Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Education Bureau

የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau A
የቴሌግራም ቻናል አርማ anrse — Amhara Education Bureau
የሰርጥ አድራሻ: @anrse
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.56K
የሰርጥ መግለጫ

Quality Education

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 27

2022-08-23 13:38:00 ትምህርት ቤቶች ሳይንሳዊ እውቀት የሚገበይባቸው ፣የሀገር ፍቅር የሚያድግባቸው ፣እርስ በእርስ መተሣሠብ የሚጎለብትባቸው እንዲሆኑ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
***
ነሐሴ 18/2014 ዓ.ም(ምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሚዩኒኬሽን): የምስራቅ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ የ2014 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2015 በጀት አመት የንቅናቄና የእውቅና ፕሮግራም እንደቀጠለ ነወ።

በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሐም አያሌው ትምህርት ዜጎችን ለመቅረፅና የሃገር እድገት ለማፋጠን ዋነኛው ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን ተናግረው ቀጣዩን ትውልድ የምናንፅበት ከመሆኑም ባሻገር ተተኪውን ትውልድ በዕውቀት ፣ በግብረ ገብነት እና በአጠቃላይ በአስተሣሠብ አንፆ ለማውጣት የማይተካ ሚና አለው ብለዋል።

ትምህርት አንዱ የስነ ምግባር ማነጫ ዋና መሣሪያ ቢሆንም አሁን አሁን ይህን አቅሙን አጥቷል "ከእኔ" ወጥቶ "ለእኛ" ብሎ ለሀገር የሚጨነቅ ትውልድ መፍጠር ተስኖን ቆይተናል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው የትምህርት ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግና በአምሮው የበለፀገ ትውልድ ለመፍጠር በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

የጎጃም ማህበረሰብ ከልጆቹ የሚሰስትለት አንድም ነገር የለም ያሉት አቶ አብረሐም አያሌው የዞኑን ማህበረሰብ በማሳተፍ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሳደግ ፣ግብዓት ለማሟላትና የተማረ ምዝገባ ስራን ውጤታማ ለማድረግ በቅንጅት እንደሚሰራ ጨምረው ተናግረዋል ።

ዋና አስተዳዳሪው በመጨረሻም ትምህርት ቤቶች ሳይንሳዊ እውቀት የሚገበይባቸው ፣የሀገር ፍቅር የሚያድግባቸው ፣እርስ በእርስ መተሣሠብ የሚጎለብትባቸው እንዲሆኑ ከመቸውም ጊዜ በላይ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አክለው ገልፀዋል።

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኀላፊ አቶ ሙላው አበበ እንደተናገሩት በአሁኑ ሰዓት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከተ የመጣውን አሳፋሪ የኩረጃ ተግባር ለማስወገድ ሁሉም አካል ርብርብ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።

በተጠናቀቀው 2014 በጀት አመት በትምህርት ተቋሙ የተሻሉ ተግባራት የተፈፀሙ ቢሆንም በትምህርት ስርዓቱ ላይ ከፍተኛ ስብራትና የትምህርት ጥራት ችግር በመኖሩ መምህራን፣ ወላጆች፣ ተማሪዎችና አጋር አካላት በጋራ ሊሰሩ ይገባል ያሉት አቶ መላው በ2015በጀት አመት ችግሮች እንዳይደገሙ ከወዲሁ በተማሪዎች ምዝገባ፣ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ትግበራና የመጽሐፍ ስርጭት እንዲሁም ቀጣይ በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ትኩረት
ተሰጥቶ ሊሰራበት ይገባል ብለዋል።

የምስራቅ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ ኀላፊ አቶ ጌታሁን ፈንቴ በበኩላቸው በተያዘው 2015 በጀት አመት የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል፣ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሳደግና የግብዓት ችግርን ለመቅረፍ ከማህበሰቡና ከሚመለከታቸው አጋርና ባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በመጭው መስከረም 2015 አገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል የሚወስዱ ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ከ3.2 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ በመመደብ የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት ተማሪዎችን ለፈተና ዝግጁ የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

በ2014 በጀት አመት የነበሩ ችግሮችን በመለየት በ2015 የትምህርት ዘመን እንዳይደገሙ በማድረግ ዘርፉን ስኬታማ በማድረግ መምሪያውን በክልል ደረጃ ቀዳሚ ለማድረግ እንደሚሰራ አቶ ጌተሁን ፈንቴ ተናግረዋል።
7.9K views10:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 10:44:15 የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1443ኛው የኢድ አል አድሃ /ዓረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በአሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የአንድነት በአል እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቱን ይገልፃል።
መልካም የዓረፋ በዓል!
8.9K views07:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 15:10:14
11.0K views12:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 12:37:43
10.5K views09:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 15:56:07
ከ359ሸህ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች ከነገ ሰኔ 28/ 2014 ዓ.ም ጀምሮ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይወስዳሉ
==================================
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙላው አበበ የ2014 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫው ከ359ሸህ በላይ የሚሆኑ በመደበኛ፣ በግልና በማታ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ከነገ ሰኔ 28/ 2014 ዓ.ም ጀምሮ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እንደሚወስዱ አስታውቀዋል፡፡
ከተፈታኞች መካከል ከ1 መቶ 93 ሽህ በላይ /53.8 %/ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው፡፡ ፈተናው በ5 ሽህ 395 ትምህርት ቤቶች እንደሚሰጥና ለዚህም አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መደረጉን አቶ ሙላው አበበ ገልጸዋል፡፡
በፈተናው 10 ሽህ ፈታኞችና ከ9 ሽህ በላይ የሚሆኑ የፈተና ተቆጣጣሪዎች ይሳተፋሉ፡፡
ፈተናውን ሰላማዊና የተረጋጋ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ተፈታኝ ተማሪዎች፣ ፈታኝ መምህራን ወላጆችና የጸጥታ አካላት የተጣለባቸውን ሃላፊነት እንዲወጡ ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የ2014 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 28 እስከ 30/ 2014 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጫኑ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን!!
10.8K views12:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 12:53:27
9.1K views09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 12:52:54 እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በሁለት 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች 1ሚሊየን ብር ወጪ የተደረገባቸው ዲጂታል ላይበራሪ አደራጀ።
==============================
በእንጅባራ ከተማ ለሚገኙ ለዛግዌ እና ለእንጅባራ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ነው ዩኒቨርስቲው ዲጂታል ላይብረሪ በማደራጀት አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር ያደረገው።
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለሀገር ተረካቢ ለሆኑ ተማሪዎች የእውቀት አድማሳቸው እንዲበለጽግ እና ከዘመኑ ቴክኖሎጂዎች ጋር በማስተዋወቅ ውጤታማ እንዲሆኑ በት/ቤቶች ላይ እየሰራ ይገኛል።ለዚህም ማሳያ ደግሞ ለሁለት ደረጃ ት/ቤቶች ዘመኑን የዋጀ በ1ሚለዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው ዲጂታል ላይብረሪ ተጠቃሽ ነው።
የዩኒቨርስቲው ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ክንዴ ብርሃን እንደተናገሩት እንደ ሀገር የገጠመንን የትምህርት ጥራት ችግር ለመፍታት ዩኒቨረሲቲው በማህበረሰብ ከአገልግሎት ዘርፍ ለአካባቢው ማህበረሰብ ት/ቤቶች የሚጠበቅበትን ለመወጣት እይሰራ ይገኛል። በዚህም በሁለት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለእያንዳንዳቸው 500ሽ ብር ወጪ በማድረግ የS.R.Eዲጂታል ቤተመጽሐፍት በማደራጀት አገልግሎት ላይ እንዲውል አድርጓል።
ዲጂታል ላይበራሪው ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የሚያስችል 60ሽ የሚሆኑ ቪዲዬ እና ድምጽ፣ ከ9-12 ክፍል ያለው የፕላዝማ ቪዲዮ መረጃዎች፣ የቤተሙከራ ስራዎች የያዘ እንዲሁም ከ21 በላይ የውጭ ቋንቋዎች የሚጠቀም ማሽን እንደሆነ ገልጸዋል። አያይዘውም ዲጅታል ላይበራሪው በቂ የሆነ ሀብት የያዘ እና በአጠቃላይ ለሁለተኛ ደረጃ ስርዓተ -ትምህርት ግብዓት የሚውሉ አጋጅ ቤተመጽሀፍትን የያዘ ማሽን ነው ብለዋል።
በማሽኑ አካባቢ ማነኛውም ሰው በ30 ሜትር ራዲየስ ውስጥ ሆኖ አገልግሎት የሚያገኝበት እንደሆነም ተገልጿል ።
የአዊ ብሄ/አስ ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ሙሉቀን መኮንን እንደገለጹት ዩኒቨርስቲው በትምህርት ዘርፍ በርካታ የግብዓት እጥረቶች እያሟላ ይገኛል ።
ከቴክኖሎጁ ጋር በማስተዋወቅ እና የቤተሙከራ ትምህርቶችን በተግባር እንዲማሩ የሚያደርገው ድጋፍ የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ የሚወሉ ናቸው ብለዋል።
ተማሪዎች በሠጡት አስተያየት የነበረባቸውን የመጽሐፍት ችግር እንደፈታላቸውና በውጤታቸውም ላይ መሻሻል መታየቱን ተናግረዋል።
መረጃው የአዊ ኮሙኒኬሽን ነው
9.4K views09:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 18:11:52
10.4K views15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ