Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Education Bureau

የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau A
የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau
የሰርጥ አድራሻ: @anrse
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.56K
የሰርጥ መግለጫ

Quality Education

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-03-04 11:46:29
2.3K views08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 11:45:51 የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ከትምህርት አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ጋር በደብረ ማርቆስ ከተማ የ6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እያካሄደ ነው።
========================
የካቲት 25/2015 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ/ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ከትምህርት አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ጋር በደብረ ማርቆስ ከተማ የ6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እያካሄደ ነው።

በግምገማ መድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ማተብ ታፈረ /ፒ.ኤች.ዲ/ በትምህርት ስርዓታችን ውስጥ የሚስተዋሉ ችግሮች በሚፈጥሩት ቁጭት መተከዝ ሳይሆን ለለውጥ መስፈንጠሪያ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል። የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ የህዝባችን ከፍታ ለማስጠበቅ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ኃላፊው ተናግረዋል። አሁን በትምህርት ዘርፉ ላይ የተፈጠረው የአመራር መደጋገፍና መደማመጥ ለላቀ ለውጥ መጠቀም እንደሚገባም አመላክተዋል።

መምህራን እና የትምህርት አመራሮች የሚቀጥለውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች በአግባቡ ለፈተና ማዘጋጀት እንደሚገባቸው ኃላፊው አሳስበዋል።

የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አያሌው ሀገር የምትከበረው፣ የምትቀጥለውና የምታደርገው በእውቀት በመሆኑ ትምህርት ላይ መስራት የዘመኑ አመራር ልዩ ተልዕኮ መሆን እንዳለበት አመላክተዋል።

በመድረኩ የክልሉ ትምህርት ያለፉት ስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት፣ የ2014/15 ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ውጤት ትንተና ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግበትና ቀጣይ አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡ ይጠበቃል።


ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
2.3K views08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 19:07:05
1.7K views16:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 19:06:26 የአማራ ክልል ትምሕርት ዘርፍ አመራሮች በምስራቅ ጎጃም ዞን በሚገኙ የተመረጡ ትምህርት ቤቶች ጉብኝት አካሂደዋል።
==============================
የካቲት 24/2015 ዓ.ም /የአማራ ክልል ትምሕርት ቢሮ/ የዞን፣ ከተማ አስተዳደር ፣ የወረዳ ትምሕርት አመራሮች፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምሕርት ቤት ርዕሳነ መምህራንና ሱፐርቫዘሮች የመምህራን ትምህርት ኮሌጅ አመራሮች በምስራቅ ጎጃም ዞን በተመረጡ አስራ አንድ ወረዳዎች በሚገኙ ትምህርትቤቶች የመስክ ጉብኝትና የልምድ ልውውጥ አካሂደዋል።

በጉብኝቱ የተማሪዎች የፈጠራ ስራዎች፣ ተጨማሪ መማሪያ ክፍሎች ግንባታ፣ የመማር ማስተማር ተግባራት፣ የቤተ ሙከራና ቤተ መጽሐፍት አደረጃጀቶች፣ የትምህርትቤቶችን አረንጓዴ ችግኞች ልማትና ሌሎችም ተግባራት አይተዋል።

በማቻከል ወረዳ አማኑኤል ከተማ ጉብኝት ማዕከል የተገኙት የምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አያሌው ትምህርት ላይ በመስራት በየትኛውም ዘርፍ ላይ ተወዳዳሪ ዜጋ መፍጠር እንደሚገባ ተናግረዋል። ዞኑ ማህበረሰቡንና አጋር አካላትን በማስተባበር ከትምህርት ቤት ግንባታ እስከ ክፍል ውስጥ መማር ማስተማር ድረስ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በዚህም የምስራቅ ጎጃም ዞን ትምህርት እየተነቃቃ መሆኑን ኃላፊው አመላክተዋል።

የማቻከል ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ታምሩ ዘውዴ በወረዳው በህብረተሰብ ተሳትፎ፣ በቀድሞ ተማሪዎች ትብብርና በአማራ ልማት ማህበር አማካኝነት በርካታ የመማሪያ ክፍሎች መገንባታቸውን ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ትምሕርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙለው አበበ የትምሕርት አመራሮች በጉብኝቱ የተገኙ መልካም ተሞክሮችን በመቀመርና በመተግበር የክልሉን ትምሕርት የበለጠ ለማሻሻል መስራት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።

ያነጋገርናቸው የጉብኝት ተሳታፊዎች በጉብኝቱ ጥሩ ተሞክሮ ማግኘታቸውን ገልጸዋል። በጉብኝቱ ያዩአቸውን መልካም ተሞክሮዎች በመቀመር በየትምሕርት ተቋሞቻቸው እንደሚተገብሩት ተናግረዋል።

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
1.7K views16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 09:12:26

948 views06:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 21:28:00 የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሙሉ ስኮላርሺፕ መሰጠቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ሙሉ ስኮላርሺፕ መስጠቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ፡፡
በዛሬው ዕለት የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወስደው ከግማሽ በላይ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች ውስጥ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች እውቅና ተሰጥቷል፡፡
የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅና በተሰጠበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በመልዕክታቸው፥ "ለተማሪዎቹ እንኳን ደስ ያላችሁ ካሉ በኋላ የተሰጣቸውን ፈተና በአግባቡ መስራት በመቻላቸው ኢትዮጵያን የሚያግዙ 273 ተማሪዎች ተገኝተዋል በዚህም ደስታ ይሰማናል" ብለዋል፡፡
ተማሪዎቹ እጅግ ዘመናዊ በሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እንደሚከታተሉና ለኢትዮጵያ እና አፍሪካ የሚደርሱ እንዲሆኑም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ተማሪዎቹ በርትተው ተምረው ሀገራቸውን ሳይረሱ የሚጠቅሙ እንዲሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
"ሁሉም ተማሪ ጥበብን እንዲሻ እና ሀገሩን ለመለወጥ እንዲሰራ ጠይቀዋል፤ በተለይም ለእውነት የቆመ ተማሪ ነገ ሃገሩን ይለውጣል፤ እናንተ የላቀ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎችም እውነትን የምትሹ መሆን አለባችሁ እንደዛ ሲሆን ደግሞ ሀገርን የምትገነቡ ትሆናላችሁ ብለዋል።
"በትውልዶች ግንባታ ላይ ነው፤ ያለፈው ትውልድ አልፏል አሁን ያለው ትውልድም አነሰም በዛም ለሀገሩ እየለፋ ነው፤ እናንተ ግን ገና ከምንጩ ለሀገራችሁ የምትጠቅሙ እንድትሆኑ ከሰፈራችሁ ወጣ ብላችሁ ለሀገር እንድታስቡና ቀድሞ የነበሩ ስመጥር ኢትዮጵያውያን ምሁራን ከእናንተ ውስጥም እንዲወጡ አደራ እንላችኋለን" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
በሽልማት ስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው፥ "እንደ መንግስትና ትምህርት ሚኒስቴር የተጀመረው ለውጥ የፈተናዎችን ቅቡልነት በማረጋገጥ ቢሆንም በሁሉም መስኮች የሚስተዋሉ የትምህርት ስብራቶችን መጠገንና በሁሉም መመዘኛ ብቁ የሆኑ ተማሪዎችንና ጠንካራ ዜጎችን ለመፍጠር እንተጋለን" ብለዋል፡፡
በዚህ የለውጥ ሂደት ደግሞ ተጠቃሚውም ተጎጂውም ህብረተሰቡ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ በቀጣይም ብቁ ተማሪዎችን የመፍጠሩ ሂደትና የትምህርት ጥራትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
እውቅና የተሰጣቸው ተማሪዎች በተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት መስክ ከ700 ድምር ውጤት ከ600 በላይ ያመጡ 263 ተማሪዎች እና በማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ዘርፍ ከ600 ድምር ውጤት ከ500 በላይ ያመጡ 10 ተማሪዎች መሆናቸው ተመላክቷል፡፡
ለሁሉም ተማሪዎችም ላፕቶፕ በሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ via Fana
2.1K views18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 21:27:13
1.9K views18:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 21:27:12
1.8K views18:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 17:02:47
1.1K views14:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 17:01:46 የሴት ተማሪዎች የንጽሕና መጠበቂያ ክፍልና የንጹህ መጠጥ ውኃ ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ኾነ።
===================================================
የካቲት 21/2015 (ትምህርት ቢሮ) በባሕር ዳር መሰናዶ ትምህርት ቤት የሴት ተማሪዎች መጸዳጃ ቤት፣ የንጹህ መጠጥ ውኃ እና ውኃ ማጣሪያ ተገንብቶ ለአገልግት ክፍት ኾኗል፡፡
የባሕር ዳር መሠናዶ ትምህር ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ ትዕይንት አባተ ሴት ተማሪዎች በትምህርት ቤቱ ውስጥ ባለው መጸዳጃ ቤት ለመጠቀም እንደሚቸገሩ ተናግራለች፡፡
በርካታ ሴት ተማሪዎች የንጽሕና መጠበቂያ ቁሳቁስ ይዘው መጥተው መቀየሪያ ቦታ በማጣት ትምህርታቸውን አቋርጠው ወደቤታቸው ይኼዱ ነበር ፤ ባስ ሲልም ትምህርታቸውን ያቋርጡ እንደነበር ተናግራለች፡፡
የ11ኛ ክፍል ተማሪዋ መሰረት ብነግረው እሷን ጨምሮ ኹሉም ሴት ተማሪዎች በወር አበባቸው ወቅት የትምህርት ክፍለ ጊዜያቸውን አቋርጠው ወደ ቤታቸው ይሄዱ እንደነበር ተናግራለች፡፡ ይህም በሴት ተማሪዎች የትምህርት ውጤት ላይ ተጽዕኖ እንዳለው ተናግራለች፡፡
ተማሪ መሠረት አሁን የተሠራው መፀዳጃ ቤት ብቻ ሳይኾን የገላ መታጠቢያ እና የንጽሕና መጠበቂያ ክፍል ያለው በመኾኑ ተማሪዎች በአግባቡ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ይረዳል ብላለች፡፡
የባሕር ዳር መሠናዶ ትምህርት ቤት መምህሩ ቁምላቸው አይተንፍሱ በትምህርት ቤቱ በተለይ ሴት ተማሪዎች በወር አበባ ወቅት ትምህርታቸውን አቋርጠው ይሄዱ እንደነበር ጠቅሰዋል፡፡ አሁን የተገነቡ የመጸዳጃ ቤቶች፣ የንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት የሴት ተማሪዎችን ችግር ይቀርፋል ነው ያሉት።
በትምህርት ቤቱ የነበረው የውኃ መሥመር ያረጀ እና የሚቆራረጥ በመኾኑ ሲያነቡ ለመዋል የሚመጡ ተማሪዎች ይቸገሩ እንደነበረ ጠቅሰዋል፡፡ አሁን 60 ሺህ ሊትር ውኃ የሚይዝ ታንከር መገንባቱንም አንስተዋል፡፡ ውኃው ለመጠጥ እና ለመታጠቢያ ተብሎ የተከፈለ በመኾኑ ተማሪዎች ለይተው እንዲጠቀሙም ተናግረዋል፡፡
ከዓባይ ባንክ ጋር በጋራ በመኾን ነዉ ስፕላሽ ኢንተርናሽናል ለትምህርት ቤቱ አገልግሎት መስጫውን የገነቡት። የስፕላሽ ኢንተርናሽናል የባሕርዳር አካባቢ ተወካይ መኮንን አዲሱ ተቋሙ ትምህርት ቤቶች የተሻሻለ መጸዳጃ ቤት፣ ንጹሕ የመጠጥ ውኃ አቅርቦት እና ምቹ የኾነ የንጽሕና መጠበቂያ ቦታ እንዲኖር አጥብቆ እንደሚሠራ ተናግረዋል፡፡
አቶ መኮንን ስፕላሽ ኢንተርናሽናል በባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር በ16 ትምህርት ቤቶች ላይ ደረጃውን የጠበቀ የሴቶች መጸዳጃ ቤት፣የእጅ መታጠቢያ፣ የንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት እና ውኃውን አጣርቶ የማቅረብ ሥራ እየሠራ መኾኑን ተናግረዋል፡፡
ፕሮጀክቱ ከሰኔ 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 2016 ዓ.ም የሚቆይ ሲኾን በ54 ትምህርት ቤቶች ላይ እንደሚሠራ ተናግረዋል፡፡ እስካሁን በ3 ትምህርት ቤቶች ላይ ሠርቶ ማጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ ለሥራው ከ3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉንም አንስተዋል፡፡
የዓባይ ባንክ የባሕር ዳር ዲስትሪክት ሥራ አስኪያጅ ሲሳይ ጸጋዬ ባንኩ ማኅበራዊ ኀላፊነቱን ለመወጣት እየሠራ መኾኑን አንስተዋል፡፡ ለሥራው 8 መቶ 50 ሺህ ብር ድጋፍ ማድረጉን እና ይህን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
ስፕላሽ ኢንተርናሽናል ከአባይ ባንክ ጋር በመተባበር በባሕር ዳር መሰናዶ ትምህርት ቤት ያስገነባውን የሴቶች መጸዳጃ ቤት እና ንጹህ የመጠጥ ውኃ ማጣሪያ ግንባታ አጠናቆ ለትምህርት ቤቱ ማስረከቡን አሚኮ ዘግቧል፡፡

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
1.1K views14:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ