Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Education Bureau

የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau A
የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau
የሰርጥ አድራሻ: @anrse
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.56K
የሰርጥ መግለጫ

Quality Education

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-03-05 20:54:30
1.1K views17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 20:54:16 ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ የአማራ ክልል ተማሪዎች ነገ ይሸለማሉ።
=======================
የካቲት 26/2015 ዓ.ም (ትምህርት ቢሮ) ነገ የካቲት 27/ 2015 ዓ.ም ከጧቱ 2:30 ጀምሮ በ2014/15 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ወስደው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 294 ተማሪዎች እውቅናና ሽልማት ይሰጣል።
የእውቅና እና ሽልማት ስነ ስርዓቱ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በሁሉም ሚዲየሞች በቀጥታ ይተላለፋል። የሽልማት ስነ ስርዓቱ ከጧቱ 2:30 ሰዓት ጀምሮ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን /አሚኮ/ በቴሌቭዥንና ሬድዮ እንድትከታተሉ እንጋብዛለን።

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
1.1K views17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 17:27:01
1.7K views14:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 17:26:44
1.7K views14:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 17:26:33
1.4K views14:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 17:26:13 ቀጣዩን የቴክኖሎጂ ዘመን በአግባቡ የሚጠቀምና የሰለጠነ ማህበረሰብ ለማፍራት በትኩረት ልንሰራ ይገባል። ማተብ ታፈረ /ዶክተር/
========================
የካቲት 26/2015 ዓ.ም (ትምህርት ቢሮ) የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ከትምህርት አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ጋር በደብረ ማርቆስ ከተማ የ6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የልምድ ልውውጥ አካሂዷል።

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ማተብ ታፈረ /ዶክተር/ ቀጣዩን የቴክኖሎጂ ዘመን በአግባቡ የሚጠቀምና የሰለጠነ ማህበረሰብ ለማፍራት በትኩረት መሰራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ለዚህም መምህራንና የትምህርት ዘርፉ አመራሮች የመማር ማስተማር ባህልን የበለጠ ለማሻሻል መስራት እንዳለባቸው ኃላፊው አሳስበዋል።

ኃላፊው የትምህርት ተቋማትን ደረጃ ለማሻሻል ከህብረተሰቡ ጋር በጋራ መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል። በመንግስት ትምህርትቤቶች ከሚቀጥለው አመት ጀምሮ ደረጃ አንድ ላይ የሚገኙ ሁሉንም ተቋማት ወደ ደረጃ ሁለትና ከዚያ በላይ ለማሳደግ እንዲሁም በየዞኑ ሞዴል የሆኑ ደረጃ አራት ትምህርትቤቶችን ለመፍጠር ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጋራ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። ደረጃቸውን ያላሟሉ የግል ትምህርትቤቶች ከሚቀጥለው አመት ጀምሮ ተማሪዎችን መቀበል እንደማይችሉ ተረድተው ከወዲሁ ደረጃቸውን ለማሻሻል እንዲሰሩ ኃላፊው አመላክተዋል።

በቀጣይ ለሚፈተኑ የ8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በተለየ መንገድ ድጋፍና ክትትል ማድረግ እንደሚገባም ተገልጿል።

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
1.9K views14:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 17:23:06
1.4K views14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 17:22:27 የምስራቅ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ሽልማት ሰጠ።
===========================
የካቲት 26/2015 ዓ.ም (ትምህርት ቢሮ) በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 600ና በላይ ላስመዘገቡ 8 ተማሪዎች የገንዘብና የቁሳቁስ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

ትምህርት መምሪያው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ሽልማት የሰጠው የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ 2015 በጀት ዓመት የ6 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የመስክ ስራዎች ልምድ ልውውጥ በደብረ ማርቆስ ከተማ ባካሄደው መድረክ ላይ ነው።


ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
1.6K views14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 15:35:26
2.1K views12:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 15:34:49 በአስራ አምስት ሚሊዬን ብር ወጭ ሞዴል ቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ።
=================
የካቲት 25/2015 ዓ.ም /ትምህርት ቢሮ / በምስራቅ ጎጃም ዞን በአማኑኤል ከተማ አስተዳደር በአልማ ድጋፍና በህብረተሰብ ተሳትፎ በ15 ሚሊዬን ብር ወጭ ለሚገነባው ሞዴል ቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የካቲት 24/2015 ዓ.ም የመሰረተ ድንጋይ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙላው አበበ እና የምስራቅ ጎጃም ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አያሌው በተገኙበት ተቀምጧል።

ትምህርት ቤቱ በ5ሽህ አምስት መቶ ካሬ መሬት ላይ የሚገነባ እንደሆነ ተገልጿል።

የአማኑኤል ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ አማረ ሰውነት የትምህርት ጉዳይ የሁሉም የህብረተሰብ ድርሻ ነው። ከተማ አስተዳደሩ አዲስ ቢሆንም እንኳ ለትውልድ ግንባታ ቅድሚያ በመስጠት በአልማ ድጋፍና በህብረተሰብ ተሳትፎ ትውልድን የሚቀርፅ የትምህርት ቤት ግንባታ የሚሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ህዝረተሰቡ ሰርተን ካሳየነው በገንዘቡም ሆነ በጉልበቱ መጀመር ብቻ ሳይሆን መጨረስ እንደሚችል አመላክተዋል።

የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አያሌው ትምህርት ቤት ማለት እናት ናት በኢኮኖሚና በፖለቲካ እንዲሁም በሁሉም ዘርፍ ጀግና የሆነ መሪና ተመራማሪ የሚፈጠሩበት መሆኑን ገልጸዋል። የትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጣልበት ቅድመ አንደኛ ላይ ዞኑ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል።


ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
2.1K views12:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ