Get Mystery Box with random crypto!

ወግ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @wegoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 21.12K
የሰርጥ መግለጫ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @lula_al_greeko

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 34

2021-08-10 22:38:01 ናብ ከአልጋ አላላቅቅ ብሏት ተኝታለች። ሰዓቱን ስትመለከት ሶስት ሰዓት ገደማ ስለሆነ እንደምንም ብላ ተነስታ ወደ
ማርያም ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ሳያልቅ ለመድረስ ተጣድፋለች። በዚያ ላይ
ከልጆቿ መካከል አራቱን የወለደችው በባለወልድ ቀን ስለሆነ ለባለወልድ የተለየ ስሜት አላት። "አዬ የኔ ጉድ፣ ለዛውም በባለወልድ ቀን እንዲህ ላርፍድ?" እያለች ነጠላዋን ተከናንባ ከወጣቷ ልጇ ሚሚ ጋር አውራ መንገዱን ተሻግረው ወደ ማርያም የሚያስገባውን መንገድ ሲጀምሩ ከአንድ ግቢ ውስጥ የሚጮኹ፣ የሚንጫጩ፣ የሚተራመሱ ሰዎች ሲመለከቱ በድንጋጤ እየተጣደፉ ወደ ውስጥ ሲዘልቁ ሁለቱም በአይናቸው ያዩትን ማመን አልቻሉም…
÷÷÷

ይቀጥላል

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Tilahun abebe
6.2K viewsDAVE / PAPI, 19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-10 22:38:01 እውነት እብዱ ማነው?
(እውነተኛ ታሪክ)
#ክፍል አንድ

እነሆ… እውነት እብዱ ማን ነው…? ልክ የዛሬ ሶስት ዓመት በዕለተ ባለወልድ አጥቢያ (ሐምሌ 28 ለሐምሌ 29) ከሌቱ ስምንት ሰዓት ገደማ ጥቂት ቀሳውስት ለቅዳሴና ማህሌት ወደ ቤተክርስቲያኒቷ እየገቡ ሳለ አንደኛው ቄስ ከቅፅሩ ባሻገር የትኩስ ውልድ ሕጻን ልቅሶ ድምፅ ሰምቶ ቆም አለ፡፡ ‹‹ይሰማችኋል የሕጻን ልጅ ልቅሶ…›› አለ፡፡ ሌሎቹም ጆሮአቸውን ቀስረው ይሰማል የተባለውን ድምፅ ለመጋራት ቆም አሉ፡፡ እንዳለውም ወዲያው የሕጻን ድምጽ ልቅሶ በድጋሜ ሲሰማ እውነትም ከቤተክርስቲያኑ ቅፅር ጀርባ ከወደ መቃብር ቤቶቹ አካባቢ የሚሰማው ድምጽ በጉልህ የትኩስ ውልድ ሕጻን እንደሆነ አረጋገጡ። የሐምሌው ዝናብ እኝኝኝ… ማለቱን ከጀመረ ቆይቷል… ይበርዳል…!
ከየት ነው…? የማን ነው…? ተጥሎ ነው…? የምን ጉድ ነው…? ወዘተ የመሳሰሉ ጥያቄ እያመላለሱ ሳለ ከመሃከላቸው አንደኛው ትንግርቱን የሚፈታ መላ መታ፡፡ ‹‹እናንተ… ያቺ እብድ እኮ ነፍሰ-ጡር ነበረች… እሷ ወልዳ መሆን አለበት…›› አላቸው፡፡ ሌሎቹም የተሰጠውን መላምት ከግምት በላይ እርግጠኛ ሆነውበት ምንም ሳይነጋገሩ በጥቆማው ተግባብተው ድምጹ ወደሚሰማበት የቤተክርስቲያኑ ቅፅር ጀርባ እየተጣደፉ ዘለቁ፡፡ "ያቺ እብድ" የተባለችው ይቺ ሴት ግን ማን ናት…? መጀመሪያ እሷን በጥቂቱ ላስተዋውቃችሁ፡፡ ስሟ በሀገሬው ሕዝብ ዘንድ “እብዷ” ይባላል፡፡ በቃ ይሄ ነው መጠሪያዋ፡፡ ከጥቂት ዓመታት በፊት ምናልባትም ከሁለት ዓመት ገደማ በፊት ነው እዚህ ከተማ የተገኘችው፣ ወይም “አምጥተው የጣሏት” ይላሉ ነዋሪዎቹ፡፡ በነገራችን ላይ ለምን እንደሆነ ባይገባትም ከተማውን በደንብ የምታውቀው እህቴ እንደነገረችኝ ከሆነ ብዙ እብዶችን በመኪና እያመጡ እዚህ ከተማ መጣል የተለመደ ነገር ከሆነ ቆይቷል፡፡ “ለእብድ መኖሪያ የሚሆን ተመራጭ ከተማ…” የሚለው ግርምተ-ሃሳብ ውስጤ ተመላለሰ፡፡ አንዳች መልስ የማገኝለት ይመስል ሃሳቡ ለአፍታም ቢሆን ውስጤ መቆየቱ ለራሴ ፈገግ አሰኘኝና ተውኩት፡፡ ክረምት ይሁን በጋ፣ ቀን ይሁን ማታ፣ “እብዷ” እዚህ ከተማ ከታየችበት ቀን ጀምሮ እስካሁን እርቃኗን ነው የምትውለው፣ እርቃኗን ነው የምታድረው፡፡ አንዳንድ ደግ ሰዎች እንደምንም ብለው ልብስ ሲያለብሷት በደማቅ ፈገግታ ታጅባ ለጥቂት ደቂቃዎች ብቻ የለበሰችውን ልብስ እንደ አንዳች ትንግርት ዙሪያ ገባውን ትመለከተዋለች፡፡ ይገርማታል ያስቃታል…! ከዚያ ሰዎቹ ዘወር ካሉ በኋላ ወዲያው አውልቃ ትጥለውና የለመደችውን ነጻነት በድጋሜ ተጎናፅፋ መለ–መላዋን ትቀጥላለች፡፡ በየትኛውም ቋንቋ ቢያናግሯትና ቢጠይቋትም በጠያቂው ድምፅ ወይም ቋንቋ ወይም ንግግር ከመደመምና አጫ በረዶ የመሰለውን ጥርሷን ብልጭ እያደረገች ፈገግ ከማለት ውጪ መልስ የሚባል ነገር ሰጥታ አታውቅም፡፡ የማትናገረው በተፈጥሮዋ “መናገር የተሳናት” ሆና ይሁን ወይም “እብዷ” ካሰኛት
የአዕምሮ ጤና መታወክ የተነሳ አይታወቅም፡፡ በአጭሩ ከፈገግታ በቀር አትናገር አትጋገር አይነት ናት፡፡ “እብዷ” እዚህች ትንሽ የገጠር ከተማ ከመጣች ጀምሮ ሰው ተተናኩላ አታውቅም ይላሉ፡፡ የተወለደችበትን አካባቢ ወይም ነገደ-ቋንቋዋን የሚያውቅ የለም፡፡ የሚገምትም የለም፡፡ ቁመቷ ሎጋ፣ ቀለሟ ጥቁር የሚባል፣ ፀጉሯ ከርዳዳና አጭር፣ አፍንጫዋ ሰልከክ ያለ፣ ጥርሷ ድርድር ያለ ነጭ ነው፡፡ ይህ ነው ስጋዊ መገለጫዋ፡፡ ከዚህ ውጪ እሷ ማለት በቃ “እብዷ” ናት፡፡ እዚህች ትንሽ ከተማ “አምጥተው ከጣሏት” ጀምሮ እዚያችው ማርያም ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ገባ እየዋለች፣ በመረጠችው መቃብር ቤት እያደረች፣ ቀንም ሆነ ማታ እርቃኗን በመሆን በራሷ ዓለም መኖር ጀምራለች፡፡
አንድ ክፉ ቀን “ጤነኛ” የሚባል/የሚባሉ የሆነ አካባቢ ሰው/ሰዎች ነው/ናቸው
አሉ እስኪደፍራት/እስኪደፍሯት ድረስ…
በዚያም ሰበብ እስክትፀንስ ድረስ…
ለሐምሌ ባለወልድ አጥቢያ በድቅድቁ ጨለማ ራሷ ሽሏን እስከምትገላገል ድረስ…
÷÷÷
ቄሶቹ የሚሰሙትን የአራስ ሕጻን ልጅ ልቅሶ አቅጣጫ እየተከተሉ፣ ድምጹ ከሚመጣበት ቦታ አካባቢ ሲደርሱ እውነትም “እብዷ” እንደማንኛውም ውሎ
አዳሯ ሁሉ በዚያ በሐምሌ ጨለማ በሐምሌ ቁር… በሐምሌ ዝናብ… እርቃኗን በድቅድቁ ጨለማ ውስጥ ቆማለች፡፡ አይናቸውን አጥብበው በጣም ተጠግተው ሲመለከቷት ደግሞ ከደቂቃዎች በፊት እዚያው እመቃብር ቤቶች አካባቢ አምጣ የወለደቻትን ልጅ ለፈጣሪ መስዋዕትነት የምታቀርብ ይመስል፣ ሕጻኗን በአንድ እጇ ወደላይ ከፍ አድርጋ ይዛ እንደተለመደው ፈገግ ትላለች፡፡ የሕጻኗ እትብት ከሕጻኗ ሆድ ጀምሮ ወደታች እስከ እናትየው እግሮች መሃል ድረስ ይወዛወዛል፡፡ ከእናትየው መዳፍ ብዙም የማትተልቀው ሕጻን በዚያ ሐምሌ ቁር እና ዝናብ እየተቀጠቀጠች በእሪታ ትነዝራለች፡፡ [ቄሶቹ የፈጣሪን እና የቅዱሳንን ስም እየጠሩ ማማተባቸውና ማነብነባቸውን መገመት ቀላል ነው፡፡]
ቄሶቹ በወቅቱ ምን አስበው ይሁን መረጃው ባይኖርም፣ በወቅቱ የወሰኑት ውሳኔ ከቤተክርስቲያኗ ፊትለፊት የሚገኝ አንድ ግቢ አስገብተውና የግቢውን በር
ዘግተው መሄድ ነበር፡፡ ግቢው ደግሞ አንድ ደግ የአካባቢው ሰው ደካማ
አዛውንቶችን የሚያኖሩበትና የሚረዱበት ነው አሉ፡፡ ለማንኛውም ቄሶቹ እዚያ
ግቢ አስገብው ወደ ቅዳሴአቸው ሄደዋል፡፡ (እዚህ ጋር ቄሶቹ ያደረጉት ነገር መልካም ነው ብዬ ለማሰብ ተቸግሬአለሁ…)
÷÷÷
የሐምሌው ዝናብ ሌቱም አልበቃ ብሎት ንጋትም እንዲሁ ሲንዛዛ ስለ ነበር፣በግቢው ውስጥ የሚኖርና በጠዋት የተነሳ ማንም ሰው አልነበረም፡፡ ከጠዋቱ ወደ ሶስት ሰዓት ገደማ በግቢው ውስጥ ከሚኖሩት ተረጂ አዛውንቶች መካከል አንዳቸውን ለመጠየቅ መጀመሪያ ወደ ግቢው የዘለቀችው አንዲት ወጣት ልጅ
ነበረች፡፡ ልጅት ወደ ግቢው ስትገባ ዙሪያ ገባ ከሚገኙት ክፍሎች መካከል ከኩሽና
ያልተናነሰውና ክፍት ከነበረው አንደኛው ክፍል ደጃፍ ላይ "እብዷ" አንዳች በጭቃ ተጨማልቆ የተድበለበለ ነገር ይዛ ወደላይ እየወረወረችና እየቀለበች ስትጫወትበት ተመለከተች፡፡ ልጅት ያየችው ነገር ትንንሽ እጆችና እግሮች
ስላሉትና ከሆዱ ደግሞ አንዲት ትንሽዬ ቁራጭ የምትወዛወዝ ነገር ስላየች በጣም ደንግጣ ጩኸቷን አቀለጠችው፡፡
የተኛም ያልተኛም ከየቤቱ ወጥቶ ምን ሆንሽ ቢሏት…‹‹እብዷ… እብዷ… እብዷ…. የሆነ አውሬ መሰለኝ… የሆነ አውሬ ነገር ይዛ እየተጫወተችበት ነው…›› ብላ እየተንቀጠቀጠች በጣቷ ወደ “እብዷ”
ትጠቁማለች፡፡ ሰዎቹም እየተጣደፉ ቢጠጉ “እብዷ” አሁንም ፈገግታዋን እያጀበች ሌት በ8:00 ገደማ በወለደቻትና በጭቃ ስታንደባልላት ባደረችው ልጇ አሁንም ትጫወታለች፡፡ አሁን የሕጻኗ እትብት ከእናትየው ተለያይቶ ትንሽዬ የእትብት ቅሪት በሕጻኗ ሆድ ላይ ተንጠልጥላለች፡፡ ራሷ ነች አሉ በጥሳ የለየችው፡፡ በጭቃ ተለውሳ ከተጨማለቀችው ልጅ ምንም አይነት ድምፅ የለም፡፡ በግቢው የነበሩት ሰዎች ተረባርበው ልጅቷን ከእናትየው ነጥቀው መሬት ላይ አስተኝተው ይተረማመሳሉ፡፡
ግንባሯ ላይ ድፍት ያለው ፀጉሯ ፈረንጅ የሚያሰኛት… ከአንድ መዳፍ በላይ
የማትተልቅ አንዲት እፍኝ ሴት ሕጻን ልጅ ትኑር ትሙት ለማወቅ የሚሞክር
ጠፍቶ ሁሉም እርስበርሱ እንደተፈራራ የሆነች እራፊ ጨርቅ ላይ አስተኝተዋት
አሁንም ወዲህ ወዲያ ይዋዥቃሉ… ይጮሃሉ… ይንጫጫሉ… አንዱ ይገባል…
የሚያየውን ማመን አቅቶትና ዘግንኖት እየሮጠ ይወጣል… ሌላው የተፈጠረውን
ለመመልከት ወደ ግቢው እየሮጠ ይገባል… ሁሉም ወዲህ ወዲያ ይላል…
ዝናቡም እኝኝኝ… ይላል…
÷÷÷
አባዬ፣ አለወትሮዋ የጠዋቱ ብርድ እና ዝ
5.9K viewsDAVE / PAPI, 19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-10 21:47:11
#Sunsethiking is hosting a day hike to "DAMOCHA"

Damocha Mountain is an eroded volcanic crater with a jagged rim surrounding the valley floor far below. The valley features a drainage stream that comes out just to the right of the museum and provides an easy, well-worn route past the lower peaks that hide the real summit (from the vantage point of the park). This trail ends at a tiny mountain village.

Hiking Date :- Aug 15, 2021 (Nehase 9), 2013).

Hiking #Cost:- 675 ETB only

Departure: Piasa (Taitu Hotel)

Departure Time - 12:30 Am LT

Package includes
Transportation
Bottled water
Guide + scout
photography
Breakfast
lunch

NB.
Sanitizer & facemask mandatory!

walking hour: 5 hour (up to 20 km of walking)

suitable for: HARD, basic skill required

for more join the

channel @sunsethiking
@sunsetphotography

tickets available at
@Paappii ( +251922303747)
4.7K viewsDAVE / PAPI, 18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-10 21:45:52 ዜማና ሰውነት
[ግዕዝ፤አሃዱ]
ሰዎች"እንዴት ነው ሰብራህ የሄደችው ?" ብለው ሲጠይቁኝ " ልቤ እስከሚያነክስ" ብዬ ከመለስኩላቸው ረጂም ጊዜ ቢያልፍም ድንገት ቀና ስል የጠራ የመስከረም ሰማይ አይቼ ናፈቀችኝ ።
ለእንቁጣጣሽ በፈካ ቢጫ አደይ ያቆጠቆጠ አረንጓዴ መስክ ላይ ይሄን ብራ ሰማያዊ ሰማይ ደርበን የተራከብን ነን። በሚያሳሳ የመስከረም ቀን መኻል
አፍላነት ያቀጣጠለው፤ ነፋስ ስሞ ያበረደው ገላችን ላይ ጣል ያደረግነው፤ የተጋፈፍነው ሰማይን ነው። ሽቅብ ያየሁበትን አይኔን ቶሎ ሰበርኩ እንጂ ባተኩር ከጭኗ የተላቀቀ የጠይምነቷን ባዘቶ ጉም ሰርቶ አየው ነበር። ሁሉ እንደዛሬ ስላይደለ ልብ ብዬ ባየው ህመሙ ነፍሴ ላይ ያረብባል እንጂ። በልጅነት ቀናቷ ድንግል ልቧን እና ነፍሷን የገረሰስኩ ተቀዳሚ ግዕዟ ነኝ። ማለት የመጀመሪያውን መሳም የትኛውም መሳም እንደማይሽረው፤ የመጀመሪያው ዜማ ድንቅነት በሌሎች እንደማይሸፈነው፤ በልቧ ቅኝት ላይ ተደላድዬ የተፃፍኩ ማንም የማይሰረዘኝ ዜማዋ ነኝ። ለመጣ ለሄደው ሳትሰለች የምትነግረኝ ገድሏ ከአንደበቷ የምወጣ ብቸኛ ተረኳ መሆን ትምክተኛ አድርጎኝ፤ ልታቅፈኝ የዘረጋቻቸው እጆቿ አየር ላይ
እንደተንከረፈፉ ትቻት ስነጉድ፤ በማንም ያልተሳሙ ለጋ ከንፈሮቿ ሊስሙኝ ሲተጉ
ስገፋ ተስፋ ቆረጠችና ያልቃል ብዬ ያልገመትኩትን ለኔ ያላትን ፍቅር ለሌላ አጋርታ አገኘኹዋት። በኔ ግዕዟ ላይ እዝል ደርባ የምታዜም ሆነች። ፀፀት ልቤን ሲበላኝ እስከዛሬ ትምክህት የሸበበው አንደበቴን ከፍቼ እንደምወዳት
ነገርኳት። ሁለተኛ ፍቅሯ ከኔ እንደማይበልጥባት አውቃ ይሁን የዘመናት ህልሟ ስለሆንኩ ብቻ ግን መውደዴን ስነግራት ደስ አላት አቅፋኝ አለቀሰች። "ሁሌም አለሁልህ "አለችኝ።
ፍቅሬ በእኔ በግዕዟ እና በሁለተኛዋ እዝሏ ዜማ የምትንገላታ አሳዛኝ አራራይ
ሆነች። በዚህ ዜማ የታመምን ሶስት ሰዎች ነበርን። ከእርሱ ጋር አሸብሽባ
እንደምትመጣ እያወኩ በቅዳሴዋ ልዘምም ደፋ ቀና ስል ከጠይም ገላዋ ላይ የሚነሳ የእዝሏ ጠረን፣ ከሴትነቷ የሚተን የእርሱ ጢስ ዜማዬን እና አቋቋሜን ቢያዛባውም። በ"የኔ ነበረች፤ ሁሌም የኔ ነች። " እምቢተኝነት በቅኝት መኻል ሽብርክ የሚል ልቤን ታቅፌ ወረቧ ላይ ከርሚያለሁ። አሁን ይሄን እኔ እና እርሷ የተጋፈፍነውን የመስከረም ብራ ሰማይ ቀና ብዬ ባይ በተመሳሳይ ቀን እኔ ጋር ከመምጣቷ በፊት ከእዝሏ ጋር የነበራትን ወረብ በበራሪ ኮከብ እንደ ስዕል አስቀምጦ ያሳየኛል። ግን አይኔን አቅንቼ ሰማዩን ሳይ ትዝ ባለችኝ ቅፅበት አንገቴን መልሼ እጄን ደረቴ ላይ አጣምሬ የልቤ ድሪቶ ውስጥ ቀበርኳት። ቢሆንም እኔ ምንም የልቤ ስርቻ ውስጥ እንደመነኛ ልጥላት ብሞክር በእርሷ ልብ ውስጥ ግን ያለኝን ቦታ አውቃለሁ፤ ብዙ ሁለተኞች ያልሻሩኝ የሁሉ ነገር አሃዱዋ ተቀዳሚ ግዕዟ ነኝ። [እዝል፤ ተደራቢ]
ትዝ የምትለኝ በእኩለ ሌሊት ነቅቼ ሲጋራዬን ለኩሼ ያጨስኩ ቀን ነው። ከሁሉ ከሁሉ የምትወደው ከንፈሬን ነው። ከንፈሬ ላይ ባለችው ጥቁር ነቁጥ ሁሉ ሳትቀር ትቀና ነበር "ማርያም ለምን ሌላ ቦታ አልሳመችህም?" ብላ ታኮርፈኛለች። ሌሊት እንዳልቀሰቅሳት ተጠንቅቄ ተነስቼ ወንበር ስቤ ተቀምጬ
ሲጋራዬን ስለኩስ ከእንቅልፏ ትነቃለች። በቅጡ ያልተከፈቱ አይኖቿን ገርበብ
አድርጋ " ጭሱን ከአፍህ ልውሰድ?" ትለኛለች። ቀጥላ ከመኝታዋ ተነስታ ጭኔ
መሃል ትንበረከክ እና አጭሼ የምተነፍሰውን ጭስ ከአፌ አንደ ወፍ ትቀበላለች። የዛኔ ከንፈሮቻችን ተጋጥመው ቅጡ በማይገባን ወረብ ቆመን መወዛወዝ እንጀምራለን።
ሁሉም እንደሚያውቀው ከኔ ቀድሞ በገጠማት ዜማ ያልተደሰተች ዘማሪ ነች እኔ አፍላነቷ ጎትቶ ከቀሚሷ ስር ከገላዋ ላይ ያዋለኝ እዝሏ ተደራቢ ዜማዋ ነኝ።
አለ አይደል በግዕዝ የጋለ እሳቷን አቀዝቅዤ አረጋጋታለሁ። ቀልበ ቢስ ቀልቃላ እና ሃይለኛ ቅላፄዋን ዳብሼ ገርቼ እመልስላታለሁ። የመጀመሪያዋ ነውና ለግዕዟ ያላትን ስሜት በአንዴ አውጥተሽ ጣይ ባልላትም። በኔ እርጋታ አገግማለች። ፍቅር ከጀመርን ከጥቂት ጊዜ በኹዋላ በወረባችን መኻል የቀደመ ትትርናዋን ችላ ብላ ሁሉ ነገሯ ሲቀየርብኝ ግራ ገባኝ ። ቆይቼ አስቸጋሪ ግዕዟን አስጣልኳት ያልኳት እርሷ የቀደመ ቅላፄዋን ሳትተው በእኔ ላይ ደርባ ማዜም መጀመሯን አወኩኝ ። ይህን ሳውቅ እውነቱን በልቤ ደብቄ ሸፋች ልቧን ላረጋጋ ርቃኗን አስተኝቼ ከላይ እስከ ታች በከንፈሬ እየዳበስኩ በእንባዬ አርጥቤ አጠብኳት። እንዲህ ሳደርግ በሃይለኛ እና እምቢተኛ የሚማረክ እርሷነቷ ለኔ መለማመጥ
ትኩረት መስጠት ተሳነው። እናም ያኔ የጀመርነው ለስላሳ ቅኝት ዜማችን
ተቆራረጠ። አሁን ዛሬ ላይ ስለ እርሷ ሳስብ ሃዘን በልቤ ያልፋል ። በህይወቷ ከተጣባት ጠንካራ ግዕዝ ላሳርፋት የጣርኩ ለስላሳ እዝሏ ብሆንም እዚያና እዚህ የሚረግጥ አሳዛኝ አራራይ ነፍሷ ግን ያን እንድታደርግ አልፈቀደም። ከብዙ ጊዜ በኹዋላም ቢሆን እኔ ላይ ካደረገችው ክህደት ይልቅ ለቅብዝብዝ እርሷነቷ እና በዚህ ምክንያት ለሚበላሹ ዜማዎቿ የማዝን ተደራቢ ዜማዋ እዝሏ ነኝ። [አራራይ፤ አሳዛኝ] ሰዎች በሰራኹዋቸው ነገሮች በሙሉ ይበሳጫሉ። ይበሳጩና ያዝናሉ።
የበደልኳቸው እንኳን ትንሽ ተበሳጭተውብኝ ቀጥሎ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር ለእኔ ማዘን ነው። እኔነቴ ሰው ጨክኖ ጆሮ እንደ ማይነፍገው አሳዛኝ ዜማ ነው፤ እንደ አራራይ። ስለ ዜማ ሳስብ ስለ ሁለቱ የቀድሞ ፍቅረኞቼ አስባለሁ። የመጀመሪያው ግዕዜ
ነው ...... ልጅነቴን በጥበቃ የጨረሸ፤ የኮራብኝ፤ የተጀነነብኝ፣ ደጅ ያስጠናኝ፣
ያስለመነኝ፣ እልህ ያጋባኝ ፣ የፈተነኝ። ሁለተኛው ደግሞ እዝሌ ነው ......የደረብኩት ፣ ያረጋጋኝ ፣ያበረደኝ ፣የወደደኝ። ስለምነው የከረምኩት ግን የገፋኝ። በኋላም ከሚያሳርፈኝ ጋር እፎይ ማለቴን ሲያይ ስመኘው የኖርኩት ፍቅር ካልሰጠሁሽ ብሎ ፊቴ ቆመ። አመታት እርሱን የኔ በማድረግ ምኞት አልፈው በመጨረሻ ፊቴ ሲቆም አይሆንም ማለት አቅቶኝ፤ እዝሌንም በቃኸኝ ግዕዜን አግኝቻለሁ ብዬ እንዳልለው የምጠለልበት የምሰክንበት ጥጋቴ ነውና እንዳላጣው ፈርቼ በሁለት ቢላ የምበላ ሆንኩኝ ። ሁለቱንም በተለያዩ ምክንያቶች ሳላስባቸው ውዬ አላውቅም። ባስታወስኳቸው ቁጥር ግን ሃዘን ይከበኛል። ሁለቱም በመቅበዝበዝ እና በመንገብገብ ያበላሸኹዋቸው የህይወቴ ዋና ዋና ዜማዎች ናቸው። በእርግጥ ከነርሱ በኋላም ያማረብኝ ቅላፄ የተዋጣልኝ አቋቋም የለም ግን እንደ ሁለቱ ያበላሸሁት የለም። አሁን ላይ ከግዕዜና ከእዝሌ የተረፈኝን አራራይ ዜማ ለራሴ ወስጄ ሌት ተቀን እህህ እላለሁ።
ሁሉን የእኔ ይሁን የሚል ልጅነቴን ለተከተለ ደመነፍሴ ፣ በሁለት ዜማ አንድ ቅኝት ለናፈቀ ለጋነቴ ፣ ለባተልኩት ፣ ለባከንኩት ፣ ከሁሉ ከሁሉ በአንድ እለት ግዕዝም እዝልንም ለተቀበለ ሴትነቴ በአራራይ ዜማ እህህ እላለሁ ። በመጨረሻ የገባኝ ግን ሁሉ በአሳዛኝ ዜማ እንደሚቋጭ ነው ፤ ህይወት የሚባል ውብ ነገርም ቢሆን

@wegoch
@wegoch
@paappii

#elssa mulugeta
4.9K viewsDAVE / PAPI, 18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-10 08:32:53 “Express your love, we can't read minds. “

@words19
4.6K views ገብርዬ, 05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-31 10:06:59 ልጅ ስትወልድ ነው ቤተሰቦችህን የምታመሰግነው ከቤ :)
ህፃናት ቤትህን ሲያምሱት ህወሀት ማረኝ ትላለህ። ለምሳሌ ልጅህ የቤትህን ቴሌቪዥን ኩባያ ወርውሮ ሊሰብርብህ ይችላል ። ነገ ወሳኝ ስብሰባ አለኝ ብለህ በክብር ያኖርከውን የሱፍ ጃኬት ባሊ ውስጥ ነክሮ ሲያንቦራጭቅ ልታገኘው ትችላለህ ። ውዷ ባለቤትህ ናፍቃህ እቅፍ አድርገሀት ጉያህ ከመክተትህ ቅናት ያንገበገበው ፈልፈላህ ስኒ ወርውሮ ግንባርህን ይገምስሀል በተለይ ወንድ ልጅ ራሱን የቻለ ወያኔ ነው። ልጄን ቅዱስ ብዬ ከምጠራው ጌታቸው ረዳ ብዬ ለምን አልሰየምኩትም የሚል ቁጭት አንገብግቦኝ ያውቃል። ሌላው ልጅ ስትወልድ የምትረዳው የሴቶችን አስማት ነው። ሴት ልጅ ምትሀተኛ ናት። ሚስትህ የውጭውን ስራ ሰርታ ቤት ተፍተፍ ብላ ልጅህን እንደፀባዩ ስትይዝልህ የሴት ልጅን ተፈጥሮ ታደንቃለህ። ብዙ ወንዶች በባህሪያችን ስልቹ ነን። 10 ደቂቃ ልጅህን አቅፈህ ተቀምጠህ ትግል ሲጀምርልህ ትማረራለህ። አንዳንዴ ረዥም ገመድ አዘጋጅቼ ከጠረጴዛ ግርጌ ልሰረው ወይ ልትል ትችላለህ ።
ቢሆንም...ቢሆንም...ወንድም መላ አለው። ልጄ ሲረብሽ ጊልዶና ሳንቾ ትዝ ይሉኛል። ጊልዶ የሚደብረኝን ያህል መርቄው አውቃለሁ። የጊልዶ ባዶ ...ባዶ ሙዚቃ ቅንብሮች ልጄን ያስጨፍሩታል። የኤልያስ መልካ አጥንት እየወቀሰኝ ሳንቾን እከፍትለታለሁ። ሙዚቃው እስኪፈፀም የሰላም አየር እምጋለሁ። ሙዚቃው ሲፈፀም Phase 2 ጦርነት በይፋ ቤቴ ውስጥ ይጀመራል። ህወሀት ማነው ቅዱሴ ያንሰራራል። የቤቱ ህገመንግስት ተጣሰ ይለኛል። ወልቃይት ....(ወይኔ ጨለልኩ በቃ !)... አንተ የተቀመጥክበት ቦታ የኔ ነው ብሎ ያንባርቃል። እየተንጫነጭኩ ቦታዬን አስረክባለሁ ።
ከልጅህ ጋር ትንሽ ከተጎራበጥክ ባለቤትህ በግልምጫ ታነሳሀለች። ያልሰከነ ቡና ልትቀሳልህ ትችላለች...እንደ ጣና ሀይቅ በቀጠነ ሽሮም ልትመታ ትችላለህ። This is life brother!
....ፈጣሪ ላያስችል አይሰጥም ብለህ ስትማረር ብትውልም የልጅህ አንገት ስር ገብተህ ስትስመው አመፁን ትረሳዋለህ። ሌላ ልጅ መድገም ሁሉ ያምርሀል። ህፃናት ገነትን በአንገታቸው ይዘው ይዞራሉ። በስራ እየጦዝክ በመሀል ልጅህ ይናፍቅሀል። ብጥብጡ.. .አመፁ...ረብሻውም ለካ አንድ መሳጭ የህይወት ሂደት ነው አባዬ ! እየከነፍክ ቤትህ ትገባለህ.. .የሶስተኛው ዙር ጦርነት መለከት ይነፋል :)

@getem
@getem
@paappii

#mikael aschenaki
8.8K viewsDAVE / PAPI, 07:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-27 22:36:58 [መደነቃቀፋችን ዳንስ መስሎን ነበረ]
የስልኬ ሙዚቃ ማጫዎቻ ላይ ሙሉ ቀን እየተደጋገመ ሲዘፍን የዋለው የBen E.King 'stand by me' የሚል ዘፈን ነው። ሁልጊዜ ለምን እንደዛ እንደማደርግ አይገባኝም ፤ አንድ ሙዚቃ ደጋግሜ አደምጣለሁ። አንዳንዴ ለተከታታይ ቀናት ሌላ ዘፈን ሳልቀላቅል ካለማቋረጥ የምሰማቸው ዘፈኖች አሉ፤ ከወደድኩት ነገር ላይ ቶሎ መላቀቅ የሚከብደኝ ለዛ ነው በቃ ከያዝኩ እንደዚ ነኝ ስወድ አፍናለሁ ስወድ አስጨንቃለሁ፤ ለራሴ ራሱ የሚረብሸኝ ባህርዬ ነው እና አዲስ ለሚተዋወቁኝ ሁሉ መጀመሪያ የምናገረው ነገር "ስወድ አስጨንቃለሁ.....ስወድ ችግር አለብኝ"ን ነው። ዘፈኑ ደግሞ አሁን እንዲህ እየተስረቀረቀ ሩቅ ልውሰድሽ ይለኛል፤ ረስቼዋለሁ ትቼዋለሁ ወዳልኩት ትናንት አጅቤሽ ካልሄድን እያለ ያባብለኛል ....
"አሻቅበን ያየነው ሰማዩ ተገምሶ ላያችን ቢደፋ ፣ ወይ ደግሞ _ ግዙፍ ተራራ ተንዶ ከውቅያኖስ ገብቶ ቢጠፋ፣
ማልቀስ እርም ነው ለኔ _አንዲት ዘለላ እንባ እንኳ 'ካይኔ ጠብ አትል አትፈስ፣
አንተ አጠገቤ እስቆምክ ከጎኔ እስካለህ ድረስ፣" አሁን ላይ ሆኜ ሳስበው በአብሮነታችን ውስጥ የነበሩ እንደቀልድ ያለፍናቸው ፤ በእብደታችን ያሸበረቁ በሳቅ ያከበብናቸው በኩርፊያ ያጀብናቸው አያንዳንዱ ቅፅበታት እጅግ ውብ ቢሆኑም ልክ ናቸው ብዬ የማስብበት ዘመን አልፏልና ድጋሚ በጨረፍታም ላስባቸው አልፈልግም። በርግጥ አንዳንዴ ከነዚህ ቀናቶቻችን ጥቂት የእብደት ስራችን የጎላባቸውን
እያነሳሁ ለወዳጆቼ ስነግራቸው ( በትንሹ፤ ስለ ምሽት ባሌት ዳንሳንችን፣ ፀጉሬን ሰብስቦ በስርአት ስለሚያያይዝበት ሻጤ። በአብዛኛው ደግሞ ስለ ፍትወት፤ የቃምነው ጫት ገረባ ላይ ስለምንፈፅመው ሩካቤ፣ ማዕዳችንን ገፍተን ስላጧጧፍነው ወሲብ፣ ዝናብ እየዘነበ ጭቃ ላይ ስላደረግነው ፣ ምናምን) ወይ 'ያማችኋል ግን?' ወይም 'እብድ ናችሁ? ' ካልሆነ ደግሞ 'ይሄ ልክ አይደለም ! '
ይሉኛል። የምንወደው እብደት ውስጥ አብረን እንዋኝ እንደነበር፤ ነፃነት እና እውነት ከሰሩት እብደት በላይ ልክነት እንደሌለ ጨምሬ ልነግራቸው ፈልጌ በቸልታ ትከሻዬን ሰብቄ እተወዋለሁ። ግን እንደዛ ያሉኝ ዕለት አመሻሽ ላይ ናፍቆኛል ልቤ እስኪርድ ናፍቆኛል አለ አይደል የኔና የእርሱ አለም በራሳችን ህግ ተከልሎ በእብደታችን የቆመ ፍፁም ሌላ ፕላኔት ነበርና ማንም የሰራነውን አለም ልክ አይደለም ቢለን የምንሰማ አይነት አልነበርንም፤ አንዳችን ላንዳችን እስካለን
ድረስ የምንፈራው ምንም ነገር አልነበረም። "ምሽቱ በመጣ ጊዜ፤ ምድር ፅልመት ስትለብስ፣ ድቅድቅ ጨለማው መሃል ጨረቃ ብቻ ተግታ ብርሃኗን ለእኛ ስትለግስ፣ ፍፁም ልፈራ አልችልም _
አንተ አጠገቤ እስቆምክ ከጎኔ እስካለህ ድረስ፣" ከሆነ ጊዜ በፊት ወደ ኋላ ተመልሼ አመሻሻችን እንዴት እንደነበር ሳጤን ከሰርክ እለት ዑደታችን ( ስንራኮት ከዋልንበት ከእርሱ ቤት ወደ ቤቴ ሲሸኘኝ) በመንገዳችን አሳብረን የምናልፈው የኡሪዎች ኳስ ሜዳ ነበር፤ ልክ እዛ ስንደርስ ከላያችን የምታበራ ጨረቃ ጥላችንን ፍንትው አድርጋ ስታሳየን ከጥላዎቻችን ጋር የደነስንበት በምሽት ከደመቀ ውበቷ ላይ ቅርፁን ቀይሮ ብርሃኗ ዜማ ሆኖ በጆሮዎቻችን ተንቆርቁሮ እንደነበር አስቤ አውቃለሁ።
በፊት ላይ ሲናፍቀኝ ከሁሉ ከሁሉ በግድግዳው እና በአልጋው ክፍተት መካከል ከፀጉሬ ሾልካ የወደቀች የአንዲት የሻጤ ነገር ያሳስበኝ ነበር። ስለ እርሷ ያልተመለሱ ብዙ ጥያቄዎች ነበሩኝና ባገኘውና ብጠይቀው እወድ ነበር። ከኔ በኋላ ቤቱን እና ገላውን የጎበኘች እንስት ከአልጋ ተንሸራቶ በዚያ በኩል መሬት ያረፈ የውስጥ ሱሪዋን እጇን ሰዳ ስታስስ የፀጉሬ ሁለት ዘለላ
የተተበተበበት ያን ሻጤ ያገኘች እለት ምንድነው የሚሰማት? ምንስ ነው
የምታስበው? እርሱም ከእኔ ጋር እንደለመደው ፍቅር ሲሰሩ የተንጨፋረረ ፀጉሯን ከጉዳያቸው በኋላ ሰብስቦ ሊያስይዝላት አልጋቸው ላይ የተበታተ የፀጉሯን ማያያዣ ሲያስስ አንዱን ተሳስቶ ገፍቶ በቀደመው ክፍተት ቢልከው፤ አልጋ ስር የተገናኙ ሁለት ሻጤዎች እንደ ባለቤቶቻቸው በጣውንትነት ስም ይጠራሩ ይሆን? የየራሳቸውን የውድቀት ታሪክ እና የሴቶቹን እንዝህላልነት እያነሱ ይወያዩ ይሆን? ወይስ... ለየባለቤታቸው ወግነው ቀጫጫ ሽቦ አካላቸውን ለድብድብ ያነሳሉ? ወይስ... እዛው ባሉበት ብዙ ቀናትን አሳልፈው ቤት አፀዳለሁ በሚል ሰበብ አልጋ በምትጎትት ሶስተኛ ሴት እጅ ከወዳደቁበት ተነስተው የወረሳቸው ትቢያ እፍፍ ተብሎላቸው ድጋሚ አናት ላይ ይወጣሉ? እና የናፈቀኝ እለት ወይስ ...... ወይስ ... ወይስ እያልኩ ስለ ጥቃቅኗ ነገር ሁሉ በጥልቅ የማስበው እና የምብከነከነው ከእለታት ድሮ ቀን በወጣች ደንጋዛ እና ፈዛዛ ጨረቃ ደነስን ያልነው መደነቃቀፍ፣ በሌላ ጥንት በሚመስል ቀን ከፀጉሬ የወደቀ ወልጋዳ ሽቦ ምናምን የገዘፈ ጥቅም ኖሯቸው ሳይሆን ከእርሱ ጋር የነበሩኝን ቅንጣቶች በሙሉ ከቋጥኝ አግዝፌ ስለማይ ነበር።
አሁን ላይ ዛሬን በአሁን መለካት ሳይሆን በነገ መስፈር ስለለመድኩ እንደ ጥንቱ
ስወድ አላስጨንቅም፣ አሁን Ben E.King ሳምንት ሙሉ ልብ በሚበላ ብሉዝ ቢለምነኝ እንኳ የሚያንኳኳውን የትዝታ በር ለመክፈት የምጥር አይነት
አይደለሁም። ዘንድሮ ከተረት እና ከኩሸት የቻልኩትን ያህል ተምሪያለሁና ይሄ ይሄ ትዝ ሲለኝ የምለው "የሁሉንም ነገር ዋጋ በሰአቱ መረዳት ብንችል ህይወት እንዴት ውብ ይሆን ነበር" ነው። የማዝነው የማይገባቸውን ዋጋ ሰጥተን ላጡን እና ላጣናቸው ስናላዘን ስለተላለፉን ቀናት ነው።

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Elssa Mulugeta
7.7K viewsDAVE / PAPI, 19:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-26 23:06:32 ሌት ተቀን አምላኬን ስወተውት ነው የማድረው!" አለችኝ። እንደባልና ሚስት ሳይሆን እንደ ፍቅረኞች ነገር ሆንን ..... ያለፀብ አለቀ እና ልንመረቅ አንድ ቀን ሲቀረን አብረን አደርን!!

በነገታው እነማሚ መጡ ልጃችን ልታስመርቀን መጣች። ተመረቅን!! እንደማንኛውም ተመራቂ ተማሪ ፊታችን እስኪገረጣ ፎቶ ስንነሳ ዋልን!! እንዳሰብኩት በማእረግ ባልመረቅም በሚያኮራ ውጤት ተመረቅኩ። በምወዳቸው ሁሉ ተከብቤ ያ የናፈቅኩት ቀን ሆነ!! በሚቀጥለው ቀን ቤተሰቦቼን ሸኝቼ ዶርም ተመለስኩ። ለማንም ምንም ሳልል እቃዬን ሸካክፌ ወደአዲስ አበባ ......... ለማሚ ያለሁበትን ለማንም እንዳይናገሩ አስጠነቀቅኩ። ብዙም ሳልቆይ የግል ዩንቨርስቲ ማስተማር ስራ ጀመርኩ።

በወሩ ደወልኩለት።

"ማወቅ ስላለብህ ልንገርህ ብዬ ነው። ፍቅርን አርግዣለሁ!" አልኩት። ደስ አለው። እብድ ናት በሉኝ በማርገዜ ደስታዬን ብታዩት። ከእርሱ ውጪ ከሌላ ወንድ ልጅ መውለድ አልፈልግማ!!

"የት ነሽ?" ቦረቀ። "ላግኝሽ? We can fix this eko ልጆቻችንን አብረን እናሳድጋለን አይደል? "

"ልጆቻችንን እናሳድጋለን። እኔና አንተ ግን አንድ ላይ ሆነን አይደለም። ልጅህን መጥተህ እንድታይ ስወልድ አሳውቅሃለሁ። በልጆችህ ህይወት ውስጥ እንደፈለግክ ሁን አባታቸው ነህ። በእኔ ህይወት ውስጥ ግን አይደለም።" አልኩት።

happily divorced

እና ዛሬ ላይ ለልጆቼ ሳወራላቸው እንዲህ ነው የምላቸው

"እንዳባታችሁ ያፈቀረኝ ወንድ የለም! ወደፊትም አይኖርም። እንዳባታችሁም ደግሞ የጎዳኝ ወንድም የለም። ....... አባታችሁ ጣኦቴ ነበር። በምድር ላይ ትልቁን ስጦታዎቼን እናንተን ሰጥቶኛል። በእናንተ ደግሞ ደስተኛ ሴት አድርጎኛል። መልካም ነገር ብቻ ይግጠመው።"

................ጨርሰናል ........

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
6.1K viewsDAVE / PAPI, 20:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ