Get Mystery Box with random crypto!

🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ wektawi_merej — 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ wektawi_merej — 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @wektawi_merej
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.68K
የሰርጥ መግለጫ

This is national and international News and advertising channel
🇪🇹🇪🇹🇪🇹"ስለኢትዮጲያ ሳትሰማ ያሳለፍከው ቀን እንደባከነ ይቆጠራል" 🇪🇹🇪🇹🇪🇹
⏭▶️➡️ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ዜናዎችን በፍጥነት ይደርሶታል።🔚

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-11-14 14:01:02
ለአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የኮማንደርነት ማዕረግ ተሰጣት

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ለአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ልዩ የኒሻን ሽልማት እና የኮማንደርነት ማዕረግ አበርክቶላታል፡፡

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በተሰማሩበት የሥራ መስክ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ 78 የኮሚሽኑ ስፖርት ክለብ አባላት የማዕረግ፣ የገንዘብና የልዩ ኒሻን ሽልማት አበርክቷል፡፡

በሽልማት ፕሮጋራሙ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ልዩ የኒሻን ሽልማት የተበረከተላት ሲሆን በኮሚሽኑ የኮማንደርነት ማዕረግም ተሰጥቷታል፡፡

ኮማንደር አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በተሰጣት ሽልማት መደሰቷን ገልጻ በማረሚያ ቤት ስፖርት ክለብ ትንሽ ልጅ ሆና በመቀጠር አሁን ለደረሰችበት ደረጃ መብቃቷንም አንስታለች፡፡

ሽልማቱ የማረሚያ ስፖርት ክለብ ወጣት አትሌቶች ጠንክረው እንዲሰሩ፣ እንዲበረታቱና የተሻለ ደረጃ እንዲደርሱ ያደርጋል ያለችው አትሌቷ በተለያዩ የውድድር መስኮች የኮሚሽኑ አትሌቶች ውጤታማ መሆናቸውን ገልፃለች፡፡

ኮሚሽኑ ለ34 ስፖርተኞች ከረዳት ሳጅን እስከ ኮማንደር ድረስ የማዕረግ ዕድገት ሲሰጥ ለ19 ስፖርተኞች ደግሞ የገንዘብ እና ለ13 ስፖርተኞች የእርከን ጭማሪና የገንዘብ ሽልማት ሰጥቷል፡፡

ለአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የተበረከተው ልዩ የሜዳሊያ ሽልማት ከረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ቀጥሎ ለ2ኛ ጊዜ መሆኑን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
1.3K views11:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-13 17:11:46 የህወሓት መግለጫ ዓላማው ምንድነው

በሴራ ሠላምን ማደናቀፍም ይሁን ኢትዮጵያን ማሸነፍ ከቶም አይቻልም ህወሓት የናይሮቢው የፊርማ ሥነ ሥርዓት እንደተከናወነ በማህበራዊ ትስስር ገፆቹ "ስምምነቱን አልፈረምኩም" የሚል መግለጫ አውጥቷል። በዚህም "የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ በደቡብ አፍሪካው ስምምነት ህወሓትን ወክሎ የሄደ አካል የለም፤ ስምምነቱ ላይ የህወሓት ታጣቂ ትጥቅ ይፈታሉ ተብሎ የተገለፀውም ህወሓት ጦር የሌለው መሆኑን ለዓለም ህዝብና ለአጋሮቻችን እንገልፃለን፤ በአጠቃላይ ሰላም መምጣቱን ግን እንደግፋለን" ይላል። አስቂኝ የጅል ቀልድ የሚመስል፣ ግን ህወሓትን መሰሪነት የሚያንፀባርቅ ተረክ ይመስለኛል

ህወሓት በአንድ በኩል የሠላም ስምምነቱን ተቃውሞ "እኔ አልፈረምኩም" እያለ፤ በሌላ በኩል ደግሞ "ሠላምን እንደግፋለን" የሚል የለበጣ ዲስኩር አስነብቧል። እዚህ ላይ የሚመለከታቸው አካላት ጥንቃቄ ማድረግ ያለባቸው ይመስለኛል። ያም ሆኖ፣ በበኩሌ የዚህ መግለጫ ዓላማ ሶስት ጉዳዩችን ለማሳካት ያለመ  ይመስለኛል። እነርሱም፦

1ኛ) የሠላም ስምምነቱን የማይፈልጉ ወገኖች እንዳሉ አስመስሎ በማቅረብ፤ በስምምነቱ መሠረት ወደፊት የሚከናወኑ ጉዳዩች ላይ ተፅዕኖ በማሳረፍ እንቅፋት የመፍጠር ፍላጎት፤

2ኛ) የስምምነቱ ፈራሚዎች የፓርቲያችን አባልላት ስላልሆኑ ስምምነቱ አይመለከተንም የሚል ጥርጊያ መንገድ የመክፈት ፍላጎት፤

3ኛ) በህወሓት በኩል ጦርነቱን የመቀጠል ፍላጎት እንዳለ በማስመሰል የሚፈልጉትን ነገር ለማስፈፀም ውስጣዊ ሸፍጥ መኖሩን የሚያሳይ ነው

በርግጥ እንዲህ ዓይነቱ መግለጫ፤ የሠላም ስምምነቱ ጥቅማቸውን ሊነካባቸው የሚችሉ አካላት ሊያቀናብሩት ይችላሉ። ሆኖም ፈራሚዎቹ እነ ጌታቸው ረዳ እጃቸው እንደሌለበት ርግጠኛ መሆን አይቻልም። ምክንያቱም በትናንትናው ዕለት ክንደያ ገ/ሕይወት የሚባለውና የመግለጫውን ዓይነት ሐሳብ የሚያራምደው የህወሓት ከፍተኛ አመራርን ትዊት፤ ጌታቸው የሠላም ስምምነቱን ትቶ ሼር አድርጎ በትዊተር ገፁ ሲያሰራጭ ነበር። ለማንኛውም መንግሥት ከዜጎች የተሻለ መረጃ ቢኖረውም፤ እኔም ከዚህ በኋላ ሊኖሩ የሚችሉ ሸፍጦችን በጥንቃቄ መመልከት እንደሚገባ እንደዜጋ ሐሳቤን ለመግለፅ እወዳለሁ። ያም ሆኖ፣ የቱንም ያህል የተቀነባበረ ሸፍጥና ሴራ ቢኖር፤ የተፈረመውን የሠላም ስምምነት ማደናቀፍም ይሁን ኢትዮጵያን ማሸነፍ ከቶም እንደማይቻል ህወሓትም ሆነ የትኛውም ቡድን ወይም አካል ማወቅ አለበት

የኢትዮጵያ ሠላም፣ ሉዐላዊነትና የግዛት አንድነት በልጆቿ ፈርጣማ ክንድ ፀንቶ ይኖራል
ሠላም ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ይሁን

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
1.9K views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-13 17:11:19
1.8K views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-13 02:04:30
#Update

ዛሬ በናይሮቢ #በተፈረመው_ስምምነት መሰረት ፤ በሚቀጥሉት 7 ቀናት ወታደራዊ ሀላፊዎቹ ለወታደሮቻቸው ኦረንቴሽን እንደሚሰጡና ከዛም የፌደራል ባለስልጣናት በትግራይ ኃላፊነታቸውን እንደሚረከቡ ይገልፃል።

የከባድ መሳርያዎች ትጥቅ አፈታትም በትግራይ ክልል ያሉ የውጭ ኃይሎች እና ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ ያሉ ኃይሎች ከክልሉ መውጣት ጋር በአንድ ግዜ እንደሚፈፀም ይገልጻል።

የቀላል መሳርያዎች ትጥቅ አፈታትን ለማሳለጥ ከሁለቱም ወገን የተውጣጣ ኮሚቴ እንደሚቋቋምም የስምምነት ሰነዱ ላይ ሰፍሯል።

(Credit : ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
1.4K views23:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-12 21:06:00
#Update

ዛሬ በናይሮቢ #በተፈረመው_ስምምነት መሰረት ፤ በሚቀጥሉት 7 ቀናት ወታደራዊ ሀላፊዎቹ ለወታደሮቻቸው ኦረንቴሽን እንደሚሰጡና ከዛም የፌደራል ባለስልጣናት በትግራይ ኃላፊነታቸውን እንደሚረከቡ ይገልፃል።

የከባድ መሳርያዎች ትጥቅ አፈታትም በትግራይ ክልል ያሉ የውጭ ኃይሎች እና ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ ያሉ ኃይሎች ከክልሉ መውጣት ጋር በአንድ ግዜ እንደሚፈፀም ይገልጻል።

የቀላል መሳርያዎች ትጥቅ አፈታትን ለማሳለጥ ከሁለቱም ወገን የተውጣጣ ኮሚቴ እንደሚቋቋምም የስምምነት ሰነዱ ላይ ሰፍሯል።

(Credit : ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
1.9K views18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-12 16:58:45
FIB ቴሌቪዥን በድንገት ሰራተኞቹን በተነ
የፊንፊኔ ኢንተግሪቲድ ብሮድካስት(fib) ከተመሰረተ 3 አመታትን ቢያስቆጥርም አሁን ላይ ድርጅቱ ሰራተኞቹን በትኖ ከሀገር መዉጣቱ ተረጋግጧል ።
ከዚህ በፊት በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወር እንደነበረዉ በድርጅቱ እና በሰራተኞቹ መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ እንደነበር ይታወሳል ።
ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
1.4K views13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-12 11:13:47
የእንግሊዝኛ ቋንቋን
ያለምንም የበይነ መረብ ክፍያ ለመማር

#Ethiopia | የእንግሊዝኛ ቋንቋን ያለምንም የበይነ መረብ ክፍያ ለመማር የሚያስችል መማሪያ  የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የኢትዮ-ቴሌ ኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ በተገኙበት ይፋ ሆኗል

መማሪያው በትምህርት ሚኒስቴር የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች የተዘጋጀ ሲሆን ከተማሪዎችና መምህራን በተጨማሪ ሁሉም የማህበረሰብ አካል ሊጠቀምበት እንደሚችል ተጠቁሟል

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ መተግበሪያው በትምህርት ቤቶች የሚሰጠውን የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት የበለጠ በማጠናከር በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ የተማሪዎችን የመረዳት አቅም ለመገንባት ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል

ፕሮፌሰሩ ከዚሁ ጋር አያይዘው እንደገለጹት የሀገራችን የትምህርት ስርአት ከሰባተኛ ክፍል ጀምሮ የመማሪያና ማስተማሪያ ቋንቋ በአብዛኛው እንግሊዝኛ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ተማሪዎች ትምህርታቸውን በአግባቡ ለመረዳት የሚገጥማቸውን ችግር ለማቃለል እየተሰራ ነው ብለዋል

ከተለያዩ ሀገራት በጎ ፈቃደኛ  የእንግሊዘኛ መምህራንን  እና የዲያስፖራ አባላትን  ወደ ሀገር ቤት በማስመጣት በትምህርት ቤቶች ውስጥ ለማሰማራት ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን የጠቀሱት ፕሮፌሰር ብርሃኑ መተግበሪያው ይፋ መሆኑ ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል ብለዋል

የስራ አስፈጻሚ ፍሬ ህይወት ታምሩ በበኩላቸው ትውልድን የመገንባት ሃላፊነት የጋራ በመሆኑ መማሪያው ያለምንም የበይነ መረብ ክፍያ አገልግሎት ላይ እንዲውል ማድረጋችን ማህበራዊ ሃላፊነታችንን የምንወጣበት አንዱ ማሳያ ነው  ብለዋል
ተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም ቀሪው የማህበረሰብ ክፍል የእንግሊዝኛ ቋንቋን ለመማርና ለማሻሻል እንዲጠቀምበት ጥሪ መቅረቡን ከሚኒስቴሩ የማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል
@wektawi_Merej
2.1K views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-12 07:40:28
#UPDATE ላለፉት ጥቂት ቀናት በናይሮቢ ሲካሄድ የነበረው ውይይትን ተከትሎ በነገው እለት 5 ሰአት ገደማ በዝርዝር ስምምነት ነጥቦቹ ላይ ፊርማ እንደሚያኖሩ የታወቀ ቢሆንም ከህወሓት መንደር ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ብዙዎች የተከድተናል ቅስቀሳው ከትላንት ጀምሮ እየተጎሰመ ይገኛል።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
2.3K views04:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-11 18:14:01 ፖለቲከኛ ጀዋር መሐመድ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የሰጠው አስተያየት እንደሚከተለው በአማርኛ በፋስት መረጃ ይቀርባል።
#FastMereja
እውነት ለመናገር ባለፉት አራት አመታት የተገደሉት የኦሮሞ ልጆች ቁጥር በወያኔ እና በደርግ ዘመን ሁለቱ ተደምረው የአሁኑ ይበልጣል። ዛሬ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀያቸው ተፈናቅለው በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይገኛሉ። ኦሮሚያን ለማልማት የተማሩ ወጣቶች ታጥቀው እርስ በርስ እየተገዳደሉ ነው። ይህ ለመናገር የሚሳፍር ነው።

ዛሬም እንደትናንቱ እንጮሃለን፣ የዚህ ጦርነት መነሻ የፖለቲካ ግጭት ነው። በውይይት እንጂ በመድፍ አይፈታም። በሰሜን እንዳየነው ይህ ጦርነት የቱንም ያህል ቢቆይ በድርድር ይጠናቀቃል። ለማይቀር ነገር ደሆችን አትጨርሱ።

በሰሜን ያለውን የኢትዮጵያን ችግር በሰላማዊ መንገድ እንፈታዋለን በኦሮሚያ ያለው በጦር እናስወግደዋለን ማለት ራስን ማታለል ነው። የቤቱን አንድ ጎን በማቃጠል ከሌላው ጎን መስራት የማይሆን ነገር ነው።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
1.7K views15:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-11 10:52:01
ኢራን ለመጀመሪያ ጊዜ ሀይፐር ሶኒክ ሚሳይል መስራቷን ገለጸች

ኢራን ሀይፐር ሶኒክ ባሊስቲክ ሚሳይል በኢራን የአብዮተኞች ጥበቃ እንደተሰራ የተገለፀ ሲሆን፤ አዲሱ ሚሳኤል ፍጥነቱ ለእይታ አስቸጋሪ እና ከድምጽም በላይ እንደሆነ ተናግረዋል።

በአየር ላይ የሚደርሱ ማናቸውንም ጥቃቶች መፈጸም ያስችላል የተባለለት ይህ ሚሳኤል በኢራን የትውልድ ታሪክ አዲስ መሆኑን በእስላሚክ አብዮተኞች ጥበቃ ኮርፖሬሽን የኤሮ ስፔስ ሀላፊ ጀነራል አሚር አሊ  ጠቁመዋል።

ከድምጽ አምስት እጥፍ ፍጥነት እንዳለው የተገለጸው ይህ ሀየፐር ሶኒክ ሚሳኤል በሰው ልጅ መደበኛ እይታ ውስጥ መለየት እንደማይቻል እና መትቶ መጣል የማይቻል እንደሆነም ተገልጿል።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
358 views07:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ