Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 127.33K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 486

2021-02-08 15:04:05
ዛሬ በሑመራ ከተማ በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መደበኛ የመማር ማስተማር መጀመሩን የከተማዋ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ፡፡

በሕግ ማስከበር ሂደቱ ከተማዋ ነፃ ከወጣች በኋላ ማኅበረሰቡ ልጆቹን ወደ ትምህርት እንዲመለሱ ተደጋጋሚ ጥያቄ ማንሳታቸውን የጊዜያዊ አስተዳደሩ ሥራ አስፈፃሚ አባል በሪሁን እያሱ ተናግረዋል፡፡ይሕንን ተከትሎም በከተማዋ ትምህርት ለማስጀመር ጊዜያዊ አስተዳደሩ የተለያዩ ተግባራት ማከናወኑን አስታውቀዋል፡፡

አቶ በሪሁን እንዳሉት በትምህርት ቤቶች የነበሩ ችግሮችን በመለዬት ቁሳቁስ እንዲሟሉ ተደርጓል፤ መምሕራንን በማሟላትም ደመወዝ እስከመክፈል ተደርሷል፡፡ በመሆኑም ዛሬ በአምስት ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደቱ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡

የአማራ ክልል መንግሥትም ባለሙያዎችን በመመደብ፣ መምሕራንን በማሟላትና ማኅበረሰቡን በማወያዬት ትምህርት ቤቶችን መልሶ በማደራጀት ሥራው ስኬታማ እንዲሆን ደግፏል ብለዋል፡፡ አሁንም ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ነው አቶ በሪሁን ያስታወቁት፡፡

Via Walta
@YeneTube @FikerAssefa
14.8K views12:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 14:37:47
የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ልዑክ ወደ ትግራይ ክልል አቀና!

የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶችን፣ የሀገር ሽማግሌዎችንና መማክርትን ያካተተ ልዑክ በወቅታዊ ሁኔታ ላይ ለመወያየትና ድጋፍ ለማድረግ ወደ ትግራይ ክልል ማቅናቱን የጉባኤው ዋና ጸሃፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ገለጹ።

ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶችን፣ የሀገር ሽማግሌዎች መማክርትን ያካተተ ልዑክ ወደ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ማቅናቱ ነው የተጠቀሰው።

ልዑኩ በሚኖረው ቆይታ በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከህብረተሰቡና ከባለድርሻ አካላት ጋር እንደሚወያይም ነው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊው ለኢዜአ ገልጸዋል።

ልዑኩ በሚኖረው ቆይታ በተካሄደው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ወቅት ያጋጠሙ ችግሮችንና፣ በተለይም በቤተ እምነቶች ላይ በደረሰው ጉዳት ዙሪያ እንደሚመክር ተናግረዋል።

በተጨማሪም ልዑኩ በቀጣይ ምን መሠራት እንዳለበት ከአከባቢው የእምነት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ እንዲሁም ከመንግሥት እና ከጸጥታ አካላት ጋር ምክክር ይደረጋል ብለዋል።

የጉባኤው አባል የሆኑት የሐይማኖት ተቋማትም የድጋፍ ስራዎችን እንደሚያከናውኑና በአሜሪካ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አገረ ስብከቶችን የሚመሩ ሊቃነ ጳጳሳት በኦን ላይን ያሰባሰቡት ድጋፍም ለህበረተሰቡ እንደሚለገስ ዋና ጸሐፊው ገልጸዋል።

ምንጭ፡- ኢዜአ
@YeneTube @FikerAssefa
14.6K viewsedited  11:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 14:10:44
የኢትዮጵያ መንግስት የዓለም ምግብ ፕሮግራም በትግራይ ያደረገውን የሰብአዊ ድጋፍ አድንቋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት የዓለም ምግብ ፕሮግራም በትግራይ ክልል ሰብአዊ ድጋፍ ላደረገው አጋርነት ያለውን አድናቆት መግለጹን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ትዊተር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
14.4K views11:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 12:49:53
ኢትዮጵያ በመጭዎቹ ዓመታት ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በሰባት ውሀማ ስፍራዎች የውሀ ትራንስፖርት አገልግሎት እንደምታስጀምር አስታወቀች።

ሀገሪቷ አሁን ያሉት እንዳለ ሆኖ ተጨማሪ የመሰረተ ልማት ማስፋፋት ይሰራሉ ቀድመው ስራ የጀመሩት ደግሞ በተሻለ ቴክኖሎጂ ወደ ስራ እንዲገቡ ይደረጋል ተብሏል።

በ10 አመቱ መሪ የትራንስፖርት የልማት እቅድ ውስጥ ከተቀመጡ ጉዳዮች መካከል የውሀ ትራንስፖርት መሰረተ ልማት ይገኝበታል፡፡

በዚህም በጣና ሀይቅ፣ ባሮ ወንዝ፣ አባያ፣ ጫሞ፣ ተከዜ፣ ህዳሴ ግድብ እና በጊቤ የውሀ ትራንስፖርት መሰረተ ልማት ለማልማት ታቅዶ ስራ መጀመሩ ተገልጿል፡፡

የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጅነር የኋላሸት ጀመረ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት በ10 ዓመት የትራንስፖርት ዘርፍ መሪ የልማት ዕቅድ የዉሃ ትራንስፖርት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።

የዉሃ ትራንስፖርት ደህንነቱ የተጠበቀና በሚፈለገዉ ደረጃ በሀገራችን ያለዉን ለዉሃ ትራንስፖርት አገልግሎት አመቺ የሆኑ ወንዞችና ሃይቆች በአግባቡ በመጠቀም ለህዝብና ለጭነት ትራንስፖርት አመቺ ሆነው ይለማሉ ተብሏል፡፡

የውሀ ትራንስፖርት አማራጭ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ ሆኖ እንዲያገለግል እንዲሁም ለመዝናኛና ለቱሪስት መስህብነትም እንዲያገለግሉ መሰረተ ልማቶች በስፋት ይለማሉ ተብሏል፡፡

[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
10.6K views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 11:45:13
ትናንት በሰሜናዊ ሕንድ በተከሰተው የበረዶ ግግር ናዳ 14 ሰዎች ሲሞቱ ከ 150 በላይ ሰዎች ጠፍተዋል!

በሰሜን ህንድ በምትገኘው ኡታራካንድ ግዛት በሁለት የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጄክቶች ላይ የበረዶ ግግር ተደርምሶ የጎርፍ አደጋም አስከትሏል፡፡በዚህ የጎርፍ አደጋ እስካሁን የ14 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 150 ሰዎች ደግሞ የደረሱበት አልታወቀም፡፡ ጎርፉ የግድቡን የተወሰነ ክፍል ፣ ዛፎችን ፣ ድንጋዮችን እና ሌሎችንም በመንገዱ ያገኛቸውን ቁሶች እና ሰዎችን እየያዘ ሲምዘገዘግ በወቅቱ የተነሱ ፎቶዎች እና የቪዲዮ ምስሎች ያሳያሉ፡፡የነፍስ አድን ቡድኖች ሌሊቱን በሙሉ የተረፉ ሰዎችን እና አስከሬኖችን ለማግኘት ሲያፈላልጉ ማደራቸውን የሲኤንኤን ዘገባ ያሳያል፡፡ በዋሻ ውስጥ ውስጥ የተጠለፉ 15 ሰዎችን ማትረፍ እንደተቻለም ተገልጿል፡፡

Al ain
@YeneTube @FikerAssefa
14.8K views08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 10:43:51 የቡድን 20 አገሮች የውጭ ዕዳ ክምችት ለተጫናቸው ታዳጊ አገሮች ማቅለያ ካመቻቹት ዕድል በተጨማሪ፣ ከውጭ የግል አበዳሪዎች ተመሳሳይ የዕዳ ጫና ማቅለያ ኢትዮጵያ ልትጠይቅ እንደምትችል መንግሥት አስታወቀ።

የገንዘብ ሚኒስቴር ባለፈው ሰኞ ጥር 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው በዓለም አቀፉ የገንብ ተቋም አይኤምኤፍ አማካይነት የቡድን 20 አገሮች እ.ኤ.አ. 
በ2020 አጋማሽ ላይ በከፍተኛ የዕዳ ጫና ውስጥ ለሚገኙ ታዳጊ አገሮች ካመቻቹት የዕዳ ማቅለያ በተጨማሪ የውጭ የግል አባደሪዎች ተመሳሳይ የዕዳ ጫና ማቅለያ እንደሚጠይቅ አስታውቋል። 

መንግሥት ይህንን የሚያደርገው የኢትዮጵያን የውጭ ዕዳ ጫና ለመቀነስ እንደሆነ የገለጸው መግለጫው፣ ከዚህ በተጨማሪ የአገሪቱን የውጭ ዕዳ ጫና ለመቀነስ በዓለም ዓቀፉ የገንዘብ ድጋፍ የተለያዩ ጥረቶችን በማድረግ ላይ እንደሆነ አመልክቷል።

የግል የውጭ አበዳሪዎች ለኢትዮጵያ የሰጡት ብድር የመክፈያ ጊዜ እንዲራዘም ወይም የመክፈያ ጊዜ እፎይታ እንዲሰጡ የሚጠይቀው የኢትዮጵያን የወደፊት የውጭ ብድር የማግኘት ዕድል በሚያስጠብቅ መንገድ እንደሚሆንም ገልጿል። 

[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
10.7K views07:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 10:26:51
ወልቂጤ ከተማ በመንግስትና በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ የ2ኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ!

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት በመንግስትና በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ ባለ 5 ወለል የማስፋፊያ አዲስ ህንፃ ተጠናቆ ተመርቋል፡፡ህንፃው 2ሺህ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተናገድ እንደሚችልም ተመልክቷል፡፡

[ደሬቴድ]
@YeneTube @FikerAssefa
14.1K views07:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 10:26:15
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የዳውሮ ታርጫ ካምፓስ ተማሪዎቹን እያስመረቀ ነው!

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የዳውሮ ታርጫ ካምፓስ ለ3ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት እያስመረቀ ይገኛል።

ካምፓሱ በመደበኛ እና በተከታታይ የትምህርት መርሃግብር በቅድመ ምረቃና በድህረ ምረቃ ያሰለጠናቸውን 365 ተማሪዎችን እያስመረቀ ሲሆን፤ ከተመራቂ ተማሪዎች መካከል 251 ወንድ እና 114 ደግሞ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል።

@YeneTube @FikerAssefa
13.5K views07:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 10:24:36
ለጓደኛ፣ ለወዳጅ ዘመድ፣ ለሙሽሮች እና ለተመራቂዎች ለየት ያለ ስጦታ መስጠት ይፈልጋሉ?
#join

@giftsoflovee
@giftsoflovee

+251914839754
+251936871620
#ኣድራሻችን፡ 4 ኪሎ: ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ
10.5K views07:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-08 10:24:36
ሁሉንም ሰብስቦ በአንድ ላይ የያዘ የግብይት ድረገፅ

@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com

0953707070
10.1K views07:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ