Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Education Bureau

የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau A
የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau
የሰርጥ አድራሻ: @anrse
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.56K
የሰርጥ መግለጫ

Quality Education

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-05-02 11:03:14
ከሚያዚያ 24_ ግንቦት 03 ቀን2015 ዓ ም በዘመቻ የሚሰጠውን የማህጸን በር ካንሰር እና የኮቪድ_19 በሽታ መከላከያ ክትባት አገልግሎት ህብረተሰቡ እንዲጠቀም የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ጥሪ አቀረበ።
ቢሮው ለ10 ቀናት በክልሉ በሁሉም ዞኖች በዘመቻ የሚሰጠውን የክትባት አገልግሎት አስመልክቶ ሚያዘውያ 23/2015 ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
በቢሮው የክትባት ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ወርቅነህ ማሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን ክትባት ዘመቻ በክልሉ ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት ተደረጓል፤ህብረተሰቡም የክትባት አገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።
የማህጸን በር ካንሰር ክትባት ከሚያዚያ 24 እስከ 27 ቀን ለተከታታይ 4 ቀናት እድሜያቸው 14 ዓመት ለሆናቸው ሴቶች በትምህርት ቤቶች፣በጤና ተቋማትና ጊዚያዊ ጣቢያዎች እንደሚሰጥ የጠቆሙት አስተባባሪው የኮቪድ በሽታ መከላከያ ክትባት ደግሞ ከሚያዚያ 28 እስከ ግንቦት 03 ቀን እድሜያቸው 18 ዓመትና ከዚያ በላይ ለሆናቸው ወገኖች ይሰጣል ብለዋል።
በዘመቻው ከ5 መቶ 70 ሽህ በላይ ሴቶች የማህጸን በር ካንሰር በሽታ መከላከያ ክትባት ለመስጠት መታቀዱን የገለጹት አቶ ወርቅነህ ማሞ መምህራን፣ወላጆችና ማህበረሰቡ 14 ዓመት የሆናቸው ሴቶች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጠይቀዋል።
ከ11 ሚሊዮን በላይ ወገኖች የኮቪድ_19 በሽታ መከላከያ ክትባት ወስደዋል፤በዚህ ዘመቻ ደግሞ 3 ሚሊዮን 5 መቶ ሽህ ሰዎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መታቀዱን አስተባባሪው አሳውቀዋል።
መረጃው የአብክመ ጤና ቢሮ ነው፡፡
10.9K views08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 11:41:04
8.4K views08:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 11:41:02 የጎንደር ከተማ በተፋጠነ መንገድ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል ሂደትን ከባለድርሻ አካላት ጋር ገመገመ።
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
የትምህርት ቤቶች ደረጃ መሻሻል ለማሻሻል አዝጋሚ ሂደትን መከተል አስፈላጊ አለመሆኑን የጎንደር ከተማ ትምህርት ከባለድርሻ አካላት ጋር ባካሄደው ውይይት ገልጽል፡፡ መምሪያው አያይዞም ከዚህ ችግር በመውጣት የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በተፋጠነ ሁኔታ ደረጃ ማሻሻል ላይ አልመው እንዲሰሩ ከትምህርት ተቋማት ባለሃብቶች፣ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ያደረገ ሲሆን በተለይም ከኢንስፔክሽን ግምገማ ውጠየትን መሰረት አድርገው መስራት እንዳለባቸው የጎንደር ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳንዔል ውበት አስታውቀዋል፡፡
በግምገማ መድረኩ የተሳተፉ የትምህርት ተቋማት አመራሮችና ባለሃብቶች የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል ሂደት አቅደው እንደሚሰሩ ገልፀዋል።
በግምገማ መድረኩ ትምህርት ቤቶች የህብረተሰቡን ተሳትፎ በማሳደግም ሆነ ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም የውስጥ ገቢያቸውን አሳድገው የትምህርትቤቶቻቸውን ደረጃ ማሻሻል እንዲችሉ የተገለፀ ሲሆን የመንግስት ትምህርት ቤቶች የተመደበላቸውን የድጎማ በጀት ለታለመለት አላማ ማዋላቸውን ክትትል እንደሚደረግ መምሪያ ሃላፊው አስረድተዋል፡፡
በቀጣይ አመት ደረጃ 1 የሆኑ የመንግስት ተቋማት እንዲሁም ደረጃ 1 እና 2 የሆኑ የግል ትምህርት ተቋማት መቀጠል እንደማይችሉ አውቀው ሁሉም ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን በመፈፀም፣ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ደረጃቸውን በማሻሻል ማህበረሰባዊ ቅቡልነትን ማረጋገጥ እና ከተቋሙ የሚጠበቀውን ውጤት ማስመዝገብ እንደሚጠበቅ በውይይቱ ማጠቃለያ የጋራ ተደርጓል፡፡
መረጃው የጎንደር ከተማ ትምህርት መምሪያ ነው
8.4K views08:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 11:40:54
7.4K views08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 10:07:06 የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ለእስልምና እምነት ተከታይ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የትምህርት ባለሙያዎች፣ የትምህርት አመራሮች እና የተማሪ ወላጆች እንዲሁም የትምህርት ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለ1444ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።
ኢድ ሙባረክ!!

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ
2.4K views07:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 17:42:07
የአብክመ ትምህርት ቢሮ የ9 ወር እቅድ አፈፃፀሙን ገመገመ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዝያ 12/2015 -ባህርዳር
የአብክመ ትምህርት ቢሮ በ9 ወሩ የተከናወኑ ተግባራትን ከአጠቃላይ ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሂዷል። በውይይቱም ለ8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች እየተደረገ ያለውን እገዛ ይበልጥ በማጠናከር ተማሪዎችን ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባ መግባባት ላይ ተደርሷል። የትምህርት ስራን በዲጂታል ቴክኖሎጅ ማገዝ እንደሚገባም ከሰራተኞች ሀሳብ የተሰጠ ሲሆን የበጀት አመቱን የትምህርት ስራ በውጤታማነት ለማጠናቀቅ በቀጣይ 3 ወራት በትኩረት ተይዘው መፈፀም ያለባቸው ስራዎች ተመላክተዋል።
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
1.7K views14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 15:59:40
ማስታወቂያ

የተባበሩት ኤምሬትስ የሰጠውን ስኮላርሽፕ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ ተማሪዎች ሁሉ
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግስት በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል ለመስጠት በፈቀደው መሰረት ቀደም ሲል በተማሪዎች ቃል የተገባላችሁ ተማሪዎችና በዕድሉ ለመጠቀም ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች Application Form link:
http://survey.ethernet.edu.et/index.php/518562?lang=en --
በመግባት ከዛሬ 09/08/15 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 ቀናት ከላይ በተቀመጠው ሊንክ በመግባት፡-
1. የ12ኛ ክፍል የማትሪክ ውጤት ኮፒ (Grade 12 Result) copy
2. ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ኮፒ (Grade 9-12 transcript) copy
3. CV/ Curriculum Vitae copy
4. የልደት የምስክር ወረቀት ኮፒ (Birth Certificate) copy እና ሌሎች በሊንኩ የተጠቀሱ መረጃዎችን እንድትሞሉ እናሳስባለን ።
መረጃዎች ተጣርተው ለፈተና የሚቀረቡ ተማሪዎችን ስም ዝርዝር በቀጣይ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የምናሳውቅ መሆናችንን እንገልጻለን።
የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር
አዲስ አበባ
4.5K views12:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 14:46:16
ለክርስትና እምነት ተከታይ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የትምህርት ባለሙያዎች፣ የትምህርት አመራሮች እና የተማሪ ወላጆች እንዲሁም የትምህርት ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለጌታችን መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ!! አደረሰን!! በዓሉ የሰላም፣የፍቅር፣የመተሳሰብ፣ የአንድነት በዓል እንዲሆንላችሁ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምኞቱን ይገልጻል፡፡
መልካም የትንሳኤ በዓል!!
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ
1.6K views11:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 14:39:30
2.8K views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 14:38:42 አይ አር ሲ የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት በ24 ሚሊዮን ብር ወጭ ያሳተማቸውን ከ87 ሽህ በላይ የአንደኛ ደረጃ የመማሪያ መጽሐፍት ለትምህርት ቢሮ አስረከበ።
===============================
ድርጅቱ በ24 ሚሊዮን ብር ወጭ ያሳተማቸውን 87 ሽህ 590 ከአንደኛ እስከ አራተኛ ክፍል በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የተዘጋጁ የተማሪዎች የመማሪያ መጽሐፍት ለትምህርት ቢሮ አስረከቧል።

መጽሐፍቱ በጦርነቱ ጉዳት ለደረሰባቸው 162 ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ 56 ሽህ የሚሆኑ ተማሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን የአይ አር ሲ ድርጅት የአማራ ክልል አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ ሞላ ገልጸዋል።

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ወንድወሰን አቢ አይ አር ሲ ትምህርትን በአደጋ ጊዜ ማስቀጠል መርሀ ግብር በክልሉ በርካታ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል። ድርጅቱ በተለየ ሁኔታ ከትምህርት ቢሮ የቀረበለትን የመጽሐፍት ህትመት ጥያቄ ተቀብሎ በማሳተሙ አመስግነዋል። ሌሎች አጋር ድርጅቶችም መጽሐፍት አቅርቦት ላይ የበኩላቸውን እንዲወጡ አቶ ወንድወሰን ጥሪ አቅርበዋል።


ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
2.9K views11:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ