Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Education Bureau

የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau A
የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau
የሰርጥ አድራሻ: @anrse
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.56K
የሰርጥ መግለጫ

Quality Education

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-06-11 18:52:57 ለክልላችን መምህራንና የትምህርት አመራሮች!! የ2015 ለ 2016 መርሱ ዝውውር ሲሰራ ቆይቶ ተጠናቋል። ሰለሆነም መሉ ስካን የተደረገውን መረጃ ሰኔ 5/2015 በቢሮው ቴሌግራም፣ ዌብሳይትና ፌስቡክ ገፅ ስለሚለቀቅ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን።
ለፍትሐዊ አሰራርና ግልፀኝነት ተግተን እንሰራለን።
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ!!
4.7K views15:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 18:20:46
4.4K views15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 18:20:33 በአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች የጥናትና ምርምር ሲምፖዚየም ተጠናቀቀ።
።።።።።።።።።።።።።።።።። ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በየዓመቱ የሚካሄደው የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች ጥናትና ምርምር ሲምፖዚየም ለተመራማሪዎች ሽልማት በመስጠት ተጠናቋል።
ከሰኔ2_4/2015 በደሴ ከተማ ከ10ሩም መምህራን ትምህርት ኮሌጆች በመጡ የጥናት አቅራቢዎች፣ የኮሌጅ ዲኖች፣ የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ምሁራን በተገኙበት 19 የምርምር ፁሁፎች ቀርበው የተለዩ ሲሆን ለጥናትና ምርምር አቅራቢዎችም በቢሮው  የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በጥናቱ የተሳተፉት መምህር አሰፋ ደምሴ እንደተናገሩት ትምህርት ቢሮ በየዓመቱ የጥናትና ምርምር ሲምፖዚየም ማዘጋጀቱ እኛንና የትምህርት ስራውን ለማነቃቃት ጥቅሙ የጎላ ነው ብለዋል። እኔ ጡረታ ለመውጣት የቀረኝ ጊዜ አጭር ቢሆንም ያቀረብኩት ጥናት ተመራጭ ሆኖ እንድሸለም በመሆኔ እጅግ ደስ ብሎኛል ብለዋል። በቀሪ ጊዜየ እንድበረታ ሀይል ይሆነኛል ነው ያሉት። የጥናትና ምርምሩን ስራ በዳኝነት ሲመሩ ከነበሩት የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ምሁራን መካከል ፕሮፌሰር ሰለሞን መለሰ እንደተናገሩት "መምህራን ተመራማሪዎች ናቸው" ። የትምህርት ችግሮችን በጥናትና ምርምር መፍታት ይገባል ያሉት ምሁሩ በተለይም ድርጊታዊ ጥናትና ምርምርን በመጠቀም የመማር ማስተማሩን ሂደት ማሻሻል እንደሚቻል አስረድተዋል። አጠቃላይ የሽልማት ሂደቱን አስመልክተው ገለፃ ያደረጉት የከፍተኛ ትምህርት ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ልሳን ወርቅ ተስፋሁን በዚህ አመት 19 ጥናቶች የቀረቡ መሆኑንና 12ቱ መሠረታዊ ጥናትና ምርምሮች፣ 7ቱ ደግሞ ድርጊታዊ ጥናትና ምርምሮች ናቸው ብለዋል። ዳይሬክተሩ አያይዘውም ቢሮው የትምህርት ችግሮች በጥናትና ምርምር ተለይተው እንዲፈቱ ፍላጎት ያለው መሆኑን አስረድተዋል። ለተሸላሚዎች የገንዘብ ሽልማት ያበረከቱት የትምህርት ቢሮ ም/ሃላፊ አቶ ወንዶሰን አቢ እንደተናገሩት ወቅቱ በርካታ ችግሮችን ያሳለፍንበት ስለነበር በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ጥናትና ምርምር በማድረግ የተሳተፋችሁና አሸናፊ ሆናችሁ የተሸለማችሁ እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በማጠቃለያው ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የአብክመ ትምህርት ቢሮ ም/ሃላፊ  አቶ መኳንንት አደመ በትምህርት ስርዓቱ ያሉ ችግሮች የምንፈታው አዝማሚያ በመገምገም ሳይሆን በጥናትና ምርምር በመሆኑ ጥናት አቅራቢዎችን አመስግነዋል። የተሻለውን ጥናትና ምርምር ሙያዊ በሆነ መንገድ በመገምገም እንዲለይ ያደረጉትን የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ምሁራንም ያመሰገኑት ም/ሃላፊው የኮሌጆች ጥናትና ምርምር በየአመቱ እንዲካሄድ ትምህርት ቢሮው በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
ከ1ኛ እስከ 5ኛ ለወጡት ጥናት አቅራቢዎች  ከ10,000-6,000 ብር ድረስ የገንዘብ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን የጥናት ውጤታቸውን በአለም አቀፍ ጆርናል ከሁለት በላይ አርቲክል ያሳተሙ ተመራማሪዎችም የ10,000 የገንዘብ ሽልማት ሲበረከትላቸው በአገር አቀፍ ጆርናል አንድ አርቲክል በጆርናል ያሳተመ ተመራማሪም የ5000ብር የገንዘብ ሽልማት ተሰጥቷል። በአጠቃላይ በጥናቱ ለተሳተፉ ተመራማሪዎች ለእያንዳንዳቸው የ4000ብር የገንዘብ ሽልማትና የምስክር ወረቀት በመስጠት ሲምፖዚየሙ በስኬት ተጠናቋል።
4.1K views15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 07:16:33
4.8K views04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 12:44:02 የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና መስጫ ጊዜ ይፋ ሆነ።
.........................................................................
ግንቦት 10/2015 ዓ.ም (ትምህርት ቢሮ) የትምህርት ሚኒስቴር የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን አሳውቋል።

የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም ድረስ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል።

ዩኒቨርሲቲዎችም ያላቸውን ስራ በማጠናቀቅ ከሐምሌ15/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
4.5K views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 11:15:29
4.4K views08:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 11:15:19 የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና መስጫ ጊዜ ይፋ ሆነ።
.........................................................................
ግንቦት 10/2015 ዓ.ም (ትምህርት ቢሮ) የትምህርት ሚኒስቴር የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን አሳውቋል።

የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም ድረስ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል።

ዩኒቨርሲቲዎችም ያላቸውን ስራ በማጠናቀቅ ከሐምሌ15/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
5.3K views08:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 12:18:10
4.9K views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 12:17:27 የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ በ2015 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚፈተኑ ተማሪወች የስነልቦና ስልጠና ሰጠ፡፡
መምሪያው ከደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ በተጋበዙ ምሁር አማካኝነት በተያዘው የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚፈተኑ ተማሪዎች የስነልቦና ስልጠና ሰጥቷል፡፡
በስልጠናው ላይ የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ደሳለኝ በላቸው እና የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል፡፡
በስልጠናው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ማህበራዊ ጉዳይ አማካሪ አቶ በፍርዱ ወጨፎ እንዳሉት ተማሪወች በስነምግባር የታነጹ እና ጥሩ አስተሳሰብ ያላቸው ሁነው በትምህርታቸው ውጤታማ ለመሆን መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡ የሀገራችን እጣ ፈንታ በተማሪወች እጅ መሆኑንም ተናግረው ሀገራችን ወደ ጥሩ መንገድ ለመውሰድ እና መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት ተማሪወች በትጋት እንዲሰሩም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በስልጠናው ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ደሳለኝ በላቸው ተማሪዎች ፈተናውን በአሸናፊነት ለማጠናቀቅ በተገቢው ሁኔታ መዘጋጀት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡ በቅርቡ በሚሰጠው ሀገር አቀፍ ፈተና ላይ ጥሩ ውጤት ለሚያመጡ ተማሪወች የከተማ አስተዳደሩ የማበረታቻ ሽልማት እንደሚሰጥም ቃል ገብተዋል፡፡

የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አቶ እየበሩ አእምሮ እንዳሉት በዘንድሮው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ላይ የከተማ አስተዳደሩ ተማሪወች ጥሩ ውጤት እንዲያመጡ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከመደበኛው መማር ማስተማር ጎን ለጎን የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን፣ ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ ቤተመጽሀፍት ለተማሪወች አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን እና በመምህራን ወርክ ሽቶችና የባለፉ አመታት ሽቶች እየተሰሩላቸው መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የባለፈው አመት የተማሪወች ውጤት አጥጋቢ እንዳልነበርም ጠቁመው በዘንድሮው አመት ግን ጥሩ ውጤት እንዲመጣ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው ባለድርሻ እና አጋር አካላትም ርብርብ እንዲያደርጉ አቶ እየበሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ለተፈታኝ ተማሪወች የስነልቦና ስልጠናውን የሰጡት የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ መምህር እሱባለው ነጋ “የስኬት ቁልፍ” በሚል ርእሰ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ስልጠና የሰጡ ሲሆን የትኛውንም አይነት ጉዳይ ለመፈፀም የአእምሮ ዝግጁነት አስፈላጊ በመሆኑ ተማሪወች በአእምሮ ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡ ተማሪወች ውጤታማ ለመሆን በራሳቸው ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸውም ገልፀው የአሸናፊነት ስነልቦናን መላበስ እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል፡፡
አመለካከት፣ እይታ እና መነቃቃት የስኬት ቁልፍ መሆናቸውንም ጠቅሰው ተማሪወች እነዚህን ነገሮች በጥሩ ሁኔታ በመገንባት ውጤታማ እንዲሆኑም መምህር እሱባለው መክረዋል፡፡

በስልጠናው ላይ የተሳተፉ ተማሪወችም በሰጡት አስተያየት በቅርቡ ለሚሰጠው ሀገር አቀፍ ፈተና ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ጠቁመው የተሰጣቸው ስልጠናም መነሳሳትን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡ እንደነዚህ አይነት ስልጠናወች ጥሩ ስነልቦናን ለመገንባት ጠቃሚ በመሆናቸው ያገኙትን ስልጠና ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ለመሆን እንደሚሰሩም ገልፀዋል፡፡
4.7K views09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 14:07:56 የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በመጭው ሐምሌ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራ እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ፡፡
==================
ግንቦት 3/2015 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ በመጭው ሐምሌ ወር ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት ስራ እያከናወነ መሆኑን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ማተብ ታፈረ /ዶ/ር/ ዛሬ ተናግረዋል፡፡
በአማራ ክልል 215590 ተማሪዎች በ574 አስፈታኝ ትምህርት ቤቶች ምዝገባ መጠናቀቁን የተናገሩት ቢሮ ኃላፊው ተማሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ከአመቱ መጀመሪያ ጀምሮ ሰፊ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ያለፈው ዓመት የተማሪዎች ውጤት ዝቅተኛ መሆኑን ዉጤቱ ተተንትኖ ከትምህርት ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ መግባባት መደረሱን ያወሱት ኃላፊው በጋራ በመስራት ከችግሩ ለመውጣት የቤት ስራችንን የምንሰራበት ጊዜው አሁን እንደሆነ አክለው ገልፀዋል፡፡
ወላጆች በተማሪዎች መማር ክትትልና ተሳትፎ ከወትሮው በተለየ የተሻለ መሆኑ፣ መምህራን የትምህርት ይዘቱን በጊዜው እንዲሸፈንናለተማሪዎችን ወርክሽቶች በመስራት እንዲሁም ተማሪዎች በጥናታቸው ላይ በቁጭት መስራታቸው በቀጣይ ውጤታማ ለመሆን ያግዛል ተብሏል፡፡
በክልል ደረጃ ለተማሪዎች ሞዴል ፈተና እየተዘጋጀ መሆኑን የገለጹት ቢሮ ኃላፊው በመጭው ሰኔ መጨረሻ ፈተናው ይሰጣል፡፡ ይህም ለተማሪዎች ዝግጅት እንደሚያግዛቸው ተጠቅሷል፡፡
ባለፈው ፈተና የታዩ የተማሪዎች የስነ ምግባር ችግር በዚህ ዓመትም እንዳይደገሙ ተከታታይ የሆኑ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የተናገሩት ኃላፊው ወደ ፈተና ማዕከል የሚመጣ ተማሪ የስነ ምግባር ጉድለት ከታየበት የሚመለከተው አካል የማይታገስ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ለዚህም ወላጆች ጭምር ሃላፊነት መውሰድ እንዳለባቸው ነው የተገለፀው፡፡
በፈተና ወቅት በተማሪዎች የስነ ምግባር ጉድለት እንዳይኖር ወላጆችና መላው ማህበረሰብም ኃላፊነቱን እንዲወጣ ቢሮ ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
10.0K views11:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ