን በወቅቱ በመመዝገብ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ይህን ለማድረግ ደግሞ የወኩም መዋቅር ከክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት ጋር በማስትሳሳር ከትምህርት፣ ከጤና፣ ሴቶች ህፃናትና ወጣትና ስፓርት ጋር በመቀናጀት መመዝገብ ይገባል፤ ይህ ሲሆን ከግምት ዕቅድ ወጠን በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔና ፍትህ ለመስጠት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል። በዞኑ በሚገኙ 7 ወረዳዎች ውስጥ 89 ቀበሌዎች ያሉ ሲሆን በዘመቻው በሁሉም ቀበሌዎች ከ27 ሺህ በላይ ኩነቶች ይመዝገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

#የአብክመ ወሣኝ ኩነት ምዝገባ አገልግሎት
7.5K views04:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ