Get Mystery Box with random crypto!

Natnael Mekonnen

የሰርጥ አድራሻ: @natnaelmekonnen21
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 174.28K
የሰርጥ መግለጫ

በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ሲፈልጉና ማስታወቂያ ማሰራት ከፈለጉ 👉 @NatnaelMekonnen7
Facebook.com/natnaelmekonnen.et
Instagram.com/natnaelmekonnen21

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-05-05 12:15:05 እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን! በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ እንዲሆን መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ። ሃገራችንን ሰላም ያድርግልን!

መልካም የትንሣኤ በዓል!!
21.4K views09:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-03 21:46:26
በአዲስ አበባ ቅርጫ ተከልክሏል የሚባለው ሃሰት ነው አልተከለከለም!

በአዲስ አበባ ከተማ በዘንድሮዉ ዓመት የሚከበረዉን የትንሳኤ በአል አስመልክቶ ህብረተሰቡ በየቤቱ በእርድ መልክ የሚጠቀመዉን እና በየአካባቢዉ የቁም እንስሳትን ቅርጫ በማረድ የሚከፋፈለዉን ተከልክሏል በሚል በማህበራዊ ሚዲያዉ ሀሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ ይገኛል።

በመሆኑም ከዚህ ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ክልከላ ያልተደረገ ሲሆን በየአካባቢዉ በህገ ወጥ መንገድ እርድ በመፈፀም ለሆቴሎች እና ለስጋ ቤቶች በማከፋፈል ተግባር ላይ የሚገኙ አካላት የቁም እንስሳቱ ጤንነት ባልተረጋገጠበት ሁኔታ የከተማዉን ነዋሪ ጤንነት ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል።

የከተማችን ነዋሪ በአላትን ሽፋን በማድረግ ጤንነቱ ያልተረጋገጠ እንስሳት አርዶ ማከፋፈል በጤና ላይ የሚያደርሰዉን ጉዳት ግምት ዉስጥ በማስገባት በህገወጥ እርድ የሚሰማሩ አካላት በሚደረገዉ ቁጥጥር ተባባሪ እንዲሆን መልክታችንን እናስተላልፋለን።
15.7K views18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-03 19:27:09
“ በየጊዜው ወጣቶች የምገብርበት የጦርነት ምዕራፍ መዘጋት አለበት “ - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ በኩል ዛሬ መልዕክት አሰራጭተው ነበር።

በዚህም ፤ “ የህዝባችን ሁለንተናዊ መብትና ጥቅም ከማረጋገጥና አስተማማኝ ከማድረግ የሚቀድም ሌላ አጀንዳ የለንም “ ብለዋል።

“ የህዝባችን ጥቅምና መብት የሚያረጋግጥ መንገድ ሁሉ እንጓዘዋለን “ ያሉት አቶ ጌታቸው “ ጉዞው እንዲሳካ የህዝቡ ተሳትፎ ወሳኝ ነው “ ሲሉ አክለዋል።

ፕሬዜዳንቱ ፤ “ ከሚገባው በላይ ያበረከተ ህዝብ በቅንነትና ታማኝነት ማገለገል ይገባል “ ሲሉም ገልጸዋል።

“ ህዝቡ ከጦርነትና ጦርነት ወለድ ችግሮች በማላቀቅ ወደ አስተማማኝ ሰላም እንዲሸጋገር መስራት ይገባል “ ሲሉም አስገንዝበዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ “ በየጊዜው ትኩስ ሃይል የሆኑትን ወጣቶች የምንገብርበት የጦርነት ምዕራፍ ተዘግቶ ፤ የልማትና የእድገት ፍላጎታችን እንዲሳካ መስራት አለብን “ ብለዋል።
21.5K views16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-03 14:30:55
ሰምተዋል ?

የትርፋማው የአያት አክሲዮን ሽያጭ ሊጠናቀቅ ነው ::


በ2014 ዓ.ም 44% እንዲሁም በ2015 ዓ.ም 51.38% የአክሲዮን ትርፍ ለባለ አክሲዮኖች አከፋፍሏል

የአንድ ሚሊየን አክሲዮን የነበራቸው በ2015 ዓ.ም ብቻ 513,800 ብር አትርፈዋል

ከ112,500 ብር ጀምሮ የአክሲዮን ባለቤት በመሆን በቶሎ የትርፍ ተካፋይ ይሁኑ

አያት አ.ማ. የተሰማራባቸው መስኮች
በሪል ስቴት ልማት
በሆቴልና ቱሪዝም
 በማርብል ማምረቻ ኢንዱስትሪ
በጠጠር ማምረቻ ኢንዱስትሪ
በብሎኬት ማምረቻ ኢንዱስትሪ
በእንጨትና ብረታብረት ውጤቶች ማምረቻ ኢንዱስትሪ
በትምህርት ኢንቨስትመንት እና
በፋይናንሻል ኢንቨስትመንት

ትርፋማ የሆነውን የአያት አክሲዮንን ለእርስዎ ፣ ለታዳጊ ልጅዎ  ፣ ለቤተሰብዎ እና ለወዳጅ ዘመድዎ በስጦታ ያበርክቱ

ትውልደ ኢትዮጵያውያን ባላችሁበት ሆናችሁ በወዳጆቻችሁ በኩል መግዛት ትችላላቹህ

አሁኑኑ በ
0911085103 በቀጥታ ወይንም በቴሌግራም በዋትሳፕ ይደውሉ @EngineerNahomT
24.4K views11:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-03 14:30:40
ናሽ ልዩ የጥርስ ህክምና ክሊኒክ ዘመኑ ባፈራቸው መሳሪያዎ ች በመታገዝ ሙሉ የጥርስ ህክምናን በመስጠት ላይ ይገኛል::  ከምንሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል በከፊል
➢ መጥፎ የአፍ ጠረንን ማከም
➢ የቆሸሹ ጥርሶችን በማሽን እናፀዳለን
➢ በህክምና መዳን የማይችሉትን ጥርሶች መንቀል
➢ ወጣ ገባ ያሉ ጥርሶችን በ ኦርቶዶንቲክ አፕላይንስ እና በብሬስ ማስተካከል
➢ የጥርስ ስር ህክምናን መስጠት
➢ የተቦረቦሩ ጥርሶችን እንሞላለን
➢ የተነቀሉ ጥርሶችን በሰው ሰራሽ አርተፊሻል መተካት
➢ የጥርስ ራጅ አገልግሎት መስጠት

አድራሻ: ሜክሲኮ ቡልጋሪያ ጫፍ ትራፊክ ማብራቱ አጠገብ
  Tel: 0913858561
21.2K views11:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-03 12:37:17 የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲን በተመለከተ ከቦርዱ የተሰጠ መግለጫ

የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ሊቀመንበር ከሀገር መውጣታቸውንና ፓርቲውንም የሚመራ ሰው መወከላቸውን ከውጭ ሀገር ሆነው ለቦርዱ ሲያሳውቁ ከፓርቲው አመራሮች መኃል ይህ በሊቀመንበሩ የተሰጠው የውክልና ሥልጣን ደንቡን የተፃረረ ነው የሚል ቅሬታ ለቦርዱ አቀረቡ፡፡ ቦርዱም ሊቀመንበሩ የሰጡት የውክልና ሥልጣን ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ አንፃር የተፈፀመ መሆን አለመሆኑን መረመረ፡፡ የፓርቲው መተዳደያ ደንብ አንቀጽ 22/1/ የፓርቲው ሊቀመንበር በማይኖሩበት ወቅት ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበሩ ሊቀመንበሩን ተክተው እንደሚሰሩ ደንግጓል፡፡ በዚሁ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ከሀገር በወጡት የፓርቲው ሊቀመንበር የተሰጠው ውክልና ደንቡን የተፃረረ በመሆኑ ቦርዱ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡ በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 22/1/ መሠረትም እንዲፈፅም ወስኗል፡፡ ይሁንና በፓርቲው አመራሮች መኃል አለመግባባቱ እየጨመረ በመሄዱ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 74 (6) መሠረት ጉዳያቸው በባለሙያዎች ጉባኤ እንዲታይ ቦርዱ ወስኖ የባለሙያዎች ጉባኤ እያቋቋመ ይገኛል፡፡

ፓርቲው በ2015 በጀት ዓመት ከመንግሥት የሚሰጠውን ድጋፍ ከቦርዱ ብር 1,184,259.85 (አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሰማንያ አራት ሺህ ሁለት መቶ ሃምሣ ዘጠኝ ብር ከሰማንያ አምስት ሣንቲም) ወስዷል፡፡ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 82/2/ መሠረት ፓርቲዎች ስለወሰዱት የመንግሥት ድጋፍ የኦዲት ሪፖርት የማቅረብ ግዴታ አለባቸው፡፡ ይሁንና የኦዲት ሪፖርቱን ፓርቲው ሳያቀርብ በመቅረቱ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ ሳያቀርብ ቢቀር ፓርቲው የመሰረዝ ዕጣ ፈንታ እንደሚገጥመው በማሳሰብ ቦርዱ ለፓርቲው አሳውቋል፡፡ ይሁንና ፓርቲው ይህንንም ሪፖርት እስከ ዛሬው ቀን ድረስ አላቀረበም፡፡

በአመራሮቹ መኃል ያለውን ልዩነት በፓርቲው ደንብና በአዋጅ 1162/2011 መሠረት ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ባለበት ሁኔታ፤ እንዲሁም ከግብር ከፋዮች ተሰብስቦ ለፓርቲው የተሰጠውን የድጋፍ ገንዘብ እንዲያወራርድ በሕጉ መሠረት ፓርቲው ተጠይቆ እያለ፤ በተለያዩ ማኅበራዊና መደበኛ ሚዲያዎች ላይ በመቅረብ የተሳሳተ መረጃ በመስጠት የቦርዱን ጥረት እያንኳሰሱ ሥሙንም የማጥፋት ሥራ ጥቂት የፓርቲው አመራሮች እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም ቦርዱ ይህን መግለጫ ለመስጠት ተገዷል፡፡

እንደሚታወቀው ቅሬታ አለኝ የሚል ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራርም ሆነ የፖለቲካ ፓርቲ አባል በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብና በምርጫ አዋጁ የተቀመጡ የቅሬታ አቀራረብ ሂደቶችን ተከትሎ ቅሬታውን ማቅረብ እንዲሁም ቦርዱም በሚሰጠው ውሣኔ ቅር የተሰኘ አካልም ጉዳዩን ለፍርድ ቤት ማቅረብ እንደሚችል በአዋጁ በግልፅ ተደንግጓል፡፡ በዚሁ መሠረትም ጉዳያቸውን ለከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርበው እየታየ ይገኛል፡፡

ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ እያለ ቦርዱም ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ባለበት ሁኔታ የቦርዱን ስም በማይገባ እና በተሳሳተ መንገድ የተለያዩ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሚካሄድን የስም ማጥፋት ተግባር ቦርዱ እንደማይቀበለው አጥብቆ እየገለፀ ይህ የስም ማጥፋት እና የተሳሳተ መረጃ የማሰራጨት ሂደት በፓርቲው ጥቂት አመራሮች የሚቀጥል ሆኖ ቢገኝ ቦርዱ ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ የሚገደድ መሆኑን አጥብቆ ያሳስባል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሚያዝያ 24 ቀን 2ዐ16 ዓ.ም.
22.5K views09:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-03 12:36:50
የአያትን አክሲዮን የገዛ ሁሌም ትርፋማ

በ 2015 ዓ.ም 51% ትርፍ /Dividend/ ለባለክሲዮኖች አከፋፍለናል

በቀላል አማርኛ የ 1 ሚሊዮን ብር አክሲዮን የነበራቸው ባለአክሲዮኖች 510 ሺ ብር ትርፍ /Dividend/ አግኝተዋል

የ 5 ሚሊዮን ብር የገዙ 2.5 ሚሊዮን ብር አትርፈዋል

የአንድ አክሲዮን ዋጋ 100 ብር ነው

ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የአክሲዮን መጠን 2500 ነው

ዝቅተኛ የአክሲዮን ዋጋ 262,500 ብር ፣ 5% የአገልግሎት ክፍያን ጨምሮ

ከፍተኛ የአክሲዮን መጠን ገደብ የለውም

40% ከፍለው ቀሪውን በሶስት ዓመት መጨረስ ይችላሉ

አክሲዮኑን ከገዙ ከአንደኛው ወር ጀምሮ የትርፍ ተካፋይ መሆን ይጀምራሉ

ለበለጠ መረጃ: በ 0948888672/ 0935407638 ይደውሉ
23.0K views09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-02 20:24:15
TPLF ወልቃይትን ይቅርና በትግራይ ክልል መከላከያ ይዞት የነበረን 1 ኢንች መሬት በጦርነት መያዝ አይችልም። ጦርነት ከፍቶ አንድ ኢንች መሬት ልያዝ ካለ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ለመጣሱ ማረጋገጫ ይሰጣል። የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት TPLF ጦርነት እንዲከፍት አይደለም ትጥቅ እንዲኖረው አይፈቅድለትም። የስምምነት አስኳሉና ቀዳሚው ጉዳይ ተኩስ ማቆም ትጥቅ መፍታት ነውና።

TPLF ይህን የሰላም ስምምነት ላለመፈፀም ያለውን ትጥቅ ይዞ ለመቀጠል ቀድሞ በእኔ ስር ለነበሩት ለወልቃይት ወይም ለራያ መሬት ነው ጦርነት የምከፍተው ችግሬ ከአማራ ክልል ጋር ነው በሚል እንደለመዱት ሌላውን እንደሞኝና እንደአላዋቂ በመቁጠር ከፋፍሎ የፖለቲካ ወታደራዊ ድል ለማስመዝገብ ጦርነት እከፍታለሁ ብሎ ከገፋበት ግጭቱ በቀጥታ ከፌደራል መንግስቱ ጋር ይሆናል። TPLF ም ራሱን ለማጥፋት በፈቃዱ እንደወሰነ ይቆጠራል።

መንግስት የአማራን የኦሮሚያን የሲዳማን የአፋርን የሶማሌን የቤንሻንጉልን እንዲሁም የሌሎቹን ክልሎች ልዩሃይል ትጥቅ ያስፈታውና የልዩሃይል አባላትን ወደፖሊስ መከላከያ እንዲቀላቀሉ ወይም ምርጫቸውን እንዲከተሉ ያደረገው እነሱ በታጠቀው TPLF ወይም ሌላ አካል እንዲጠቁ አይደለም። ከመከላከያ ጋር ተገዳዳሪ የሆነ ሃይል በአንድ ሐገር ውስጥ እንዳይኖር ነው። እነሱን ትጥቅ አስፈትቶ ለዛውም በሰላም ስምምነቱ ዋና ጉዳይ የሆነውን ተኩስ የማቆምና ትጥቅ የመፍታት ስምምነትና አጀንዳን ደርቦ የትግራይ ክልል እስከ ትጥቁ ይቀጥል ሲፈልግ በተመቸው ጊዜ ጦርነት ይክፈት ሊባል አይችልም። የኢትዮጵያ መከላከያ መቀሌ ሊገባ ጫፍ ደርሶ እንዲቆም የተደረገው በጉልበት አሸንፎ ሁሉንም ነገር ከመቆጣጠር በጉልበት ለተሸነፈው TPLF በ1/5 ጥርነፋ አንድ አይነት መረጃ እየተጋተ ለደገፈው ቁጥሩ ለማይናቅ የትግራይ ሕዝብ ለኢትዮጵያ ቀጣይ ሁኔታ ጉዳዩን በሰላም መጨረስ የተሻለ ዕድል ይዞ ይመጣል የአሸናፊ ተሸናፊ ትርክት ቀርቶ የኢትዮጵዬ አሸናፊነት ይታወጃል ሁሉንም አሸናፊ የሚያደርግ የፖለቲካ ባህል ይገነባል በሚል ነበር።

ከሰሞኑም በራያ በኩል የጦርነት ትንኮሳ ሲደረግ የፌዴራል መንግስቱ መከላከያ ምላሽ ያልሰጠው መላሽ የሚሰጥ ከሆነ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሚሆን በመሆኑ አሁንም የጥሞና እና የሰላም ዕድል በተለይ ለትግራይ ሕዝብ የሰላም ፍላጎት ቦታ በመስጠት ነው። TPLF በሁሉም በኩል ላለው የፖለቲካ ኤሊት ከፍተኛ ንቀት ስላለውና ራሱን እንደብልጥ አዋቂ አድርጎ የሚያስብ ከመሆኑ አንፃር በመከፋፈል በተናጠል ቀስ ቀስ እያልኩ የፖለቲካ ወታደራዊ ድል አስመዘግባለሁ ብሎ የሚያደርገው ሙከራ የመጨረሻው ሊሆን ይችላል።
32.0K views17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-02 18:10:55
ለፉሲካ በአል ወደ ሀገር እየገቡ ላሉ 2ኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን በቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት አቀባበል እየተደረገላቸው ነው::

በአቀባበል ስነ ስርዓት ላይ የቱሪዝም ሚንስትሯ አምባሳደር ናሲሴ ጫሊን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

“Back to your origins” የሚል ስያሜ የተሰጠው እና ጠ/ሚር ዐቢይ አህመድ በውጭ ለሚኖሩ የ2ኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን ያቀረቡት ጥሪ በሶስት ዙሮች የሚካሄድ ነው::

በዚህም እከታህሳስ 20 እስከ ጥር 30 በመጀመሪያው ዙር ከብዝኃ ባህል መሰረትዎ ጋር ይገናኙ በሚል በተሰየመው መርሃ ግብር ወደ ሀገራቸው ገብተው እንደነበር ይታወሳል።

አሁን ደግሞ ታሪካዊ መሰረትዎን ይወቁ (connect to your historical roots) በሚል በተሰየመው መርሀግብር በሁለተኛ ዙር ወደ ሀገር እየገቡ ይገኛሉ::

በሁለተኛው ምዕራፍ ኢትዮጵያውያን የእረፍት ጊዜያቸውን (Spring Break) ተጠቅመው የሀገራቸውን ታሪክ እንዲያውቁ፣ የአያቶቻቸውንና ቅድመ አያቶቻቸውን አይበገሬነትና መስዋዕትነት
እንዲሁም ከራሳቸው አልፎ ለጥቁር ህዝቦች ነፃነት ያበረከቱትን አስተዋፅዖ አንዲረዱ በማድረግ የሀገር ፍቅር ስሜታቸው እንዲዳብር ብሎም በዚህ አኩሪ
ታሪክ ተነሳስተው በዘመናቸው ፍሬያማ አስተዋፅዖ እንዲያበረክቱ ለማስቻል ያለመ ነው::

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ትኬት፣ሆቴሎች፣ አስጎብኚ ድርጅቶች የዋጋ ቅናሽ በማድረግ 2ኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያኑን ተቀብለው በማስተናገድ ላይ ናቸው::
32.5K views15:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-02 16:13:25
የተሰጠንን ተልዕኮ በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ የህብረተሰቡን ሰላም እናረጋግጣለን ፦ ሌተናል ጄኔራል ዘውዱ በላይ

አዛዡ የአሃዱዎችን የግዳጅ አፈፃፀም በተመለከተ ከሠራዊት አባላቱ ጋር የተወያዩ ሲሆን ማዕከላዊ እዝ በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና አሸባሪውን የሸኔ ቡድን በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጥፋት ቡድኑ የሚንቀሳቀስባቸው ዞኖች ወደ ሰላምና ልማት እንዲመለሱ በማድረግ ተልዕኳችንን ለመወጣት ከመቼውም ጊዜ በላይ መዘጋጀት አለብን ብለዋል።

ዕዙ የሠራዊቱን የማድረግ አቅም የሚያጎለብቱ ስልጠናዎችን ከግዳጅ ጎን ለጎን በመስጠት የአመራሩንና የአባሉን ስነ ልቦናዊ፣ አካላዊና ታክቲካዊ ክህሎቱን በማሳደግ ግዳጁን በብቃት የሚፈፅም ሰራዊት ገንብተናል ፤ ሰራዊቱ ማንኛውንም ተፈጥሯዊም ሆነ ሰው ሰራሽ መሰናክል በማለፍ ጠላትን መደምሰስ የሚያስችል ቁመና ላይ ይገኛል ሲሉም ገልፀዋል።

የመንግስትን የሰላም ጥሪ ባለመቀበል ጫካ የመረጡ ሀይሎች በራሳቸው ጊዜ የቀረበላቸውን አማራጭ እንዲቀበሉ ካልሆነም ተበትኖ እየተንቀሳቀሰ ያለውን የሸኔን የሽብር ቡድን በመደምሰስ አስፈላጊውን ዋጋ ከፍለን ሰላምን ለህብረተሰቡ እናረጋግጣለን ሲሉ ጄኔራል መኮንኑ ተናግረዋል።

ከሠራዊቱ ጋር ፊት ለፊት የተወያዩት ሌተናል ጄኔራል ዘውዱ በላይ የቀጣይ ተልዕኮ ውጤታማነት የሚረጋገጠው የሰራዊቱ ሞራላዊና ስነ- ልቦናዊ ዝግጁነት የተገነባ ሲሆን መሆኑን ጠቁመው እስካሁን በስልጠና ላይ የተፈጠሩ አቅሞች ይህንን የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ማዕከላዊ ዕዝ በተሰማራባቸው አካባቢዎች ከህብረተሰቡና ከፀጥታ ሀይሉ በመጣመር ሰላም በማረጋገጥ ለህዝቡ እፎይታ ለመስጠት የተለመደ ጀግንነቱን እና ድል አድራጊነቱን ለማስቀጠል መነሳሳት ይገባል ሲሉ ለሰራዊቱ አባላት መልዕክት አስተላልፈዋል።
29.6K views13:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ