Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Education Bureau

የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau A
የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau
የሰርጥ አድራሻ: @anrse
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.56K
የሰርጥ መግለጫ

Quality Education

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-02-28 10:11:33
2.0K views07:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 10:10:53 የደቡብ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ሽልማት ሰጠ፡፡
===========================================
ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ 3 ተማሪዎች የዞኑ ተምህርት መምሪያ ለእያንዳንዳቸው የ10 ሽህ ብር ሽልማት አበርክቶላቸዋል።

የደቡብ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደስታ አስራቴ ተሽላሚ ተማሪዎቹ የላቀ ውጤት በማስመዝገባቸው ክልላችንና ሀገራችን ለኩራት ያበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ለተማሪዎቹ ውጤታማነት ከመምህራን ባሻገር የተማሪ ወላጆች ልጆቻቸውን ኮትኩተውና ደግፈው በማብቃታቸው መሆኑን ኃላፊው ገልጸዋል።

በሽልማቱ ላይ የተገኙት የተማሪ ዮሐንስ አድማሱ ወላጅ አባት አቶ አድማሱ ልጃቸው ከፍተኛ ውጤት በማምጣቱ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ በቀጣይ ልጃቸው ውጤታማ እንዲሆን የሚሟሉ የመማሪያ ቁሳቁሶችን በሟሟላት እገዛና ክትትል እንደሚያደርጉለት ተናግረዋል፡፡ ወላጆች ልጆቻቸው በዕውቀትና በስነ ምግባር ለማነፅ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ አለባቸው ብለዋል። አቶ አድማሱ አክለውም የዞኑ ትምህርት መምሪያ ላደረገው የማበረታቻ ሽልማት አመስግነዋል።
መረጃውን ያደረሱን የደቡብ ጉንደር ዞን ትምህርት መምሪያና የዞኑ ኮሙዩኒኬሽን ናቸው፡፡

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
2.0K views07:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 15:02:24
1.9K views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 15:02:22
2.0K views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 15:02:22
1.9K views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 15:02:21
1.7K views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 15:02:20
1.6K views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 15:02:18
1.6K views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 15:02:16 ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች ገለጻ አደረገ
========================

የካቲት 20/2015 ዓ.ም (ትምህርት ቢሮ) ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም ትምህርት ሚኒሲቴር ባወጣው መመሪያ መሰረት ውጤታቸው 50 በመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ ቁጥራቸው ከአንድ ሽህ በላይ የሆኑ ተማሪዎችን መቀበሉን አስታወቀ፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) እንዳሉት ባለፉት አመታት በነበረው የትምህርት ስርዓት ጥሩ ብቃት ያላቸውና በራሳቸው ሰርተው የመጡ ተማሪዎች እንዳሉ ሁሉ አላማ የሌላቸውና በኩረጃ ጭምር የገቡ እንደነበሩም አይዘነጋም ብለዋል፡፡
በዚህ አመት የገቡ ተማሪዎች ግን በእውቀታቸውና በችሎታቸው እንደ ወርቅ የነጠሩና በአግባቡ ተመዝነው የመጡ ስለሆኑ ዩኒቨርሲቲያችን እነሱን ለማስተማር የሚችሉ በእውቀታቸው፣ በክህሎታቸውና በስነ- ምግባራቸው የበቁ መምህራንን አዘጋጅቷል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም የትምህርት ስርዓቱን ችግር ለመቅረፍ በትምህርት ሚኒስቴር በዘንድሮው አመት የሚጀመረውን የመውጫ ፈተና አሁን ለገቡት ተማሪዎችም ጊዜውን ጠብቆ ስለሚሰጥ እሱንም ከወዲሁ ታሳቢ በማድረግ እራሳቸውን እንዲያበቁና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መዘጋጀት አለባቸው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በመድረኩም የዩኒቨርሲቲው የተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተማሪዎች የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃ አድርገዋል፡፡ እነዚህ የስራ ክፍሎች የተማሪዎች አገልግሎት፣ የስነ ምግባርና ስብዕና ግንባታ፣ የሴቶች፣ህፃናትና ወጣቶች፣የላይብሪና ዶክመንቴሽን፣የረጅስትራርና አሉሙናይ፣የጋራ ኮርሶች ማስተባበሪያ፣የግቢጥበቃና ደህንነት ዳይሬክተሮችና ጽህፈት ቤቶች ሲሆኑ ለተማሪዎቹ የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች እንዲሁም ህግና ደንቦቻቸውን አበራርተዋል፡፡
በመጨረሻም የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ደረጀ አንዳርጌ (ዶ/ር) እንደተናገሩት በዚህ አመት ለገቡ አዲስ ተማሪዎች የሚያስተምሩ መምህራንን ስንመድብ ባለፉት አመታት ከነበሩት አሰራሮች ለየት ያለና ጥንቃቄ የተሞላበት ነው ብለዋል፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያትም በዘንደሮው አመት የገቡት ተማሪዎች እስካሁን ስናስተናግዳቸው ከነበሩት ተማሪዎች በእውቀታቸው የተሻሉ ስለሆኑ በእውቀትም ሆነ በስነ- ምግባር እነሱን የሚመጥኑ መምህራንን መድበናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
1.7K views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 09:51:50 የRemedial ፕሮግራም ምደባ ይፋ ሆኗል።
በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባችሁን ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑንና በተመደባችሁበት የትምህርት ተቋሞች በሚያስተላልፉት ጥሪ መሰረት የ Remedial ፕሮግራሙን እንድትከታተሉ እንገልፃለን ።
ማሳሰቢያ :-
የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማናስተናግድ መሆኑን ከወዲሁ ለመግለጽ እንወዳለን።
የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች
Website:
https://placement.ethernet.edu.et
SMS: 9444
ትምህርት ሚኒስቴር
869 views06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ