Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 127.33K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 484

2021-02-09 18:32:40
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ቡሩንዲ ገቡ!

የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ዛሬ ቡሩንዲ መግባታቸው ተገልጿል፡፡ ፕሬዝዳንቷ ቡጁምቡራ እንደደረሱ በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት የቀድሞው የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ፒዬሬ ንኩሩንዚዛ የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት የቀድሞው የቡሩንዲ ፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ አዲስ አበባ በሚገኘው የቡሩንዲ ኤምባሲ በመገኘትም የአበባ ጉንጉን ማስቀመጣቸው ይታወሳል፡፡

ንኩሩንዚዛ በ55 ዓመታቸው በድንገተኛ የልብ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወሳል፡፡ በፈረንጆቹ 1963 የተወለዱት ንኩሩንዚዛ እ.ኤ.አ ከ2005 ጀምሮ ህይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ቡሩንዲን መርተዋል።ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በሁለቱ ሀገረታት እና በቀጣናዊ ጉዳዮች ከቡሩንዲ መሪዎች ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
10.1K viewsedited  15:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 17:18:41
በኢትዮጵያ ወደ ሰሜንና ሰሜን ምዕራብ አንዳንድ ከተሞች ተቋርጦ የነበረው የአየር በረራ ተጀመረ!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተፈጥሮ ሰሞኑን ተፈጥሮ ነበር ባለው አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ ምክንያት ተቋርጦ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ አብዛኞቹ ከተሞች የአየር በረራ ማቋረጡን አስታውቆ ነበር።ነገር ግን ዛሬ እንደተሰማው ከአዲስ አበባ ባህርዳር፣ ጎንደር እና ላሊበላ የአየር በረራ ትናንት መጀመሩን አየር መንገዱና ተሳፋሪዎች ገልፀዋል፡፡

አንድ የአየር መንገዱ ባልደረባ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ሰሞኑን ተፈጥሮ በነበረው ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ ምክንያት ከአርብ ከሰኣት ጀምሮ ከአዲስ አበባ ባህር ዳር፣ ጎንደርና ላሊበላ ይደረጉ የነበሩ በረራዎች ተቋርጠው ቆይተዋል፡፡ይሁን እንጂ የአየር ሁኔታው የተሰተካከለ በመሆኑ እሁድ ወደ ላሊበላ በረራ መጀመሩን፣ ባህርዳርና ጎንደር ደግሞ ትናንት ሰኞ የበረራ አገልግሎት መቀጠሉን ገልፀዋል፡፡አንድ ከአዲስ አበባ ወደ ባህር ዳር ለመምጣት ሲጠባበቁ የነበሩ የአየር መንገዱ ደንበኛ ትናንት በረራ መጀመሩ ከአየር መንገዱ ተነግሯቸው በነበረው የበረራ መስተጓጎል በተፈጠረ ወረፋ በረራቸው ተዛውሮ ዛሬ ባሕር ዳር መግባታቸውን ለዶይቼ ቬለ በስልክ ተናግረዋል፡፡

የዶይቼ ቬለ ዘጋቢ እንዳረጋገጠውም ከትናንትና ጀምሮ በባህር ዳር አውሮፕላን ማረፊያ አውሮፕላኖች እየተነሱ ሲያርፉ ነበር፡፡ሆኖም ያለው የአየር ሁኔታ ሞቃታማነቱን እየጨመረ ስለሚሄድ በቅርቡ ተመሳሳይ የአየር ሁኔታ ለውጥ ሊኖር እንደሚችል በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ አጀንሲ የባህር ዳር ቅርንጫፍ የትንበያና ትንተና ቡድን አስተባባሪ አቶ ጥላሁን ውቤ የትንበያ ሪፖርቶችን ጠቅሰው ተናግረዋል፡፡

[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
16.2K views14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 16:41:14
የዓለም ጤና ድርጅት ኮቪድ የመጣው ከውሃን ቤተ ሙከራ ሳይሆን ከእንስሳት መሆኑን አስታወቀ!

የዓለም ጤና ድርጅት የኮሮና ቫይረስ መነሻ ከውሃን ቤተ ሙከራ ሳይሆን ከእንስሳት መሆኑን በጥናቱ አረጋገጠ፡፡የድርጅቱ ልዑክ ቻይና በመገኘት የኮሮና ቫይረስን መነሻ ሲያጠና መቆየቱ ይታወቃል፡፡የልዑክ ቡድኑ መሪ ፒተር ቤን ኢምባረክ መነሻውን ለማወቅ ተጨማሪ ስራዎች መሰራት እንዳለባቸውም ገልጸዋል፡፡ጥናቱን የድርጅቱ ልዑክ እና ቻይና የጤና ኮሚሽን በጋራ ማጥናታቸው ነው የተነገረው፡፡ውሃን በቻይና ምዕራባዊ ሁቤ አውራጃ የምትገኘ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ኮሮና ቫይረስ የተገኘባት ከተማ መሆኗ ይታወሳል፡፡ባለሙያዎች ወረርሽኙ ወደ ሰዎች ከመሰራጨቱ በፊት ከእንስሳ እንደመጣ ቢያምኑም እንዴት ሊከሰት እንደቻለ እርግጠኞች አይደሉም ተብሏል፡፡

(ኤፍ ቢ ሲ)
@YeneTube @FikerAssefa
15.9K views13:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 13:17:41 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሰራተኞቹ ጥቅማ ጥቅም የሚያስገኝ ስምምነት ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ማህበር ጋር ተስማማ!

ስምምነቱ የባንክ ብድር አገልግሎት በማመቻቸት ሰራተኞች ጥቅማ ጥቅም ያገኙ ዘንድ የሚያስችል ነው።አየር መንገዱ ወደ 17ሺ የሚጠጉ ሰራተኞች ያሉት ሲሆን ፤ ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የነበረው ስምምነት ለሁሉም ሰራተኞች ተደራሽ አልነበረም ተብሏል።በመሆኑም የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ጋር የተደረገው ስምምነት ሁሉም ሰራተኞችን ተጠቃሚ ሊያደርግ ታሳቢ ያደረገ ነው ሲሉ የአየር መንገዱ ቀዳማዊ መሰረታዊ ሰራተኛ ማህበር ፕሬዚዳንት ኢ/ር ተሊላ ደሬሳ ተናግረዋል።

ስምምነቱ አብዛኛው ሰራተኛ በተሻለ መልኩ የቤት፣ተሽከርካሪ እና ሌሎችም ጥቅማ ጥቅሞችን እንዲያገኙ ያስችላል።የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም ይህ ስምምነት እውን ይሆን ዘንድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውንም በመድረኩ ገልፀዋል። ኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንኩም ይህንኑ ሲቀርብላቸው ከሌሎች ባንኮች ይልቅ ሃሳቡን በመቀበል ስምምነቱ እውን እንዲሆን በማስቻሉ ለባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ደርቤ አስፋው ምስጋና ቀርቧል።

በዚህ በኮቪድ 19ወረርሽኙ በቅት ታላላቅ አየር መንገዶች ሰራተኞቻቸውን ሲያባርሩ ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግን 1,600 ሰራተኞች ቋሚ እንዲሆኑ ማደረጉንም አንስተዋል።የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ በዚህ በአስቸጋሪ ወቅት ምንም እንኳ የአየር መንገድ ኢንዱስትሪ ቢጎዳም ፤ ያለምንም ድጋፍ አሁንም ስራውን በተገቢው መልኩ ማስቀጠሉን አንስተዋል።ለውጡ እየመጣ የሚገኘው በሰራተኞች ልፋት መሆኑን በመግለፅም ፤ አየር መንገዱ 1,200 ቤቶች ከዚህ ቀደም ለሰራተኛው ሰርቶ አስረክቧል ብለዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
17.0K views10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 12:54:36
አዲስ አበባ ከተማ የ2021 የዓለም አቀፍ ራእይ ለዜሮ የመኪና አደጋ ተጋላጭነት ሽልማት አሸናፊ መሆኗ ተገለፀ፡፡

የአሜሪካው ብሄራዊ ማእከል ለምቹ መንገድ FIA ከተባለ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን ተካሂዷል በተባለው ምርጫ አዲስ አበባ የ2021 የዓለም አቀፍ ራእይ ለዜሮ የመኪና አደጋ ተጋላጭነት ለወጣቶች አመራር(International vision zero for youth leadership award) ሽልማት አሸናፊ ሆናለች፡፡

ሽልማቱ የተበረከተው ኢትዮጲያ ለወጣቶች እና ተማሪዎች የእግርኛ መንገድ አጠቃቀም ፖሊሲ በማውጣት እና በመተግበር ላሳየችው ተምሳሌት ፤ በትምህርት ቤቶች አካባቢ ፍጥነትን ቀንሶ በማሽከርከር እና የትራፊክ አደጋ መቀነሻ ዘላቂ መንገዶችን በመተግበር ላስመዘገበችው ለውጥ ነው ተብሏል ፡፡

በተጨማሪም በትምህርት ቤቶች አካባቢ የእግረኛ መጠቀሚያ መሰረተ ልማቶችን በማስፋፋት እና መኪና አልባ(CAR-FREE ROAD) መንገዶች መርሐግብር በወር አንድ ቀን በመተግበር የሰዎችን አሰተሳሰብ በመቀየር የመኪና መንገዶች ለወጣቶች የመዝናኛ ቦታዎች እንዲሆኑ በማድረጓ ነው ሲል የአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪ ጽፅህፈት ቤት ገልጿል።

@YeneTube @FikerAssefa
15.5K views09:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 12:53:04
ሠመራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ያሠለጠናቸውን ከ1ሺህ 700 በላይ ተማሪዎችን ዛሬ ማስመረቁን ከዩኒቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

@YeneTube @FikerAssefa
13.8K views09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 12:50:55
በመጪው ሚያዚያ ወር መጀመሪያ 9 ሚሊየን የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ክትባት ወደ ሃገር ውስጥ እንደሚገባ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ::

የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ኢትዮጵያ አባል በሆነችበት የአለም አቀፉ የኮቫክስ የጋራ ትስስር በኩል የሚገባውን ክትባት አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል::

ክትባቱ በተያዘው አመት ሚያዝያ መጀመሪያ እንደሚገባ የገለፁት ሚኒስትሯ ክትባቱም በተለይም ለበሽታው ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በቅድሚያ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል::

ይሄንን ሃላፊነት የሚወጣ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱንም ገልፀዋል::ከክትባቱ ጎን ለጎን ህብረተሰቡ አሁንም ቢሆን መከላከል ላይ ትኩረት እንዲያደርግም ሚኒስትሯ ጥሪ አቅርበዋል::

@YeneTube @FikerAssefa
13.5K views09:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 12:49:37 ኦነግ በምርጫው ለመሳተፍ እየተፍጨርጨርኩ ነው አለ::

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ በውስጣዊ የፖርቲ ቀውስ የተነሳ በ6 ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ለመሳተፍ አጣብቂኝ ውስጥ መውደቁን ለኢትዮ ኤፍ ኤም አሳውቋል፡፡የፖርቲው ቃላቀባይ አቶ ቀጀላ መርዳሳ ምርጫ ቦርድ ፖርቲው የገጠመውን ችግር ለመቅረፍ አሰቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን እንዲያደርግ ጥብቅ ማሳሰቢያ ቢሰጥም በተቀዳሚ ሊቀመንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ እንቢተኛነት ማድረግ እንዳልቻለና እና ልመና ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ውዝግቡ ከተፈጠረ ወዲህም ምርጫ ቦርድ ጋር በስመ ሊቀመንበርነት የግንባሩ ተወካይ ናቸው በሚል ግንኙነት ስላላቸው ፈጽሞ የጋራ ውሳኔና መመሪያ እየሰጡም ፤እየተቀበልንም አይደለም ነው የሚሉት አቶ ቀጀላ፡፡እኛ ምርጫ ቦርድ ችግሮን ተገንዝቦ በአፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጠን እና ወደ ምርጫ ዝግጅቱ እንድንገባ እየጠየቅን ነው ይላሉ፡፡

አሊያም ግን ምርጫ ውስጥ የማይሳተፍ ፖርቲ ጥቅሙ ምን ሊሆን ይችላል ሲሉም ይጠይቃሉ፡፡በዚህ አይነት ከሄድንም የእርሳቸው ስብስብ በምርጫው ለመሳተፍ አይችልም ምክንያቱም ህጋዊ አይደለም ባይ ናቸው ፡፡

የእኛ ጥያቄ ምርጫ ቦርድ ከእርሳቸው ጋር የሚያደርገውን ግንኙንት እንዲያጤነውና መፍትሔ እንዲሰጠን ነው ምክንያቱም ይህ ነገር አግባብነትም ሆነ ፍትሐዊ አይደለም ነው የሚሉት አቶ ቀጀላ፡፡

ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሄድ የግድ መሆኑን የሚያነሱት አቶ ቀጀላ አሁን ድርጅታዊ ቀውስ ውስጥ ስላለን ወደ ምርጫው መግባት አንችልም ከባድ ብለው፡፡ችግሮ እስኪፈታ ምርጫ ቦርድ በልዩ ሆኔታ ቀናትን ገፋ እንዲያደርግልን እንጠይቃለን፡፡ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ምርጫውን መካፈል ከባድ ሊሆን እንደሚችል ነው ያነሱት፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
9.7K views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 10:16:05
የዱራሜ-ዳንቦያ-አንጋጫ-አመቾ ዋቶ-ሃላባ 65 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ይጀመራል።

በተመሳሳይም የሐዌላ-ቱላ ወተራሬሳ-የዩ እና ወንቻ 85 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት ይጀመራል።65 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር ርዝመት ላለው ዱራሜ-ዳንቦያ-አንጋጫ- አመቾ ዋቶ-ሃላባ የመንገድ ፕሮጀክት 1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በጀት ተይዞለታል።ለሐዌላ-ቱላ ወተራሬሳ-የዩ-ወንቻ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት ደግሞ 1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ተበጅቶለታል።የመንገዶቹ ግንባታ ወጪ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው።

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን የመንገድ ግንባታውን ሲከውን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ኮርፖሬሽን ደግሞ በአማካሪነት ይሠራል።

የመንገዶቹ ግንባታው ሶስት ዓመት የሚወስድ ሲሆን እስከ ታህሳስ 2016 ዓ.ም ድረስ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።ፕሮጀክቱ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት ይገኛል።በፕሮጀክቶቹ ማስጀመሪያ መርሃግብር ለመገኘት የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በቦታው ተገኝተዋል።የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች፣ የሲዳማና የኦሮሚያ ክልሎችን በማስተሳሰር የጎላ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ፋይዳ ይኖራቸዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
10.4K views07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 10:15:07
ለጓደኛ፣ ለወዳጅ ዘመድ፣ ለሙሽሮች እና ለተመራቂዎች ለየት ያለ ስጦታ መስጠት ይፈልጋሉ?
#join

@giftsoflovee
@giftsoflovee

+251914839754
+251936871620
#ኣድራሻችን፡ 4 ኪሎ: ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ
7.9K views07:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ