Get Mystery Box with random crypto!

🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ wektawi_merej — 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ wektawi_merej — 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @wektawi_merej
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.68K
የሰርጥ መግለጫ

This is national and international News and advertising channel
🇪🇹🇪🇹🇪🇹"ስለኢትዮጲያ ሳትሰማ ያሳለፍከው ቀን እንደባከነ ይቆጠራል" 🇪🇹🇪🇹🇪🇹
⏭▶️➡️ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ዜናዎችን በፍጥነት ይደርሶታል።🔚

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2022-10-04 18:07:13 በአዲስ አበባ ከተማ ከ22 ሺህ በላይ ኩንታል ሲሚንቶ በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር ተያዘ

ተግባራዊ የተደረገው የሲሚንቶ ግብይት መመሪያ ከሚፈቅደው ውጪ በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ 22 ሺህ 293 ኩንታል ሲሚንቶ ተይዞ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ፡፡

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እየተስተዋለ ያለውን የሲሚንቶ ዋጋ ንረት ለመግታት የሲሚንቶ ግብይት መመሪያ ቁጥር 908/2014 አውጥቶ በመላው ኢትዮጵያ ተግባራዊ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

የመመሪያው ዓላማ፡- በረጅም የግብይት ሰንሰለት አማካይነት ያለአግባብ እየናረ ያለውን የሲሚንቶ ዋጋ ለማስቀረት ብሎም በሀገራዊና ማህበረሰባዊ እድገት ላይ ፋይዳ ያላቸው የግንባታ ፕሮጀክቶች እንዳይስተጓጎሉና ቅድሚያ እንዲያገኙ ለማድረግ ነው፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ንግድ ቢሮ ኃላፊ አቶ አደም ኑሪ፥ በተደረጉ የቁጥጥር ስራዎች 22 ሺህ 293 ኩንታል ሲሚንቶ በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር ተገኘቶ እርምጃ ተወስዷልል ነው ያሉት፡፡

ከዚህ ውስጥም 15 ሺህ 179 ኩንታሉ ተወርሶ መሸጡንም ከንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በተጨማሪም 2 ሺህ 226 ኩንታሉ ተጣርቶ ህጋዊነቱን የሚያረጋግጡ መረጃዎች ተሟልተው ሲለቀቅ፥ ቀሪው መንግስት በተመነው ዋጋ መሸጡ ነው የተገለጸው፡፡

የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን፣ የውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን፣ የሜጋ ግንባታ ፕሮጀክቶች ጽ/ቤት፣ የመንገዶች ባለስልጣን እና የዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ቢሮ ሲሚንቶ ቀጥታ ከፋብሪካዎች ገዝተው እንዲጠቀሙ በመመሪያው ተፈቅዶላቸዋል፡፡

ከነዚህ ውጪ ላለው የከተማዋ የሲሚንቶ ፍላጎት ከፋብሪካዎች በመረከብ በችርቻሮና በጅምላ የሚያቀርቡት የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት (ኢግልድ) እና የንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን ብቻ መሆናቸውም ነው የተጠቀሰው፡፡

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
@wektawi_Merej
1.1K views15:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 11:11:37
አዲስ አበባ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች አሸባሪው ህወሓትን የሚያወግዝ ሰልፍ አካሄዱ

አዲስ አበባ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች አሸባሪው ህወሓትን የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።

ሰልፈኞቹ መነሻቸውን ከ6 ኪሎ በማድረግ ወደ አሜሪካ ኤምባሲ በማቅናት እና የተለያዩ መፈክሮችን በመያዝ ነው አሸባሪው ህወሓትን የተቃወሙት።

“ህወሓት አሸባሪ ነው ህወሓት የትግራይ ወጣቶችን እና ሕፃናትን ወደ ጦርነት መማገድ መቀጠሉን እናወግዛለን፤ መንግሥት ለሰላም የዘረጋውን አማራጭ በመተው የጀመረውን ሦስተኛ ዙር ጦርነት እናወግዛለን” የሚሉት አሸባሪው ህወሓት ላይ ከተሰሙ ድምፆች መካከል ናቸው።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
@wektawi_Merej
3 views08:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 23:29:21
የህወሓት ጉጀሌ ጀኬ እንደ ሌሎች ምሽጎቹ ሁሉ የግራ ካሱን ተራራ ምሽጎች ሲመካባቸው ቆይቷል። ትናንት15 ኪሎሜትር የሚዘልቅ ምሽጉ እንደተሰበረው ሁሉ፤ በአንበሳዎቹ የኢትዮጵያ ልጆች የግራ ካሱ ተራራ ምሽጎቹም የባንዳው ህወሓት ወያኔ ጉጀሌ ጀሌ በሪያ ሆነው ድርምስምሳቸው መውጣቱ አይቀሬ ነው:: በአሁኑ ሰዓት ግራካሱ የመሸገው የህወሓት ወያኔ ግብስብስ ጀሌ ከየአቅጣጫው "እግዚኦ!" የሚያስብል መዓት እየወረደበት ነው

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
@wektawi_Merej
418 views20:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 22:57:20
የህወሃት መሸነፍን የማትወደው አሜሪካ አምባሳደር ማይክ ሐመርን ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ልትልክ ነው።

አሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመርን ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ልትልክ መሆኑን ዛሬ መስከረም 23፣ 2015 ምሽት በውጭ ጉዳይ መልሪያ ቤት በኩል አስታውቃለች።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
@wektawi_Merej
587 views19:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 11:42:37 የሆራ ሀርሰዴ ኢሬቻ በዓል በሰላም ተከብሮ ተጠናቀቀ - ፖሊስ
*******

በቢሾፍቱ ከተማ የተከበረው የሆራ ሀርሰዴ ኢሬቻ በዓል ባማረ እና በደመቀ መልኩ ባህላዊ ሥርዓቱን ጠብቆ በሰላም መጠናቀቁን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

የሰላም እና የፍቅር እንዲሁም የወንድማማችነት መገለጫ የሆነው የኢሬቻ በዓል ሥርዓቱን እና እሴቱን በጠበቀ መልኩ አጊጦ በሰላም እንዲከበር ሚናቸውን ለተወጡ የበዓሉ ታዳሚዎች፣ የፀጥታ ኃይሎች እና የአካባቢው ማኅበረሰብ ፖሊስ ምስጋናውን አቅርቧል።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
@wektawi_Merej
2.1K views08:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-01 19:18:13 ፈተና የሚሰጥበት የጊዜ ሠሌዳን ይፋ አደረገ
#Ethiopia | የዘንድሮው የ12ኛ ከፍል መልቀቂያና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሠሌዳ የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል።

በዚህ መሠረት በመጀመሪያ ዙር የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች ከመስከረም 26 እስከ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ተፈታኞች ወደ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገቡ ሲሆን÷ መስከረም 29 ቀን 2015 ዓ.ም ኦሬንቴሽን ይሰጣል፡፡

ከመሰከረም 30 እሰከ ጥቅምት 2 ቀን 2015 ፈተና ይሰጣል፤ ጥቅምት 3 እና 4 ቀን 2015 ዓ.ም ተፈታኞች ወደየአካባቢያቸው ይመለሳሉ።

በሁለተኛው ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ።

በዚህም ጥቅምት 5 እና 6 ቀን 2015 ዓ.ም ተፈታኞች ወደ ዩኒቨርስቲ ይገባሉ፤ ጥቅምት 7 ቀን 2015 ዓ.ም ኦሬንቴሽን ለተፈታኞች ይሰጣል።

ከጥቅምት 8 እሰከ 11 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ፈተና የሚሰጥ ሲሆን፥ ከጥቅምት 12 እና 13 ቀን 2015 ተፈታኞች ወደየአካባቢያቸው እንደሚመለሱ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
@wektawi_Merej
3.2K views16:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-01 13:35:44 የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በአል በደመቀና ባማረ ሁኔታ የገዳ ስርአቱን በጠበቀ መልኩ በሰላም መከበሩን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ

ለበዓሉ በሠላም መከበር የድርሻቸውን ለተወጡ አካላት በሙሉ ግብረ ኃይሉ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡አባ ገዳዎች ፣ ሀዳ ስንቄዎች ፣የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ፣ ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የመጡ እንግዶች እንዲሁም የውጪ ሀገር ቱሪስቶች የታደሙበት የ2015 ሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል በሰላም እና በልዩ ድምቀት መከበሩን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡የፀጥታ አካላት ለወንጀልና ትራፊክ አደጋ መከላከልና ምርመራ ተግባራት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት አባላትንና አመራሮችን በመመደብ እና በተለይም ህብረተሰቡን አጋዥ በማድረግ ባከናወኗቸው ተግባራት በዓሉን በሰላም ማክበር ተችሏል፡፡

የከተማችን ነዋሪዎች ፣ የበዓሉ አስተባባሪዎች ፣ በየእርከኑ የሚገኙ የአስተዳደር አካላት የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የመጡ እንግዶችን በወንድማማችነትና በእህታማማችነት መንፈስ በማስተናገድ ካከናወኑት ተግባር ባሻገር ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በመቀናጀት ለበዓሉ ሰላማዊነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ በማበርከታቸው እንዲሁም መላው የፀጥታ አካላት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ኃላፊነታቸውን በብቃት በመወጣታቸው በአሉ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንደተከበረ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ አስታውቋል፡፡

የበዓሉ በሰላም መከበር የከተማችንን መልካም ገፅታ ለመገንባት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ግብረ ኃይሉ አስታውሶ በዓሉ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንዲከበር የድርሻቸውን ለተወጡ አካላት እንዲሁም ድካማቸውን ተቋቁመው ኃላፊነታቸውን በትጋት ለተወጡ መላው የፀጥታ አካላት አባላትና አመራሮች ግብረ ኃይሉ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡

በአሉ የሰላምና የደስታ እንዲሆን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብር ኃይል በድጋሚ መልካም ምኞቱን እየገለፀ መስከረም 22 ቀን 2015 ዓ/ም በቢሾፍቱ የሚከበረው የሆራ አርሰዲ የኢሬቻ በአል በተመሳሳይ በሰላም እንዲከበር ህብረተሰቡ ለፀጥታ አካላት የሚያደርገውን እገዛ አጠናክሮ እንዲቀጥል የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል መልእክቱን አስተላልፏል፡፡

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
@wektawi_Merej
3.4K views10:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 12:17:29
አሜሪካ ሱዳንን አስጠነቀቀች

በሱዳን የአሜሪካ አምባሳደር ጆን ጎድፍሬይ ፤ ካርቱም ሩሲያ በቀይ ባህር ዳርቻ የጦር ሰፈር እንድትመሰርት ከፈቀደች ከባድ መዘዝ እንደሚኖረው አስጠንቅቀዋል።

ከ25 ዓመታት በኋላ በሱዳን የመጀመርያው የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑት ጎድፍሬይ እንዲህ ዓይነት ውሳኔ ሱዳንን ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ መነጠል ብቻ ሳይሆን ጥቅሟን የሚጎዳ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።

አምባሳደር ጎድፍሬይ ከሱዳን አል ታይያር ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ፤ "ሩሲያ በቀይ ባህር ላይ የጦር ሰፈር ለመመስረት እ.ኤ.አ. በ2017 ከስልጣን ከተወገዱት ፕሬዝዳንት ኦማር አልበሽር ጋር የተፈራረመችውን ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ እየሞከረች ነው የሚሉ አንዳንድ ሪፖርቶች አሉ"  ብለዋል።

አልበሽር ለወራት የዘለቀን ተቃውሞ ተከትሎ ከስልጣን የተወገዱት በሚያዝያ 2019 እንደነበር ይታወቃል።

የአሜሪካው ዲፕሎማት " የሱዳን መንግስት የጦር ሰፈሩ (የሩስያ) እንዲቋቋም እንዲቀጥል ከወሰነ ወይም እንደገና ለመደራደር ከወሰነ ለሱዳን ጥቅም ጎጂ ነው " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

" ሁሉም አገሮች ከየትኞቹ አገሮች ጋር አጋር እንደሚሆኑ የመወሰን ሉዓላዊ መብት አላቸው " ያሉት አምባሳደሩ " ነገር ግን እነዚህ ምርጫዎች በእርግጥም መዘዝ አላቸው " ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል።

እንደ ዲፕሎማቱ ገለጻ አሜሪካ በሱዳን አዲስ በሲቪል የሚመራ መንግስት እና ሀገሪቱን ወደ ዲሞክራሲያዊ ጎዳና የሚመልስ የሽግግር ማእቀፍ ለማየት ትፈልጋለች።

እ.ኤ.አ ህዳር 2017 ሱዳን እና ሩሲያ በወታደራዊ ስልጠና፣ የልምድ ልውውጥ እና የጦር መርከቦችን ወደ ሁለቱ ሀገራት ወደቦች ለማስገባት የትብብር ስምምነቶችን ተፈራርመዋል።


ምንጭ፦ ሱዳን ትሪቢዩን

ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም

@wektawi_Merej
4.1K views09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 11:33:57
የአርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ የአስክሬን ሽኝት መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው

የአርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ የአስክሬን ሽኝት መርሐ ግብር ከመኖሪያ ቤቱ ጀምሮ እየተካሄደ ነው፡፡

ከአርቲስቱ መኖሪያ ቤት ጀምሮ እየተካሄደ ያለው የአስክሬን ሽኝት መርሐ ግብር÷ በመቀጠልም በወዳጅነት ፓርክ በመንግሥት ባለስልጣናት፣ በሙያ አጋሮቹ፣ በአድናቂዎቹ እና ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት የአስክሬን ስንብት ይካሄዳል።

የተወዳጁ አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ የቀብር ሥነ ስርአት በመንበረ ጸባኦት ቅድስተ ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል።

ተወዳጁ የጥበብ ሰው ማዲንጎ አፈወርቅ ስለ ፍቅር፣ ትዝታ፣ ባህል፣ ሀገር፣ ታሪክና ሌሎች ጉዳዮችን የሚዳስሱ መልዕክቶችን በተስረቅራቂ ድምጹ በማዜም በኢትዮጵያ የኪነጥበብ ስራ ላይ የራሱን አሻራ አሳርፏል።

ማዲንጎ አፈወርቅ ኢትዮጵያ በተፈተነችበት ወቅት እያመመው ግንባር ድረስ በመሄድና ማሰልጠኛም ምልምሎችን በማነቃቃት የራሱ የሆነ ታሪክ የሰራ አርቲስት መሆኑም ይታወቃል።

በቀድሞው የጎንደር ክፍለ ሀገር አዘዞ ተወልዶ በደብረታቦር ያደገው አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ መስከረም 17 ቀን 2015 ዓ.ም ህይወቱ ማለፉ ይታወሳል።


ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
@wektawi_Merej
675 views08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 00:14:00 የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማሻሻያ ተደረገ

የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማሻሻያ መደረጉን የንግድ እና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር ለኢቢሲ በላከው መግለጫ አስታወቀ።

በዚሁ መሠረት ከመስከረም 18 ቀን 2015 ዓ.ም እኩለ ሌሊት 6:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ የሚከተለው እንዲሆን ተወስኗል።

1. ቤንዚን በሊትር - 57 ብር ከ05 ሣንቲም
2. ነጭ ናፍጣ በሊትር - 59 ብር ከ90 ሣንቲም
3. ኬሮሲን በሊትር - 59 ብር ከ90 ሣንቲም ሲሆን

4. በሥራ ላይ የነበረው ዋጋቸው ባለበት የሚቀጥል የነዳጅ ውጤቶች

4.1. የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር - 76 ብር ከ87 ሣንቲም

4.2. ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር - 43 ብር ከ89 ሣንቲም

4.3. ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር - 43 ብር ከ06 ሣንቲም እንዲሆን ተወስኗል።

በሌላ በኩል አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በተረዘጋው የታለመ ድጎማ አሠራር ታቅፈው ሕዝቡን እንዲያገለግሉ የተመረጡት የሕዝብ ትራንስፖርት ተሽክርካሪዎች በሚጠቀሙት ነዳጅ ላይ በሁለተኛው ምዕራፍ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አልተደገረም።

እነዚህ ተሽከሪዎች በሐምሌ ወር በተወሰነላቸው ዋጋ ቤንዚን በብር 41.26 በሊትር እንዲሁም ነጭ ናፍጣን በብር 40.86 በሊትር እየገዙ እንዲቀጥሉ ብቻ ሳይሆን ከእጥፍ በላይ ያደገ ድጎማ ከመንግሥት እንዲያገኙ የተደረገ ስለሆነ በሚቀጥው ጊዜ ዋጋ እስኪሻሻል ድረስ በሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ምንም ዓይነት ጭማሪ አይደረግም ሲል ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ገልጿል።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
@wektawi_Merej
265 views21:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ