Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 125.42K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 481

2021-02-13 09:47:11
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት ሠላም አስከባሪ የሠራዊት አባላትን እያስመረቀ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ጦሯን ለዓለም አቀፍ የሠላም ማስከበር ተልዕኮ ማዝመቷን አጠናክራ መቀጠሏን የመከላከያ ሚኒስቴር በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አመላክቷል፡፡የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት የ15ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አስከባሪ ሻለቃ በማስመረቅ ላይ ነው።ሕግን በማስከበር እና በህልውና ዘመቻ ላይ የቆየው የመከላከያ ሠራዊት የጎረቤት ሀገርን ሠላም ለማስፈን ወደ ጁባ ለመዝመት 15ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አስከባሪ ሻለቃ ስልጠናውን ማጠናቀቁን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
17.2K views06:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 09:45:17
ሁሉንም ሰብስቦ በአንድ ላይ የያዘ የግብይት ድረገፅ

@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com

0953707070
6.1K views06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-12 19:57:11 የኢትዮጵያ መንግሥት የአሜሪካ ኮንግሬስን እና የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደርን የሚያግባባለት ኩባንያ መቅጠሩን ፎሬን ፖሊሲ መጽሄት ዘግቧል፡፡በዋሽንግተን የኢትዮጵያ ኢምባሲ ቬኔብል ከተባለው የፖሊሲ አግባቢ ኩባንያ ጋር የ3 ወራት ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ለአገልግሎቱ ኢምባሲው በወር 35 ሺህ ዶላር ይከፍላል ተብሏል፡፡ ኩባንያው የተቀጠረው በሕዳሴ ግድብ ድርድር እና በትግራዩ ግጭት ላይ የአሜሪካ መንግሥትን ለማግባባት ነው፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
15.2K views16:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-12 19:34:11
ፊች የተባለው ዐለማቀፍ የሀገራት ብድር ከፋይነት ደረጃ አውጭ ሰሞኑን የኢትዮጵያን የብድር ከፋይነት ደረጃ በ2 ነጥብ ዝቅ እንዳደረገ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ ድርጅቱ የኢትዮጵያን ደረጃ ያወረደው፣ መንግሥት የብድር ቅነሳ እንዲደረግለት ወይም የመክፈያ ጊዜ እንዲሸጋሸግለት ቡድን 20 ሀገራትን እንደሚጠይቅ መማሳወቁን ተከትሎ ነው፡፡ ሌሎች ሀገራትም የኢትዮጵያን መስመር ከተከተሉ ደረጃቸውን ዝቅ እንደሚያደርገው ድርጅቱ ገልጧል፡፡

[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
18.5K views16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-12 17:44:09
ንግድ ባንክ የወለድ ምጣኔ ጭማሪ አደረገ!

ንግድ ባንክ በየአመቱ በአማካኝ የማስመዘግበው የእድገት መጠን እየቀነሰ በመምጣቱ በአንዳንድ አገልግሎቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ አድርጌያለሁ ሲል በዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ አቤ ሳኖ በኩል አስታውቋል።

በዚህም መሰረት ለቤቶች ልማት 9.5 በመቶ የነበረዉ የወለድ መጠን ወደ 10.5 በመቶ፣ የማዳበሪያ 9.25 በመቶ የነበረዉ የወለድ መጠን ወደ 10 በመቶ፣ የኮርፖሬት ቦንድ ብድር 9 በመቶ የነበረዉ የወለድ መጠን ወደ 10 በመቶ፣ የዉጭ ምንዛሬ በአንድ ፔሬድ ማለትም በ90 ቀናት 5.5 በመቶ የነበረዉ ወደ 9.5 በመቶ ከፍ ማድረጉን ባንኩ ተናግሯል።

በሌላ በኩል ለኤሌክትሪክ ኃይል፣ ለመድሀኒት አቅርቦት፣ ለስኳር፣ ለማዳበሪያ እንዲሁም ለዘይት የሚያስፈልጉ የውጭ ምንዛሬዎች ላይ ያለው የወለድ መጠን ወደ 4.5 በመቶ ዝቅ ማድረጉን ባንኩ ገልጿል።

Via Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
18.5K views14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-12 17:43:07 ኢትዮጵያ ከ6 ሚሊዮን በላይ ዶላር በሆነ ወጪ የክትባት ማጓጓዣ ተሸከርካሪዎችን ልትገዛ መሆኑን አስታወቀች።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ከተባበሩት መንግስታት ጋር በ6 .4 ሚለዮን ዶላር የግዥ መግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡በዚህ ገንዘብም የማቀዝቀዣ ክፍል የተገጠመላቸው የተለያዩ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎችም ክትባቱን ተደራሽ ለማድረግ የሚያለግሉ ግብአቶች ግዢ እንደሚፈፀም ኤጀንሲው አስታውቋል፡፡

የጋራ ስምምነቱን የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ጋልጋሎ እና በመንግስታቱ ድርጅት የኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ህብረት ተወካይ የሆኑት ወ/ሮ ወርቅነሽ መኮንን ተፈራርመዋል፡ለግዥው 6.4 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የተመደበ ሲሆን የበጀት ድጋፋ የተገኘው ከአለም አቀፉ የክትባት ድጋፍ ድርጅት መሆኑን ኤጀንሲው አስተውቋል።

[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
13.2K views14:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-12 17:37:20
ህብረተሰቡ የህገመንግስት ትርጉም የሚስፈልጋቸውን ጥያቄዎች ባግባቡ መገንዘብ ባለመቻሉ ባለፉት 5 ዓመታት የቀረቡ አቤቱታዎች በጣም ዝቅተኛ መሆናቸውን የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡

የፍርድ ቤቱ ፕረዚደንትና የአማራ ክልል ህገመንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሰብሳቢ አቶ አብዬ ካሳሁን ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ከ2008 ዓ ም ጀምሮ 14 ብቻ የህገ መንግስት ትርጉም አቤቱታዎች ቀርበዋል፡፡ከዚህ ውስጥ 4ቱ የህገ መንግስት ትርጉም የሚያስፈልጋቸው አቤቱታዎች ሆነው በመገኘታቸው በውሳኔ ሀሳብ በማስደገፍ ለመጨረሻ ውሳኔ ለአማራ ክልል ህገመንግስት ተርጓሚ ኮሚሽን ተልከው የህገ መንግስት ትርጉም ያስፈልጋቸዋል በሚል እንዲፀኑ መደረጉንም አቶ አብዬ ተናግረዋል፡፡10ሩ ደግሞ እንደማያስፈልጋቸው የውሳኔ ሀሳብ እንደቀረበባቸውም አስረድተዋል፡፡ የአቤቱታዎቹ ቁጥር አናሳነት ችግር አለመኖሩን የሚያሳዩ እንዳልሆነ ያመለከቱት ፕረዚደንቱ፣ በየደረጃው የህገመንግስት ትርጉም የሚሹ ኢ ህገመንግስታዊ ህጎች፣ የተዛቡ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችና የፍርድ ቤት ዳኝነቶች ሊኖሩ ስለሚችሉ ህብረተሰቡ መብቱን ወደ ህገመንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ አቤት ማለት አለባቸው ሲሉ አመልክተዋል፡፡በአጠቃላይ በክልሉ ካለው የህዝብ ቁጥር አኳያ የህገመንግስት ትርጉም አቤቱታዎች በዝቅተኛ ደረጃ ላይ መገኘታቸው ህብረተሰቡ ስለጉዳዩ ግንዛቤ እንደሌለው ማሳያ መሆኑን የገለፁት አቶ አብዬ፣ የህግ አዋቂዎች፣ ብዙሀን መገናኛና የህግ ተቋማት ለህብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲፈጥሩ አሳስበዋል፡፡አማራ ክልል 11 አባላት ያሉት የህገ መንግስት አጣሪ ጉበኤ አሉት፡፡

[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
15.8K views14:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-12 14:54:38 ኦነግ በቀጣዩ ምርጫ ላይ የሚያስመዘግበው እጩ ተወዳዳሪ እንደሌለው አስታወቀ።

ከአራት ወራት በኋላ እንደሚካሄድ የሚጠበቀው 6ኛው አገር አቀፍ ምርጫ ፓርቲዎች የእጩ ተወዳዳሪዎቻቸውን ከሰኞ ከየካቲት 8 እስከ 21 ቀን 2013 ዓ.ም ማስመዝገብ እንዳለባቸው የምርጫ ቦርድ ጊዜ ሰሌዳ ያስረዳል።በውዝግብ ውስጥ የሚገኘው ኦነግ ደግሞ የውስጥ ችግሩን ሳይፈታ የእጩ ምዝገባ ወቅት ደርሷል።በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ቀናት በቀሩት የእጩዎች ምዝገባ የማስመዘግበው እጩ እንደሌለው ገልጿል።ፓርቲው እንዳስታወቀው ከሆነ በየምርጫ ክልሎች ላስመዘግባቸው ያሰብኳቸው እጩ ተወዳዳሪዎቼ በሙሉ በእስር ላይ ይገኛሉ ብሏል፡፡

ምርጫ ስለመካሄዱ በራሱ እርግጠኛ አይደለሁም የሚለው ኦነግ በፖርቲያችን ላይ ከፍተኛ ጫና ከገዢው ፖርቲ እየደረሰበት እንደሆነ ተናግሯል።የፓርቲው ቃል አቀባይ አቶ በቴ ኡርጌሳ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት አስፈላጊ የሚባሉ የምርጫ ዝግጅቶችን ተንቀሳቅሰው ማከናወን እንዳልቻሉ ተናግረዋል።ኦነግ የገጠመው ውስጣዊ መፈረካከስም በራሱ በብልጽግና ፓርቲ ጣልቃ ገብነት የተፈጸመ ነው የሚል ዕምነት እንዳላቸውም ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።ብልፅግና የራሱን ከፍተኛ አባላት ከማዕከላዊ አባልነት ሲያግድ ማንም በጸጋ ነው የተቀበለው እኛ በፖርቲያችን ውስጥ ያንን ውሳኔ ስንሰጥ ግን ማንም ሊያከብርልን አልቻለም ብለዋል፡፡ይህም ፓርቲያችን አላስፈላጊ ችግር ውስጥ ለመግባቱ ዋናው ምክንያት መሆኑን አቶ በቴ ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ ጦር ሀይሎች የሚገኘው የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሜቲ ፅህፈት ቤት በፖሊስ መጠበቅ ከጀመረ ስድስት ወራት እንዳለፈውም ተናግረዋል።በዚህ ሁኔታ ስራችንን መስራት አንችልም በአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የፖርቲው ሀላፊዎችና አባላት እየታሰሩ የምናስመዘግበው እጩ የለንም ብለዋል።እጩ ካላስመዘገባችሁ በምርጫው ላትወዳደሩ ትችላላችሁ? ብሎ ጣቢያው ላነሳላቸው ጥያቄ ግን እኛ ምርጫ አንሳተፍም አላልንም ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

የኦሮሚያ ክልል ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ምክትል ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ግዛቸው ገቢሳ ኦነግ ባነሳው ጥያቄ ዙሪያ ምላሽ እንዲሰጡ ጣቢያው ጠይቋል።እሳቸው እንዳሉትም ታሰሩ የተባሉት ሰዎች እንደ ግለሰብ በሰሩት ወንጀል ተጠርጥረው አንጂ በኦነግ አባልነታቸው አይደለም ብለዋል።ማንም ሰው በህግ ፊት እኩል ነው ያሉት አቶ ግዛቸው ከቀበሌ ጀምሮ ያሉ 646 የብልጽግና አመራሮች ህግ በመተላለፋቸው ታስረዋል ብለዋል።ከምርጫ ጋር ተያይዞ በኦሮሚያ ክልል የሚወዳደሩ ሁሉም ፓርቲዎች ጽህፈት ቤታቸውን ከፍተው እየተንቀሳቀሱ ነው የክልሉ መንግስትም ድጋፍ እያደረገ ነው ብለዋል።

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
12.8K views11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-12 14:43:08
የገበያ ዋጋ መረጃ የሚሰጥ ድረ-ገጽ አገልግሎት ላይ ዋለ!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ከአዲስ አበባ ከተማ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ኤጀንሲ ጋር በትብብር ለህብረተሰቡ ዕለታዊ የገበያ ዋጋ መረጃ የሚሰጥ አዲስ ድረ-ገፅ ይፋ አድርጓል፡፡

ድረ-ገጹ በከተማዋ ያሉ የገበያ ማዕከላትን በማስተሳሰር በተለይ ሸማቹ ማህበረሰብ ቀጥታ በተንቀሳቃሽ ስልክ እና ሌሎች የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም መረጃዎችን በማግኘት ግብይት ማድረግ ያስችላል ተብሏል።

በተጨማሪም የምርት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማወቅ፣ በምርቶች የተጋነነ ዋጋ ጭማሪን ለመለየት እና ሸማቹ ህብረተሰብ በየትኛው የገበያ ስፍራ በምን አይነት ምርት በምን ዋጋ እንደሚሸጥ ካለበት ሆኖ ለማወቅ እንደሚያስችል ተነግሯል፡፡

"www.aaminfo.gov.et" በሚል ይፋ የተደረገው የመረጃ ድረ-ገጽ ከ28 በላይ የገበያ ማዕከላት ጋር የተሳሰረ ነው፡፡

[Addis Zeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
15.2K views11:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-12 14:35:18
በትግራይ ድጋፍ ለማድረግ ላመለከቱ 75 የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ፈቃድ ተሰጠ!

ባለፉት 3 ወራት በተለያዩ ጊዜያት በቦታው ተገኝተው ድጋፍ ለማድረግ ላመለከቱና አለም አቀፍ መመዘኛውን አሟልተው ለተገኙ 75 የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ወደ ትግራይ ክልል በመግባትና የሰብዓዊ ድጋፍ ሂደቱን እንዲያግዙ ፈቃድ ተሰጥቷል።

የሰላም ሚኒስቴር በትግራይ ክልል የሰላም ማስከበር ሂደቱን ተከትሎ በክልሉ ላለፉት 3 ወራት የተባበሩት መንግስታት ልዩ ልዩ ድርጅቶችን ጨምሮ ከ26 በላይ አለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በጥምረት የሰብዓዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ተግባራትን ለማገዝ ሰፊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።

የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ድጋፍ አስተባባሪ የኢትዮጵያ ጽህፈት ቤት በአስቸኳይ ጊዜ ማስተባበሪያ ማዕከል በምክትል ሰብሳቢነት የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፉንና የመልሶ ማቋቋም ሂደቱን የማስተባበር ሂደቱን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በቅንጅት እያስተባባረ እንደሚገኝ ከሰላም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

@YeneTube @FikerAssefa
14.9K views11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ