Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ አበባ ከተማ የ2021 የዓለም አቀፍ ራእይ ለዜሮ የመኪና አደጋ ተጋላጭነት ሽልማት አሸናፊ መ | YeneTube

አዲስ አበባ ከተማ የ2021 የዓለም አቀፍ ራእይ ለዜሮ የመኪና አደጋ ተጋላጭነት ሽልማት አሸናፊ መሆኗ ተገለፀ፡፡

የአሜሪካው ብሄራዊ ማእከል ለምቹ መንገድ FIA ከተባለ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን ተካሂዷል በተባለው ምርጫ አዲስ አበባ የ2021 የዓለም አቀፍ ራእይ ለዜሮ የመኪና አደጋ ተጋላጭነት ለወጣቶች አመራር(International vision zero for youth leadership award) ሽልማት አሸናፊ ሆናለች፡፡

ሽልማቱ የተበረከተው ኢትዮጲያ ለወጣቶች እና ተማሪዎች የእግርኛ መንገድ አጠቃቀም ፖሊሲ በማውጣት እና በመተግበር ላሳየችው ተምሳሌት ፤ በትምህርት ቤቶች አካባቢ ፍጥነትን ቀንሶ በማሽከርከር እና የትራፊክ አደጋ መቀነሻ ዘላቂ መንገዶችን በመተግበር ላስመዘገበችው ለውጥ ነው ተብሏል ፡፡

በተጨማሪም በትምህርት ቤቶች አካባቢ የእግረኛ መጠቀሚያ መሰረተ ልማቶችን በማስፋፋት እና መኪና አልባ(CAR-FREE ROAD) መንገዶች መርሐግብር በወር አንድ ቀን በመተግበር የሰዎችን አሰተሳሰብ በመቀየር የመኪና መንገዶች ለወጣቶች የመዝናኛ ቦታዎች እንዲሆኑ በማድረጓ ነው ሲል የአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪ ጽፅህፈት ቤት ገልጿል።

@YeneTube @FikerAssefa