Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 127.33K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 485

2021-02-09 10:15:07
ሁሉንም ሰብስቦ በአንድ ላይ የያዘ የግብይት ድረገፅ

@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com

0953707070
4.6K views07:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 22:47:21 60 ከፍተኛ ውጤት ያላቸው ተማሪዎች አመራርነት እና አገልጋይነትን በተግባር ሊሰለጥኑ መሆኑ ተገለጸ!

ከሁሉም ክልሎች በከፍተኛ ውጤት ያጠናቀቁ 60 ተማሪዎች አመራርነትን እና አገልጋይነትን በተለያዩ ተቋማት ተሰማርተው በተግባር እንደሚሰለጥኑ የሴቶች፣ ሕፃናት እና ወጣቶች ጉዳይ ሚኒስትር ወ/ሮ ፊልሰን አብዱላሂ ገለጹ።

ለዚህም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ወጣቶቹን ከሚያሰለጥነው 'ሴንተር ፎር አፍሪካን ሊደርሺፕ' ከተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር ተፈራርሟል ብለዋል።

ወጣቶቹ 6 ሺህ ብር ወርሃዊ ደመወዝ ይከፈላቸዋል ተብሏል።

ፕሮግራሙ ለተከታታይ አምስት ዓመታት የሚቆይ ሲሆን በየዓመቱ የወጣቶቹ ቁጥር እየጨመረ እንደሚሄድ ወ/ሮ ፊልሰን ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል።

Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
16.6K views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 22:46:57 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተመለመሉ የምርጫ ክልል አስፈፃሚዎችን በተመለከተ ፓርቲዎች ባቀረቡት ቅሬታ ላይ ውሳኔ ሰጠ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ክልል ደረጃ ምርጫ ለማስፈጸም የመለመላቸውን የምርጫ አስፈጻሚዎች ዝርዝር ለፖለቲካ ፓርቲዎች በሁለት ዙር በማቅረብ አስተያየታቸውን እንዲሰጡበት በጠየቀው መሠረት ከ10 ፓርቲዎች የተሰጡ አስተያየቶችን መርምሮ ውሳኔዎችን ሰጥቷል።

ከአስሩ መካከል ሦስት ፓርቲዎች ዝርዝር አስተያየት ያቀረቡ መሆኑን ነው ቦርዱ ያስታወቀው።

“የምርጫ አስፈፃሚው ገለልተኛ አይደለም” እና “የሌላ ፓርቲ አባል ነው” በማለት የቀረቡ አቤቱታዎች መኖራቸውን የገለጸው ምርጫ ቦርዱ፣ ያለምንም ማስረጃ የቀረቡትን አቤቱታዎች እንዳልተቀበለው አስታውቋል።

ነገር ግን የፓርቲ አባልነት የከፈሉ ማስረጃ የቀረበባቸውን አስፈጻሚ ከአስፈጻሚነት መሠረዙን በምሳሌነት አንስቷል።

“የምርጫ አስፈፃሚው የራሴ አባል ነው” በማለት ማረጋገጫ ያቀረበ ፓርቲ በአቤቱታው መሠረት አባላቶቼ ናቸው ያሉት ከአስፈጻሚነት እንዲሰረዙ ተደርጓል ብሏል።

“በዞናችን ላሉት ምርጫ ክልሎች የአስፈፃሚዎች ዝርዝር አልተላከም” በሚል ላቀረቡት ቅሬታ ደግሞ በሦስተኛው ዙር እንደሚላክ እንዲገለጽላቸው መወሰኑን ገልጿል።

“የማይታወቁ አስፈፃሚዎች ናቸው” በሚል ለቀረበው ቅሬታ የምርጫ ቦርድ የኦፕሬሽን ክፍል አድራሻቸውን አጣርቶ በሦስተኛው ዙር እንዲልክ እንዲደረግ ተወስኗል ነው ያለው።

“የሥራ ፈጠራ ኮሚሽን እና ከማዕከላዊ ስታስቲክስ ባለሥልጣን ከመጡ ዝርዝሮች ውስጥ ምልመላው መከናወን አልነበረበትም” የሚል አቤቱታ የቀረበ መሆኑን እና ተቋማቱ የመንግሥት ተቋማት በመሆናቸው ብቻ የሚመለመሉ ሰዎች ዝርዝር መካተት የለበትም የሚለውን ውሳኔ ቦርዱ እንዳልተቀበለው አሳውቋል።

@YeneTube @FikerAssefa
16.9K views19:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 20:39:28
ለመጭው ሀገር ዐቀፍ ምርጫ የምርጫ ክልል እና የዞን ማስተባበሪያ ቢሮዎችን አዘጋጅተው ለቦርዱ ባላስረከቡ የክልል መስተዳድሮች በተቀመጠው የጊዜ መርሃ ግብር የዕጩዎች ምዝገባ እንደማያካሂድ ዛሬ ለመገናኛ ብዙኀን በላከው መግለጫ አስታውቋል። እስካሁን የክልል እና ዞን የምርጫ ቢሮዎችን ባላሳወቁት አማራ፣ አፋር፣ ሱማሌ፣ ደቡብ እና ሲዳማ ክልሎች፣ የዕጩዎች ምዝገባ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ሥልጠና እና የምርጫ ቁሳቁሶች ስርጭት ማከናወን አልቻልኩም- ብሏል ቦርዱ። በተጠቀሱት ክልሎች ሌላ ጊዜ የዕጩዎች ምዝገባ እንዲደረግ፣ እስከ የካቲት 5 ቢሮዎችን እንዲያሳውቁም አሳስቧል።

@YeneTube @FikerAssefa
16.3K views17:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 20:32:43 የኖርዌይ ስደተኞች ካውንስል በትግራይ ክልል ለስደተኞች የገነባኋቸው ሕንጻዎች ወድመውብኛል ወይም ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ሲል ዛሬ ባሰራጨው መግለጫ አውግዟል።

በሒጻጽ እና ሽመልባ የኤርትራዊያን ስደተኛ ጣቢያዎች፣ በቅርብ ሳምንታት አንድ ትምህርት ቤት እና ክሊኒክም እንደወደሙ የድርጅቱ ዋና ሃላፊ ጃን ኢግላንድ ገልጠዋል። በተቋማቱ እና በዕርዳታ አቅርቦቶች ላይ የደረሰውን ጉዳት መንግሥት እና ለጋሽ ሀገራት እንዲያጣሩ እና ጥፋተኞችን ተጠያቂ እንዲያደርጉም ድርጅቱ ጠይቋል። ድርጅቱ በምንጭነት የተጠቀመው ግን ተቀማጭነቱን ለንደን ያደረገ ዲ.ኤክስ ኦፕን ኔትወርክ የተባለ ድርጅት ያሰራጫቸውን የሳተላይት ምስሎች ነው። በሌላ በኩል የተመድ ዐለም ምግብ ፕሮግራም በመላው ትግራይ ክልል ለረድዔት ሠራተኞች ተደራሽ እንዲሆን እና የዕርዳታ አቅርቦቱም እንዲያድግ ከመንግሥት ጋር ስምምነት ላይ እንደደረሰ የድርጅቱ ዋና ሃላፊ ዴቪድ ቢዝሊ በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል። አስገዳጅ ሁኔታ ሲያጋጥም የዕርዳታ ማጓጓዣዎች በወታደሮች እንዲታጀቡ ስምምነቱ ይፈቅዳል። መንግሥትም ወደ ክልሉ ለመግባት ፍቃድ ለሚጠይቁ የረድዔት ሠራተኞች አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ተስማምቷል።

[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
12.6K views17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 20:09:29
17 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ!

የምዕራብ ዞን የኦሮሚያ ልዩ ፖሊስ 17 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ መውሰዱንና ሶስት ታጣቂዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ፡፡ከታጣቂዎቹ በተጨማሪም የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች መያዙን ከኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
14.8K views17:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 20:05:00
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አዲሱን የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር “እንኳን ደስ ያለዎት” አሉ!

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የደቡብ አፍሪካውን ፕሬዘዳንት ሲሪል ራማፎዛን በመተካት የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር የሆኑትን የዲአር.ኮንጎ ፕሬዚዳንት ፊሊክስ ቲሼኬዲን በአዲስ አበባ አግኝተዋቸዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዐቢይ ፕሬዚዳንት ፊሊክስ ቲሼኬዲ ሊቀመንበር ሆነው በመመረጣቸው “እንኳን ደስ ያለዎት፤ መልካም የሥራ ዘመን ይሁንልዎ” ብለዋቸዋል።

ሊቀመንበሩ የተጣለባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ኢትዮጵያ እንደምትደግፋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ገልጸዋል፡፡ ዲአር ኮንጎ የህብረቱ ሊቀመንር በመሆኗ በህዳሴው ግድብ ድርድር ላይ የደቡብ አፍሪካን የማደራደር ሚና ትቀበላለች፡፡የኢትዮጵያ ውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ደ/ር ኢ/ር ስለሺ ዲአር.ኮንጎ በግድቡ ድርድር ላይ የሚኖራት ሚና ሚዛናዊ እንደሚሆን ከሰሞኑ መሰጡት መግለጫ ተናግረዋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
15.4K views17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 19:59:45
በሰሜን ሪጅን የቴሌኮም መሠረተ ልማት ጥገና እና አገልግሎትን የተመለከተ ወቅታዊ መረጃ!

@YeneTube @FikerAssefa
15.2K views16:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 16:10:20
የጉምሩክ ኮሚሽን ከመቀሌ ቅርንጫፍ በኹለት ወራት ተኩል 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ማጣቱን አስታወቀ!

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በትግራይ ክልል ጥቅምት 24/2013 በተከሰተው ችግር ምክንያት ላለፉት ኹለት ወራት ተኩል ከመቀሌ ጉምሩክ ቅርንጫፍ መሰብሰብ የነበረበትን አንድ ነጥብ ኹለት ቢሊዮን ብር መሰብሰብ አለመቻሉን ለአዲስ ማለዳ አስታውቋል።

@YeneTube @FikerAssefa
10.3K views13:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 15:27:17 የምርጫ ሥልጠና ያልወሰዱ ፖሊሶች በምርጫ ወቅት ሕግ ለማስከበር አይሰማሩም ተባለ!

በምርጫ ወቅት ሰላም ለማስከበር በ55,220 የምርጫ ጣቢያዎች የሚሰማሩ የፀጥታ አካላት ተልዕኳቸውን ሳይረዱና አስፈላጊውን ሥልጠና ሳያገኙ እንደማይመደቡ፣ የፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር አስታወቁ፡፡

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል ዘለዓለም መንግሥቴ ሐሙስ ጥር 27 ቀን 2013 ዓ.ም. በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ‹‹የኮሙዩኒኬሽን መንገዶቻችን ለምርጫ ሰላምና ደኅንነት›› በሚል ርዕስ በተካሄደ ውይይት ላይ፣ ‹‹ምርጫ በመንግሥት ቅድሚያ የሚያገኝ ተግባር ነው፤›› ብለዋል፡፡ ለምርጫው ሰላምና ደኅንነት መጠበቅ የፀጥታ ኃይሉ ሚናውን ለይቶ ይሰማራ ዘንድ፣ መመርያዎችና የሥልጠና ማኑዋሎች ተዘጋጅተዋል ሲሉ አስረድተዋል፡፡

በእነዚህ መመርያዎችና ማኑዋሎች መሠረት ሥልጠናዎች እየተሰጡ እንደሚገኙ፣ ሥልጠናዎችን ያላለፈና ሚናውን ያልለየ አንድም ፖሊስ ሥምሪት እንደማይሰጠው አስታውቀዋል፡፡

የምርጫ ወቅት ደኅንነትን የሚከታተልና የሚመራ ኮሚቴ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መቋቋሙንና በጠቅላይ ሚኒስትሩ የደኅንነት አማካሪ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው እንደሚመራ ያስታወቁት ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራሉ፣ ‹‹በዚህ ኮሚቴ ውስጥ የአገር መከላከያ ሠራዊት፣ የክልል ፖሊስ ኮሚሽነሮችና የፌዴራል ፖሊስ በአባልነት ይገኛሉ፤›› ብለዋል፡፡

[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
15.8K views12:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ