በመጪው ሚያዚያ ወር መጀመሪያ 9 ሚሊየን የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ክትባት ወደ ሃገር ውስጥ እንደሚገባ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ::
የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ኢትዮጵያ አባል በሆነችበት የአለም አቀፉ የኮቫክስ የጋራ ትስስር በኩል የሚገባውን ክትባት አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል::
ክትባቱ በተያዘው አመት ሚያዝያ መጀመሪያ እንደሚገባ የገለፁት ሚኒስትሯ ክትባቱም በተለይም ለበሽታው ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በቅድሚያ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል::
ይሄንን ሃላፊነት የሚወጣ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱንም ገልፀዋል::ከክትባቱ ጎን ለጎን ህብረተሰቡ አሁንም ቢሆን መከላከል ላይ ትኩረት እንዲያደርግም ሚኒስትሯ ጥሪ አቅርበዋል::
@YeneTube @FikerAssefa