Get Mystery Box with random crypto!

ወግ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @wegoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.51K
የሰርጥ መግለጫ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @leul_mekonnen1

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 31

2021-12-26 10:45:21 አክስቶቼ እና ላሞቻቸው
-----
ጸሐፊ: አፈንዲ ሙተቂ
------
ስለሁለት አክስቶቼ ላወጋችሁ ነው። አሚና ኢብራሂም (በቀኝ) እና ሐኒፋ ሼኽ ሙሐመድ ረሺድ ይባላሉ፡፡ “ሐኒፋ” የአባቴ እህት ስትሆን መላው ዘመዶቿ እና የሰፈሩ ህዝብ “አዴ” እያለ ነው የሚጠራት፡፡ ከዚህ ቀደም “ኦነግ እና ኢህአዴግ በአንድ ቀን ጦርነት” በሚል ርዕስ በጻፍኩት ጽሑፍ ያወጋኋችሁ ጦርነት የተጀመረው በርሷ ግቢ ውስጥ ነው፡፡ አሚና ኢብራሂምም የስጋ ዘመዴ ናት፡፡ ይሁንና አያቴ (ሼኽ ሙሐመድ ረሺድ) ያገቧት የመጨረሻ ሚስት እርሷ በመሆኗ የሼኽ ሙሐመድ ረሺድ ልጆች “አዮ አሚና” እያሉ ነው የሚጠሯት፡፡ እኛም የአባቶቻችንን ልማድ በመከተል “አዮ አሚና” እያልን እንጠራታለን፡፡

እነዚህ አክስቶቼ ልጅ በነበርኩበት ዘመን በርካታ ከብቶች ነበሯቸው፡፡ በግቢዎቻቸው ጥግም ለከብቶች የተሰሩ ሰፋፊ በረቶች ነበሯቸው፡፡ ባለፈው በጥቅምት ወር 2008 ስዘይራቸው ግን የሁለቱም በረት በቦታው አልነበረም፡፡ “ከብቶቹ ወዴት ጠፉ?” ብዬ ስጠይቃቸው ልዩ ልዩ ምክንያቶችን ዘረዘሩልኝ፡፡ ዋነኛው ምክንያታቸው “ድሮ የግጦሽ ስፍራ የነበሩት መስኮች በሙሉ ወደ እርሻ ማሳነት ተቀይረዋል፤ ስለዚህ ከብቶቹን ለማብላት ወደ ሩቅ ስፍራዎች መሰማራት ግድ ይላል፤ አሁን ባለው ሁኔታ ግን ያንን ማድረግ አንችልም፤ በመሆኑም ከብቶቹን ለመሸጥ ተገደድናል” የሚል ነው፡፡ ምክንያታቸው አሳማኝ ቢሆንም ከሁለቱ ቤቶች እንደ ድሮው ትኩስ ወተት በ“ቀቤ” ለመጠጣት ባለመቻሌ አዘንኩ! እስቲ ስለነዚያ ከብቶች ያለኝን ትዝታ በትንሹ ላውጋችሁ፡፡
*
በዚያ ዘመን በሰፈሩ የሚኖረው እያንዳንዱ ቤተሰብ ጥቂት የማይባሉ ከብቶች ነበሩት፡፡ በዘመኑ ወግ መሰረት ሴት ከብቶች (ላም እና ጊደር ) እና ጥጆች ባለቤትነታቸው የእመወራዎች ነው፡፡ ከነዚያ እመራዎች ሁሉ በከብቶች ብዛት የምትበልጠው ደግሞ “አዮ አሚና” ነበረች፡፡ በበረቷ ከሚያድሩት ላሞች መካከል በአንድ ጊዜ የሚታለቡት ብቻ አስራ አምስት ያህል ይሆናሉ፡፡ በመሆኑም ከቤቷ ወተት፣ ቅቤ እና እርጎ ጠፍተው አያውቁም፡፡ አያቴን ሊዘይሩ ለሚመጡ እንግዶች የሚቀርበው “ሆጃ” የሚፈላው በአብዛኛው ከርሷ ቤት በሚታለበው ወተት ነበር፡፡ ልጆች በቤታቸው እንጀራ እና ቂጣ ብቻ አግኝተው ማባያ ሲያጡ ወደርሷ ይመጡና ወተትና እርጎ ይጠይቃሉ፡፡ ለልጃገረዶችም ጸጉራቸውን የሚሰሩበትን ቅቤ ትሰጣቸው ነበር፡፡

በዘመኑ ወግ መሰረት ከብቶችን በስም እየለዩ መጥራት የተለመደ ነው፡፡ ታዲያ ለከብቶች የሚሰጠው ስም በአብዛኛው የከብቱን ቀለም እና ቁመና የተከተለ ነው፡፡ የ“አዮ አሚና” ስም አሰያየም ግን ከዘመኑ ልማድ ወጣ ያለ ነው፡፡ “መጋል” እና “ጉራቻ” ከተሰኙት ሁለት ላሞች በስተቀር ሌሎቹ ከብቶች ለየት ባሉ ስሞች ነበር የሚጠሩት፡፡ ለምሳሌ “ደንገሹ”፣ “ኩሜ”፣ “ባቲ”፣ "መገርቱ" ፣ “ሂና” “ኩሊ”፣ “ኩሪ”፣ "ዱኮ" ወዘተ…. በመሳሰሉ ስሞች የሚጠሩ ከብቶች ነበሯት፡፡ ስያሜዎቹን እንዴት እንደምታወጣቸው አላውቅም፡፡ ታዲያ አዮ አሚና ከብቶቿን ስታነጋግራቸው ዋዛ እንዳትመስላችሁ!! እያንዳንዱን ከብት እያከከችው እንደ ሰው ልጅ ታዋራው ነበር፡፡
*
የአዴ (ሐኒፋ ሼኽ ሙሐመድ ረሺድ) ከብቶች በብዛት የአሚናን ያህል አይደሉም፡፡ ይሁንና ከሰፈሩ ከብቶች ሁሉ ለኔ በጣም የሚታወሱኝ እነርሱ ነበሩ፡፡ ምክንያቱም ነፍስ ካወቅኩ በኋላ ወደሰፈሩ በምሄድበት ወቅት የማርፈው እርሷ ዘንድ ስለሆነ ነው፡፡

ከነዚያ ከብቶች መካከል በጣም ቁጡዋ “ዳለቲ” ትባላለች፡፡ “ዳለቲ” ቀንድ የላትም፡፡ ሆኖም በድቡልቡል ጭንቅላቷ በቴስታ “ገጭ” እያደረገችን ከመሬት ላይ ትፈጠፍጠን ነበር፡፡ ከልጅነት እስከ ጉልምስና ዘመኗ ድረስ የምታውቃት አክስቴ እንኳ ቀኑ ሲመሽ ዳለቲን ይዛ በማደሪያ ስፍራዋ ላይ አስራ አታውቅም፡፡ “ዳለቲ” የማትነካቸው ሁለት ልጆችን ብቻ ነው፡፡ አንደኛው ሙሐመድ አሕመድ (ነጋሺ) የሚባለው የራሷ (የአክስቴ) ልጅ ሲሆን ሌላኛው “ናጂ በደው” ይባላል፡፡ ስለዚህ ዳለቲን ለማሰር ከተፈለገ እነዚያ ልጆች የግድ መገኘት ነበረባቸው፡፡
“ዳለቲ”ን የወደለቻት “ጋሬ” የምትባል ላም ናት፡፡ ይህቺ ጋሬ “ጄብሎ” የተሰኘ ሌላ ላምም ወልዳለች፡፡ ታዲያ ይህቺ “ጄብሎ” በውጊያ እናቷን ታሸንፋታለች፡፡ አክስቴ የቡና አተላ (ረጃ) እና ድርቆሽ ለጋሬ በምትሰጥበት ጊዜ “ጄብሎ” እያባረረቻት ትነጥቃለች፡፡ ሆኖም “ጄብሎ” ምንም ቀንድ ያልነበራትን ዳለቲን አትችላትም፡፡ በመሆኑም ዳለቲ ከእናቷ አፍ ድርቆሹን የነጠቀችውን “ጄብሎ”ን ታባርርና ለራሷ መብላት ትጀምራለች፡፡ ይሄኔ ግን የድርቆሹ የመጀመሪያ ባለቤት የሆነችው “ጋሬ” ከተፍ ትላለች! ምክንያቱም እርሷ ጄብሎን ባትችላትም ቀንዳ አልባ ለሆነችው ዳለቲ ትበረታለችና! እናም ከጅምሩ ለርሷ የተሰጠውን ድርቆሽ ያስመለሰችው “ጋሬ” ዘና ብላ መመገብ ትጀምራለች፡፡ ይሁንና ምንም ያህል ሳይቆይ “ጄብሎ” እንደገና ከተፍ ትልና እንደለመደችው “ጋሬ”ን በማባረር ድርቆሹን መብላት ትጀምራለች፡፡ አንድ ጊዜ ያህል ዋጥ ካደረገች በኋላ ግን “ዳለቲ” ከተፍ ትልና ድርቆሹን ትነጥቃታለች፡፡ “ዳለቲ” መብላት ስትጀምር ደግሞ እንደገና “ጋሬ” ትመጣለች፡፡ እንደገና “ጄብሎ”፤ እንደገና “ዳለቲ”፤ እንደገና “ጋሬ”!
አክስቴ ለሶስቱ ከብቶች በተለያየ ቦታ ድርቆሽ ብታስቀምጥላቸው እንኳ ላሞቹ ጥላቸውን አይተውም፡፡ አንደኛው ከብት ለርሱ የተሰጠውን ከማላመጥ ይልቅ ሌላኛውን ነጥቆ መብላቱ ያስደስተዋል፡፡ ስለዚህ አክስቴ የከብቶቹን ጥል ለማስቀረት ሌላ ዘዴ ፈጠረች፡፡ ላሞቹ ከማደሪያቸው ሳይፈቱ ድርቆሽና ውሃቸውን መስጠት!! በዚህ ዘዴ ሁሉም ተስተካከለ፡፡ ሆኖም አንዳንዴ አክስቴ በቤቷ በሌለችበት ጊዜ የአክስቴ ልጆች የሶስቱን ከብቶች ጥል ለማየት ሲሉ ብቻ መመሪያውን እየጣሱ ከብቶቹን ይፈቷቸው ነበር፡፡ እናም ጋሬ፣ ዳለቲ እና ጄብሎ ለረጃ እና ለድርቆሽ ሲሉ እየተቁነጠነጡ ውጊያ ይገጥማሉ፡፡

ይህ የሶስቱ ላሞች ጥል ለረጅም ጊዜ ሲገርመኝ ነበር፡፡ አንዱ ከብት አንደኛውን ብቻ ይችለዋል፤ ሌላኛውን ለማባረር ግን ወኔ የለውም፡፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው እንዴት ነው…? ሁለቱንም ላሞች የወለደችው “ጋሬ” ሌሎቹን ማሸነፍ ያልቻለችበት ምክንያትስ ምንድነው…? ቀንድ ያላት “ጄብሎ” ቀንድ አልባዋን “ዳለቲ”ን የምትፈራበት ምክንያትስ ምንድን ነበር….?

መልሱን በጭራሽ አላውቀውም!! ይሁንና በኋለኛው ህይወቴ ተመሳሳይ አጋጣሚዎችን በማይበት ጊዜ ሁሉ የነዚያ ከብቶች ጥል ወደ አዕምሮዬ ይመጣል፡፡
*
የአዴ” (አክስቴ) ከብቶች የሚጠሩባቸው ስሞች ከአዮ አሚናም ይበልጥ ያስገርማሉ፡፡ ለምሳሌ ከላይ የጠቀስኳት “ጋሬ”ን እና “ጋሬ” የወለደቻቸውን ብቻ በስም ላስተዋውቃችሁ፡፡

በሀረርጌ ኦሮሞ ባህል መሰረት “ጋሬ” የሚባለው ሰውነቱ በጥቁር ወይም ቀይ ቆዳ ተሸፍኖ በጭንቅላቱ ላይ ብቻ ነጭ የሆነ ከብት ነው፡፡ “ጋሬ” ግን ሙሉ በሙሉ ቀይ ነበረች፡፡ በዚህ ረገድ ከሌሎች ጋሬዎች ሁሉ የተለየችው እርሷ ብቻ ነበረች፡፡ አክስቴ ለምን ከህዝቡ ልማድ ውጪ ለላሚቱ “ጋሬ” የሚል ስም እንዳወጣች ስጠይቃት “ጋሬ የእናቷ ስም ነበር፤ እናቷን በጣም እወዳት ነበር፤ ብዙ ወተት ያለስስት የሰጠችኝ ላም ናት፤ ነገር ግን የአባ ጎርባ በሽታ ገደለብኝ፤ ስለዚህ እርሷን ለማስታወስ ብዬ ለልጇ “ጋሬ” የሚል ስም አወጣሁ” አለችኝ፡፡
1.3K viewsDAVE / PAPI, 07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-25 18:56:43 ልጅነት...
*
በልጅነታችን ሁላችንም ለወላጆቻችን ጨዋ ነበርን። ሼባዎቹ ጠጅ ቤት በተጣሉ ቁጥር
<<ከእገሌ ልጅ ጋር አትዋል!!>> የሚል ሀርድ ይበጨቁብናል። ጥሎብን ደግሞ
የተከለከልነውን ጓደኝነት ነፍሳችን አጥብቃ ትሻለች። በልጅነቴ ኩኩሻ ከተባለ ልጅ ጋር
እንዳልውል ማዕቀብ ተጥሎብኛል። እሱም እንደኔው ከእኔ ጋር እንዳይውል ማስጠንቀቂያ
ተሰጥቶታል። በእዚህ ምክንያት ለአባቶቻችን <<ጦጣው>> የሚል የጋራ ቅጽል ስም
አውጥተንላቸው በድብቅ እንገናኝ ነበር።
አንድ ቀን ጨፌ ኳስ ልጫወት የጨርቅ ኳሴን ታቅፌ በበራቸው ላይ እያለፍኩ ሳለ
ከግቢያቸው ውስጥ የኩኩሻን ድምጽ የሰማኹ መሰለኝ።
<<ኩኩሻ!>> ብዬ ተጣራሁ።
ከግቢው ውስጥ <<እ!>> የሚል ድምጽ ሰማሁ።
<<ኳስ አትጫወትም? ጨፌ እየሄድኩ ነው!>>
መልስ ሳጣ በድጋሚ <<ምነው? ጦጣው አለ እንዴ?>> ብዬ ጠየቅኹ።
ይሄኔ ከግቢው ውስጥ <<ኧረ አለሁ..አለሁ...ግባ!>> የሚል የአባትየውን ጎርናና ድምጽ
ተሰማ።
ከእዚያ በኋላ እንዴት ነፍሴ እስክትወጣ በርሬ ቤት እንደገባሁ እኔና እግሬ ብቻ ነን
የምናውቀው። ሁለቱ ሼባዎች እስኪታረቁ ድረስ የእኔና የኩኩሻ ጓደኝነትም ተቋርጦ ቆየ።
**

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Tilahun girma ango
306 viewsDAVE / PAPI, 15:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-25 12:23:19 አንዳንድ ቀን ይበለኝ የደስታዬ ጠላት እኔ ነኝ እላለሁ ።የማፈቅራት ልጅ ነበረች ፤ ቅብጥ
ያለች ፤ ጨዋታ አዋቂ ነፍሷ በጥንጥ ነገር የሚደሰት ። ቁም ነገሬ ለምለው ነገር ያላት
ቸልታ ነገ ለምመሰርተው ኑሮ ተፅዕኖ እንዳለው እጠረጥራለሁ ። ጥርጣርዬ ግንኙነታችን
ወደ ትዳር እንዳያድግ አገደኝ ።
መልክ አይቼ፤ ዳሌ አይቼ ፤ ሳቄን ብዬ እንዴት ኑሮ እመሰርታለሁ ብዬ ነው የተውኳት።
አብረን ሆነን ስኮምክ እንደትንሽ ልጅ አፏን ከፍታ ደረቴ ላይ ተለጥፋ ታሽካካዋለች ፤ አሳሳቋ
የድብርት ፤ኩርፍያን ይገነብራል።
እኔ ጅንኑ ከእሷ ጋ ስሆን ነፃነቷን ታፈናጥርብኛለች ፤ እላፋታለሁ ፤ ተው እያለችኝ ለልፊያ
እራሷን ታዘጋጃለች ፤ ስታገላት እየሳቀች በሳቋ መሃል "ጅል ነህ እንዴ"? ትለኛለች
ጅል ላልሆነ ሰው ጅል ሲባል የበለጠ ያስቃል የበለጠ ያጃጅላል።
ኩርፊያዋ አይቆይም ፤ ረስታው ታወራኛለች እያወራች መሃል ላይ "ኤጭ ለካ አኩርፌ ነበር
በቃ ምስኪን ስለሆንኩ ትጫወትብኛለህ ኣ"? ትለኛለች አንገቷ ስር ሽጉጥ ብዬ ስስማት
"እሰ..ይ" ትለኛለች ።
እንስቃለን ።
ቁጠባ፤ እቅድ ፤ ነገር ማወሳሰብ ጠላቷ ነው አትችልበትም ። ጫማሽን እንሽጠው እና
እንጠጣበት ብላት አረ ? ጥሩ ሃሳብ ከማለት ውጪ አትግደረደርም ።
አውጥቼ ፤ አውርጄ ፤ ብልጣ ብልጥነቴን ተጠቅሜ ተውኳት።
ሌላ ጠበስኩ
አገባሁ።
ጨዋ ፤ ጠንካራ ፤ነብሴ ከነብሷ የማይናበብ
ሰው ስለወደደልኝ ፤ ጨዋ ነች ብዬ ስላሰብኩ አገባኋት ።
ባለ መነፅር ፤ እርግት ያለች ፤ ለእያንዳንዱ ነገር ማብራሪያ ያላት ጎበዝ ታታሪ ነች ሚስቴ ።
ደስ አለኝ ራሷን የቻለች ልጅ፤ ትጉህ ሰራተኛ እና የሚጠቅማት ላይ የምትመሰጥ በመሆኗ
ነው የመርጥኳት ።
ነገር ግን
ድሮ ቀልድ እችል እንደነበረ ሁላ ነው ያጠፋችብኝ ። ኑሮዬ ሎጂክ ሆነ ። እሷ ጋ ሁሉ ነገር
ቁምነገር ነው። ልለውጣት ብሞክር ብጣጣር ከሆነችው ነገር ፈቀቅ አልል አለች ።
ረጅም ማሽካካት ፤ ልግጫ ፤ ልፍያ ፤ ቀልድ ድራሹ ጠፋ ።
ከስራ መልስ ሌላ ስራ ነው። እራት ይቀርባል ፤ እንበላለን። ቀስ ብለን ልክ እንደ ምግብ
ተሰናድተን ልክ ለደሞዝ እንደሚሰራ ስራ አንዳንዴ እንዋሰባለን።
ወሲባችን ልፍያ የለው ፤ ግፍያ የለው ፤ ችኮላ የለው፤ መላላስ የለው ፤ መቀባጠር የለው ፤
ሁካታ የለው፤ ቅድመ ወሲብ እና ድህረ ወሲብ በወሲቡ ዙርያ ቀደዳ የለ፤ ሁሉ ነገር እሷ ጋ
ቁምነገር ነው ።
ቁጥብ ያለ ነው ሁሉ ነገሯ ።
በቃ ኑሮን ካለ እቅዴ ኮስተር ብሎ ከሚኖሩት ውስጥ ተቀላቀልኩ ። ጭምትር ማለቷን
ላላቅቃት ሞከርኩ ። በሙከራዎቼ መንፈሳዊ ጥቅሶች ፤ ባህል፤ እሴት፤ ወግ እየሞጀረች
ኩም ታደርገኛለች ።
ዝግጁ ያልሆነን ሰው እና ፍቃድ የሌለው ፍጡርን እንደ መቀየር ከባድ ነገር የለም ።
ብዙ ጭቅጭቅ የለ ፤ ብዙ ንዝንዝ የለ ። የማሽን ኑሮ እየኖርኩ ነው።
አንዳንዴ
ምን አለ የድሮ ፍቅረኛዬን ባገባት ኖሮ እላለሁ። እሺ ይሁን እጣ ፈንታችን አልገጠመም ።
ያን የመሰለ ማሽካካት ፤ልፊያ ፤ልግጫ ፤ ቡረቃ አይቼው ባልነበር ፤ ዛሬ እንደዚህ መች
አይኔ ላይ ውል ይለኝ ነበር?!
እጦትን ከሚያጎሉ ነገሮች አንደኛው አግኝቶ ማጣት ነው ።
ቁም ነገረኛዋን ሚስቴን ማግባቴ ትክክል ነኝ አይደለሁም አላቅም።
ኑሮዬ ስራ ሲሆን የድሮ ኑሮዬ ንፍቅ ይናፍቀኛል።
ሚስቴ ጋ ከጓደኛ ጋ መሰብሰብ ፤ ማምሸት መቀምቀም ምቾት አይሰጣትም በዚህም
ምክንያት በአጋጣሚ ካልሆነ አላመሽም አልሰበሰብም አልቀመቅምም።
ጥንካሬዋ እና ጉበዝናዋ የኑሮ ሸክሜን ስታቀልልኝ አይ እሰይ እንኳን ያገባኋት እላለሁ።
ነፃ መሆን ፤መፍታታት ፤መሽካካት ነፃ አበላለግ ከአጋሬ ጋ ሲያምረኝ የትላንቷ እጮኛዬ
ትናፍቀኛለች ።
ማስታወሻ
እጅግ የበዛ እጅግ እንዳነሰ ያህል ነው ።


@getem
@getem
@paappii

#Adhanom Mitiku
446 viewsDAVE / PAPI, edited  09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-25 10:35:31 "ባንቺ ሁኔታ ስለምግብ ማውራት ቅንጦት ስለመሰለኝ እንጂ ቁርስ እንኳን ሳንበላ ነውኮ ጠዋት የወጣነው!" አለኝ ግሩም!

ይቀጥላል ......

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
648 viewsDAVE / PAPI, 07:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-25 10:35:30 አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #5

አፌን ለቆ ሲወጣ የሰማሁት ዓረፍተ ነገር
"አብረን በነበርንበት ጊዜ ወደኸኝ ታውቅ ነበር?" የሚል ነው። ጥያቄዬ አፌን ለቆ ወጥቶ ሳያልቅ በፊት

"ባባ ደህና ነው?" የሚለው የእርሱ ጥያቄ ዓለሜን አዞረብኝ። ለመጠየቅ መልሱን ፈርቶ እያማጠ እንደያዘው ያስታውቅ ነበር። እኔ ሳየው የ15 ዓመት ቁስሌን ነው የጠዘጠዘኝ። ለካስ የእኔ መከሰት ለእሱ የቤተሰቡ ህልውና አደጋ ላይ መውደቅ ማመላከቻ መርዶ ነው። ራስ ወዳድ እንደሆንኩ ተሰማኝ።

"እሱ ደህና ነው። እኔጋ ነው!" አልኩት። በረዥሙ ከሆዱ እስከ ጭንቅላቱ የናጠው የመገላገል ትንፋሽ ተነፈሰ።

"እሷስ?" አለኝና መልሶ "ተይው አትንገሪኝ!" አለኝ። ለሆነ ደቂቃ ስረግመው የኖርኩት አሸናፊ መሆኑን ረሳሁት። የምመልስለትም የምጠይቀውም ተወነባበደብኝ።

"ሞታ ነው አይደል? በህይወት እያለች ላንቺ እንዲደወል አታደርግም።" አጠያየቁ እንድመልስለት የፈለገ አይደለም።

"በህይወት አለች!" አልኩት:: ሲቃ አይሉት ለቅሶ አይሉት ያለየለት ድምፅ አሰምቶ በዛ ቁመቱ ግንድስ ብሎ መሬቱ ላይ ዘፍ ብሎ ተቀመጠ። ላለማልቀስ እየታገለ ግን እንባ ሳይወጣው እያለቀሰ እንደሆነ ያስታውቅበታል። ዝም ብሎ ከማየት ውጪ ማድረግ የቻልኩት ነገር የለም። ድንገት የሆነ ነገር ትዝ እንዳለው ነገር በጥያቄ እያየኝ ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ ተነስቶ

"ቆይ ቆይ ታዲያ ህሉ በህይወት ካለች ባባ አንቺጋ ምን ይሰራል? እ ...እ ... በፍፁም! ህሉ ትንፋሿ እያለ ልጇን አሳልፋ አትሰጥም!" ተቁነጠነጠ። የተፈጠረውን ነገር ስነግረው ጭንቅላቱን በእጆቹ ይዞ ጀርባውን ሰጥቶኝ ቆመ። ምልስ ብሎ

"አንቺ ውሸት አትችዪበትም። እውነቱን ንገሪኝ! ትድናለች?" ሲለኝ የእኔ እንባ ምን ቤት ነው ከእርሱ ቀድሞ የተዘረገፈው?

"አላውቅም!! ሀምሳ ሀምሳ ነው የመንቃት እድሏ ነው ያሉት ሀኪሞቹ።"

እዚህ ደቂቃ ላይ ስለራሴ ምንም እንደማልጠይቀው አወቅኩ። ጥያቄዎቼን መልሼ አዝያቸው ልሄድ ወሰንኩ። ቤተሰብ ለእሱ ዓለሙ ነው። ዓለሙ ፈርሷል። የእኔን ህመም እርሱ ካለበት ሁኔታ ጋር ማነፃፀር አልፈለግኩም። ዝም አልኩ።

"ከሞተች። (ሲቃ እያነቀው ቃሉን ሲለው እንደዘገነነው ያስታውቃል።) ለልጄ እናቱ እንደሞተች አትንገሪው። ሲቆይ ይረሳታል። "

"እንዴ?" ብዬ ጮህኩኝ ሳላስበው።

"ልግባ?" አለኝ ለመሄድ ፊቱን እያዞረ። ግራ ገባኝ። እንዲህ ሁሉ ነገር እጄ ላይ ጥሎ እንዴት ነው የሚገባው? ባባን ምን ላድርገው? እሺ ልጄንስ ምን ልበላት? እሺ ሚስቱን የገጨበትን ሰው በህግ ልጠይቀው በሽማግሌ? እሺ ሚስቱንስ ምን ላድርጋት? ዥውውውው አለብኝ። ይሄን ሁሉ መከራ እላዬ ላይ ጥሎማ አይገባም! ግን የቱን አስቀድሜ የቱን እንደማስከትል እንጃ!

"አዎ እያንዳንዱን ቀን ወድጄሽ ነበር።" አለኝ ለመሄድ እየተንቀሳቀሰ። ማለት የምፈልግ የነበረው ብዙ ነበር። ለምን ብዬ የምጠይቃቸው እልፍ ጥያቄዎች ነበሩ። ፊቱ ላይ ካለው ስቃይ ጋር ሲነፃፀር የእኔ ጥያቄ ገለባ ሆነብኝ። መርዶ ይሁን የምስራች ሳይገባኝ

"እርጉዝ ነበርኩ። ያኔ ..... " ብዬ 'ትተኸኝ ስትሄድ' ልል ነበር። የምጎዳው ነገር መሰለኝና ሌላ የሚተካው ቃል ስፈልግ....

"እና? " አለኝ። ሊሄድ ከነበረበት ተመልሶ በጉጉት

"15 ዓመቷን ባለፈው ሰኔ 6 አከበረች::" አልኩት። ሳቅና ለቅሶ ፊቱ ላይ ተሳከረበት። ወደፊት ወደኋላ ከዛ ወደጎን ተንቆራጠጠ። እጁን አንዴ ጭንቅላቱ ላይ አንዴ ወደኋላ አንዴ ጉንጩ ላይ ያቅበዘብዘዋል።

"ታውቂያለሽ ....." ብሎ ዝም አለ

"አውቃለሁ። ብታውቅ ልጅህን ያለአባት እንድታድግ አታደርጋትም። ልነግርህ ነበር። ልነግርህ ስመጣ አንተ ሄደሃል።" አልኩት። ልክ እንደቅድሙ መሬቱ ላይ ዘጭ ብሎ ተቀመጠ። ግን እንደቅድሙ ለቅሶ ብቻ አይደለም። ፈገግ እያለ ነው የሚያለቅሰው። ቅስስ ብሎ ከመሬቱ ላይ ተነሳ መደሰት ይሁን ማዘን ያለበት ግራ የገባው ይመስላል።

"አባቷ ?...." ብሎ እንዴት መጠየቅ እንዳለበት ግራ ሲገባው

"ታውቃለች። እውነቱን ነው የነገርኳት። የአሁኑን እንዴት እንደምነግራት ነው ግራ የገባኝ።"

ሰዓታችን ማለቁን ደጋግመው እየገገሩን ነው። እንደማሰብ ካለ በኋላ ...... እስከአሁን የሆነውን መሆን እንዳልሆነ ...... ክፉ ዜና እንዳልሰማ ...... ምንም ዝንፍ ያለ ነገር እንዳልተፈጠረ ..... ተረጋግቶ ከፊቱ ላይ እንባውን ካበሰ በኋላ በሰከነ ዝግተኛ ድምፅ

"ጥያቄዎችሽን ሁሉ ብመልስልሽ : የሆነውን ሁሉ አንድ በአንድ ባስረዳሽ ደስ ይለኛል። ምናልባት እድሉን ካገኘሁ የሆነ ቀን ያደረግኩትን ለምን እንዳደረግኩ እነግርሻለሁ። ያ ማለት አንቺ ያ ይገባሻል ማለት አይደለም። እመኚኝ አንቺን ከጎዳሁሽ በላይ ባሰብኩሽ ቁጥር እቀጣበታለሁ። ይገባኛል ብዬም አይደለም የምጠይቅሽ ግን በዓመታት ብዛት ሊከፋ የማይችል ደግ ልብ እንዳለሽ አውቃለሁ። ልጄ ቤተሰብ እንዲኖረው እፈልጋለሁ። ካንቺ የተሻለ ብዙ ፍቅር ያለው ሰው አላውቅም!! እኔ የኖርኩትን ህይወት እንዲኖር አልፈልግም። የተፈረደብኝ ቀን ለሄሉ ድንገት የማትወጣው ነገር ውስጥ ከገባች ላንቺ እንድትደውልልሽ ነገርኳት። ታውቂያለሽ ሁለታችንም ቤተሰብ የለንም። 'በህይወት እያለሁ አላደርገውም ድንገት እኔ የሆነ ነገር ከሆንኩ ግን ልጄ በፍቅር የሚያድግበት ቤተሰብ ያስፈልገዋል።' አለችኝ:: ለዛ ነው መታወቂያዋ ላይ ያንቺ ስም የኖረው። "

ከዚህ በላይ መቆየት አይችልም ነበር። "እሺ አደጋ ያደረሰባትን ሰው ......" ብዬ ሳልጨርስ

"ምን እንደምታደርጊ አንቺ ታውቂያለሽ!! ካንቺ የተሻለ ምክንያታዊ ሆኖ የሚወስን ሰው አላውቅም !" አለኝ ፊቱን አዙሮ እየሄደ።

በቃ! ??? ስመጣ የሆነ ከባድ ሸክም ላራግፍ ...... የሆነ የሚስጥር መፍቻ ቁልፍ ላገኝ ........ የሆነ ያልኖርኩትን መኖር ልጀምር ....... የሆነ ከበሽታዬ የምፈወስ ........ የሆነ ጥያቄዬ ሁሉ የሚመለስ ዓይነት አልነበር የነበርኝ ስሜት?

ጥያቄዬ ግማሹ እንኳን መልስ ሳያገኝ ይባሱኑ ልሸሸው እንደማልሞክር የማውቀውን ሀላፊነት አሸክሞኝ ገባ! ተገተርኩ ለደቂቃ! ልክ እሱ መሬቱ ላይ ዘጭ ብሎ እንደተቀመጠው ንጥፍ ማለት አማረኝ። ራሴን ምን ውስጥ ነው የከተትኩት? ምኑን ከምኑ ነው የማዛምደው? ጭራሽ ልጠይቀው ያላሰብኩት ጥያቄ ትዝ አለኝ። ምን አድርጎ ነው የታሰረው? ምን ያህል ዓመት ይሆን የሚቆየው? ለልጄ እውነቱን ከነገርኳት ቢያንስ ይሄን ማወቅ አለብኝ። እንደገባኝ ከሆነ የግሩም አባት መረጃዎችን በአቋራጭ የማግኘት መክሊት አለው። እግሬ መሬቱ ላይ የተተከለ ይመስል ከተገተርኩበት ተስፈንጥሬ አጠገባቸው ደረስኩ። እንደሆነ ሊፈነዳ እንደተቀባበለ መዓት የምለውን ለመስማት ጠበቁኝ።

"አንድ ውለታ ዋሉልኝ!" ስላቸው ሁለቱም ግራ ገብቷቸው ያዩኛል።

"የታሰረበትን ምክንያትና ምን ያህል እንደተፈረደበት ማወቅ አለብኝ!" ስላቸው ፍፁም የጠበቁት ጥያቄ አለመሆኑ ያስታውቅባቸዋል። አባትየው ከድንጋጤው መለስ ብሎ

"ስልኮች እደዋውላለሁ። " አለኝ።

ወደአዲስአበባ እየተመለስን ጭንቅላቴን የጨመደደው ሀሳብ የታሰረው ክፉ ነገር አድርጎ ቢሆን ለልጄ እንዴት ብዬ እንደምነግራት ነበር። በመስኮቱ አሻግሬ እያየሁ ውስጤ ያለው ስሜት ቅድም ስሄድ የነበረው ዓይነት እንዳልሆነ ገባኝ ..... ምን አጊንቼ ነው የቀለለኝ??

"እርቦኛል:: የሆነ ቦታ ምግብ እንብላ?" አልኩኝ
693 viewsDAVE / PAPI, 07:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-25 10:04:33 አላየሁትም ነበር ።ጠራኝ። ወደ ተጠራሁበት ዞሬ ተመለከትኩ ዘመናዊ መኪና ውስጥ ያለ
ሰው ነው ። ኮስተር ብዬ ስመለከት አበጀ ነው ። በፈገግታ ወደ መኪናው ሄድኩ ።በቶሎ
ከመኪናው ወረደ ተቃቅፈን ሰላምታ ተለዋወጥን ተመችቶታል ።
አይኔ ላይ ተመችቶታል እያልኩ እንዳየሁት ያስታውቃል ። አይኑ ላይ አልተመቸክም አይነት
እያየኝ እንዳለ ገብቶኛል ።
"ምነው በእግርህ መኪና እስካሁን አልገዛህም" አለኝ አዎ ባክህ አልገዛሁም አልኩት ።
ቀጠለ ወፍራም ሳቅ እየሳቀ "ደሞ እግረኛነት ቦርጭህን ከመገበድ ኣላዳነውም"
ሁለታችንም ሳቅን ።
ቀጠለ "አረ ዱብ ዱብ እማ በል አለኝ" ኑሮ ዱብ ዱብ እያደረገኝ ደሞ ሌላ ዱብ ዱብ
ስለው ወፍራም ሳቅ ሳቀ ።
በራሴ ቀልድ እኔም በስሱ ሳቅኩኝ. ።
"አሁንም አዛው የድሮ ቦታ መብራት ሃይል ነው
ነው የምትሰራው"?? አዎ እዛው ነኝ ።
"እና በተረፈ?"
አለው
"አላገባህም?"
አዎ አላገባሁም አልኩት ትከሻዬን ቸብ አድርጎ "አግባ እንጂ በዚህ አያያዝህ የኔ ልጅ ቤቢ
ይቀድምሀል"። ሌላ ወፍራም ሳቅ
በዝባዝንኬ ወሬው ከሱ ጋ ማሽካካት ደከመኝ
በቃ ቻው አልኩት ። "ወዴት ነህ "አለኝ ወደ ቢሮ አልኩት ልሸኝህ አለኝ አይ የምጠብቀው
ሰው አለ እዚህ አካባቢ አልኩት
ቤት አንደገዛ፤ ለቤተሰቦች ምን ምን
እንዳደረገ፤ እንዴት እንደተሳካለት ለጨዋታው ማዋዣ የእኔን እያጣቀሰ እንዲያፌዝበት
ለምን እድል እሰጠዋለሁ ?!
ደመቅ አድርጎ "ቻው አትጥፋ እንደዋወል አለኝ" ወፍራም ፈገግታ ታጅቦ ። ቀዝቀዝ ባለ ፊት
ፈገግታ አልባ ስንብት ሰጥቼው ተሰነባበትን።
ቻው አልኩት ።
ቅር አለኝ። ሰው በዚህ መጠን ለምን ይታበያል ?
ያለን ከሚያስፈልገን አንፃር አይደል ብዙ እና ትንሽ የሚሆነው ።
የሰው ስኬት መለኪያው ገንዘብ ብቻ ነው?? የሰው ስኬት ከአምላኩ ጋ ባለው ታማኝነት
አይለካም ??
የሰው ሰኬት ከቤተሰቡ ጋ ባለው ሰላም አይለካም ? የሰው ስኬት ከራሱ እቅድ እና ፍላጎት
አንፃር አይለካም?? የሰው ስኬት መመዘኛው ንዋይ ብቻ ነው ??
ይሁን እሺ !!!
ሰው በየአጋጣሚው እና ባገኘው አጋጣሚ
እኔ ... እኔ ...እኔ ...እኔ ማለት አለበት ??
ይበል እሺ !!
ስኬቴ ብሎ ሲቀባጥር ለማን እንደሚያወራ እና የሚያወራው ሰው በምን ሁኔታ ላይ
እንዳለ መረዳት የለበትም ?
ሃጠራው !!
ከሴተኛ አዳሪነት ለመውጣት ታግላ የወጣች እንስት አና በድንግልና ለማግባት አልማ
አቅዳ የተሳካላት እንስት ደስታቸው ለራሳቸው እኮ ግዙፍ ነው።
የሰው ስኬት ሁሉ ለባለቤቱ ትልቅ ነው። ባንተ ስኬት እቅድ የሰው መንገድ አታንኳስስ!!
ማስታወሻ ፦ ፩
ያንተ ማግኘት ላንተ ነው
በአንተ ማግኘት ከቻልክ ማገዝ ካልቻልክ ኑራቸውን እንዲያማርሩ ምክንያት አትሁን ።
ማስታወሻ፦ ፪
ባገኘህው አጋጣሚ የተሳካልህን ጉዳይ እየዘበዘብክ ሰው ትግል ላይ ማላገጥ ጠላት
ማፍራት ነው።

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Adhanom Mitiku
160 viewsDAVE / PAPI, edited  07:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-24 11:19:12 "እ? አዎ አይ እርግጠኛ ነኝ! ችግር የለውም!" አልኩኝ ደረቴን በርቅሳ ልትወጣ ይመስል የምትደልቅ ልቤን እንዳያዩብኝ ልብሴን እየነካካሁ። ምንም ባልናገርም ፊቱን ማየት እንደሞት እንዳስፈራኝ ከሁኔታዬ ገብቷቸዋል።

አባትየው ለአንደኛው ፖሊስ ሲያስረዳ ሲጨቃጨቁ አጠገባቸው ሆኜ እንደእሩቅ ድምፅ ነው የሚሰማኝ። የማስበው ሳየው ምን እንደምለው ነው! ሊመልስልኝ የሚችለውን መልስ መላ እመታለሁ። ልጅ እኔጋኮ ልጅ አለህ ስለው ይደነግጥ ይሆን? ይፀፀት ይሆን? እና? ቢለኝስ?

የሆነ ስም ጠርቶ እገሌ ይጠራልኝ ብሎ አባትየው ሲቀውጠው ፖሊሶቹ አልፈቅድ ብለው እንደሆነ ገባኝ። ከመምጣታችን በፊት አጣርቶ ነው ማለት ነው? ፍርሃቴ ከማየሉ የተነሳ እዚህ ድረስ ከመጣሁ በኋላ እንቢ ብለው ሳላገኘው ብመለስ ብዬ አስቤ ለቅፅበት ደስ እንደሚለኝ ተሰማኝ። ትልቁን ፍርሃቴን ተጋፍጬ ከእውነት ከመጋፈጥ መሸሽ!! የሰው ልጅ በብዙ እንደዛ አይደለ? ፍርሃቱን በመሸሽ ውስጥ ያለውን መንገድ ያውቀዋል። ቢወደውም ቢጠላውም ስለለመደው ይኖራል። ፍርሃቱን ሲጋፈጥ ከተራራው ጀርባ ያለውን ግን አያውቀውም። ሳያውቀው ይፈራዋል። አልለመደውማ! ስለዚህ ፍርሃቱን እሹሩሩ እያለ የለመደውን የተለመደ ህይወት ይኖራል።

የተባለው ሰው ተጠርቶ ተጨባብጠው። ሁኔታውን በእርጋታ ከተረዳዱ በኋላ ተስማሙ። ሰውየው አሸናፊ እንዲጠራ ትእዛዝ ሲሰጥ መሮጥ ሁሉ አማረኝ። ብቻ እነግሩም ስለተንቀሳቀሱ እግሬን ወደፊት እየዘረጋሁ ዘለቅኩ። ተጠርቶ ሲመጣ የሚቆምበት ቦታ የሆነ ፖሊስ ነገር እየመራ ወስዶ ሲያደርሰኝ እነ ግሩም ወደኋላ ቀሩ

ከጀርባው ለእኔ ከማይታየኝ ከሆነ ሰው ጋር እያወራ እየሳቀ ብቅ አለ። ሲያየኝ እንደመቆም አለ። ፊቱ ግን የገረመው አይመስልም ነበር። የሆነ ቀን እንደምመጣ የሚያውቅ ዓይነት መረጋጋት ነው ያለው። በረዥሙ ቢተነፍስ ትንፋሹ በሚሞቀኝ ዓይነት ርቀት ላይ ደርሶ ሲቆም ለምን ላገኘሁ እንደመጣሁ ፣ ምን ልጠይቀው እንደነበር ሀሳቤ ሁሉ ጭንቅላቴ ውስጥ ተደነባበረ። እልህ ፣እንባ ፣ላለመሸነፍ ትንቅንቅ ..... አፈነኝ። ወዲያው ደግሞ በራሴ ተበሳጨሁ። እንዴት ያለሁ ልፍስፍስ ነኝ ከዚህ ሁሉ ዓመታት በኋላ እንኳን የበደለኝን ሰው ሳየው ጎብዞ መታየት የሚከብደኝ? እኔ እስካወራ ድረስ ከንፈሩን አላላቀቀም። አይኖቹን እንኳን አልሰበራቸውም። ሳይነቅል ከማየቱ የተነሳ በአይኑ እየቦረቦረኝ ያለ ዓይነት ስሜት ሁላ ነው የተሰማኝ። ለደቂቃ ትንፋሼን ውጬ አይኖቼን አይኖቹ ውስጥ ዘፈዘፍኳቸው። አፌን ለቆ ሲወጣ የሰማሁት ዓረፍተ ነገር

"አብረን በነበርንበት ጊዜ ወደኸኝ ታውቅ ነበር?" የሚል ነው።

ይቀጥላል እንግዲህ......

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
952 viewsDAVE / PAPI, 08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-24 11:19:11 አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #4

ልነግረው ነበር እኮ ደስታ አቅሌን አስቶኝ እቤት የደረስኩት። "አርግዣለሁ እኮ" ልለው።

"ቤት ፣መኪና ፣ የተሻለ ስራ ...... ምናባቱ! አንተን ሙሉ የሚያደርግህ ልጅ መውለድ ከሆነ ሁሉንም ትቼዋለሁ።"ልለው ነበር እቤት ስደርስ

"የእኔ እቅድ አንተን ካስከፋብኝ ባላቅድስ ያንተን ፍላጎት ልኑርልህ" ልለው ነበር። ከመፈንጠዙ የተነሳ ምድር ትጠበዋለች ብዬ እያሰብኩ ከሀኪም ቤት እንደህፃን ዝግዛግ እየረገጥኩ መደነስ እየቃጣኝ እቤት የደረስኩት። እሱ አልነበረም! ብጣሽ ወረቀት አስቀምጦልኝ ሄዷል።

እስከዛች ቀን ድረስ የዓለምን ክፋት በመልካምነት መብለጥ እችላለሁ ብዬ የማምን ጅል ነበርኩ። ከሰዎች ውስጥ ጥሩነታቸውን ለማድመቅ የምጋጋጥ .... ለክፋታቸው ምክንያት እየፈለግኩ ይቅር ማለት የምችል ጀለገግ ነበርኩ። የማንም ክፋት እንዳይሰብረኝ ሆኜ በእድሜዬ በስያለሁ ብዬ የማምን ገልቱ !!! .... ክፋት በምሳሳለት ሰው ተመስሎ ሲመጣ ተሰብስቤ እንዳልገጣጠም ሆኜ ተሰባበርኩ እንጂ.... ለሰዓታት ቁጭ ብዬ እየደጋገምኩ ወረቀቱን አነበብኩት።

"ፌቪዬ አንቺ ቤተሰብ መመስረት እንዳያጓጓሽ በሚወዱሽ ቤተሰቦች ተከበሽ ነው ያደግሽው። መጉደልን አታውቂውም! እኔ የሌለኝን አባት ለልጄ መሆን እፈልጋለሁ። በህይወቴ የተመኘሁት ብቸኛ ነገር የራሴን ቤተሰብ መመስረት እንጂ ቤት መገንባት ወይም ሀብት ማጠራቀም አልነበረም። እንድትረጂኝ አልጠብቅም! አንቺ የተመቻቸ ህይወትም ቤተሰብም ኖሮሽ ስላደግሽ የተመቻቸ ህይወት ሳይኖረን መውለድ አትፈልጊም። ላስጨንቅሽ አልፈልግም! ደስተኛ እንደሆንኩ እያስመሰልኩ አብሬሽ መሆኑንም አልፈልግም። በራሴ ምክንያት በትዳራችን ደስተኛ አይደለሁምና ከሀገር ለመውጣት ወስኜ ፕሮሰሱን ጨርሻለሁ። እንዳትፈልጊኝ። ደስተኛ ሁኚ!

በቃ! በዝህች ሙንጭርጭር ነው 'ደስተኛ ሁኚ' ብሎ ተሳልቆ ደስታዬን ይዞት እብስ ያለው። እያንዳንዱን ዓረፍተነገር እየደጋገምኩ አመነዥካለሁ። ስለልጅ ያወራነውኮ ሁለቴ ነበር። 'ለልጃችን የተስተካከለ ህይወት አበጅተንለት ብናመጣው አይሻልም?' ነበር ያልኩትኮ።

ከመረዳት አልፌ እነማዬጋ ስንሄድ በዝምታ ስለሚያሳልፍ ይከፋው ይሆናል ፣ጉድለቱን ያስታውሰው ይሆናል ብዬ እነማዬን ላለማየት ሰበብ የምደረድር ሰው ነበርኩኮ። ትቶኝ ቢሄድ እንኳን ቢያንስ በአካል ቢነግረኝ ምን ነበረበት? ከእቅዴና ከፍቅራችን የቱ እንደሚበልጥብኝ ለመረዳት እድሉን እንዴት አይሰጠኝም?? ሰዓታት? ሰዓታት ታግሶኝ ቢሆን "ልጃችንን በሆዴ ይዣለሁ!" ልለው አልነበር?

ሁሉም ክስተት እንደአዲስ ውስጤ እየተገላበጠ ያምሰኝ ገባ! የወረቀቱ ሻካራነት እንኳን ጣቶቼ ላይ ይሰማኛል። በእንባዬ የተኮማተሩት ፊደላት .... ደብዳቤው የነበረበት ጠረጴዛ ..... እኔ የተቀመጥኩበት ረዥም ወንበር ...... ቀን ላይ ተሰርቶ የበላነው የነበረው ሳሎኑን ያፈነው የቀይወጥ ሽታ ....... ልክ እንደአሁን ይንጠኝ ጀመር። ረዥም ሳግ የቀላቀለው ትንፋሽ ተፈስኩ።

ወደ ሸዋሮቢት እየሄድን ነው። ከግሩም እና ከአባቱ ጋር ። ሳገኘው ምን እንደሚሰማኝ ማሰብ አልፈልግም። ትቶኝ የሄደበት ምክንያት ልጅ ያለመሆኑን ብቻ ነግሮኝ ራሴን ይቅር እንድለው ነው ጥድፊያዬ። ዓመታቱን እጎነጉናለሁ። ከመታሰሩ በፊት 10 ዓመት አብሯት ኖሯል። ልጅ የወለዱት ምናልባት ከ8 ዓመት በኋላ ነው። ፎቷቸው ያስታውቃል ደስተኛ ነበረ። ከሀገር ወጥቻለሁ ያለኝም ጭራሽ ውሸቱን ይሆናል አይደል? እንዳልወደደኝ ማወቅ ወይም ምክንያቱ ልጅ እንዳልነበር ማወቅ የቱ የበለጠ እንደሚሳምም ማመዛዘን አልቻልኩም።

ለማንም ምንም አልተናገርኩም። ሰኞ እስኪደርስ እንዳልፈነዳ ስፈራ ነበር ሰኞ የነጋልኝ። የዛን ቀን እነእማዬጋ ካደርኩ ጥያቄያቸውን ስለማልችለው ባባንና ልጄን ይዤ ወደቤቴ ተመለስኩ። ልጄ በእኔ ፈንታ አባብላ ዝም ባታስብልልኝ በነበርኩበት ሁኔታ ባባን ማረጋጋት ፈታኝ ነበር። እሁድ ቀን ወደሆስፒታል የሄድኩት ጥያቄዎቼን እንድትመልስልኝ ይሁን ወይም በጥሩነት እንድትድን ፈልጌ ይሁን ሳላውቅ ነው። እሷ እቴ! የትናንት ህመሜን ፣ ስድስት ማትሪክ የሚወጣቸው ዳሽ ሙላ ጥያቄዎች እና ባባን አስታቅፋኝ ....... ለሽሽሽ ብላለች።

ልጄ ለወትሮ ክፍሏ ከገባች ብጠራት የማትሰማኝ ከስር ከስሬ እያለች

"እማ ምንድነው የሆንሽው? እንደዚህኮ ሆነሽ አታውቂም ምንድነው?" ትለኛለች።

"ምንም አልሆንኩም!" እላታለሁ እየደጋገምኩ። ምልስ ብላ ያበረታችኝ መስሏት

"ባባ አሳስቦሽ ነው? አንቺ እንኳን ለአንድ ልጅ ለአንድ መዋዕለ ህፃናት ልጆችኮ እናት መሆን የምትችዪ ምርጥዬ እናት ነሽ!" ስትለኝ ሲንቀለቀል ዓይኔን የሞላውን እንባዬን እንዳታየው ዘልዬ ወደመታጠቢያ ቤት ገባሁ።

እንዴት ነው አይደለምኮ አባትሽን አገኘሁት!! ባባ ወንድምሽ ነውስ የምላት? ለእኔ ለትልቋ ሴት መሸከም ከብዶኝ እያንገታገተኝ ያለሁትን ጉድ በምን ለውሼ ብነግራት ነው ህመሟን የሚያለዝበው?

"አባቴን ማወቅ እፈልጋለሁ!፣ አባቴ ማነው? ለምንድነው የማይፈልገኝ?" ብላ ስትሰፋኝ

"አባትሽ አንቺን ማርገዜን ሳያውቅ ነው ተጣልተን ትቶኝ የሄደው። ቆይተን እንውለድ ስላልኩት ነው የተጣላኝ ..... አየሽ በተዘዋዋሪ አንቺን ስላልሰጠሁት ነው የተጣላኝ እንጂማ ልጁን ቢያውቅሽ ኖሮ ይኖርልሽ ነበር። ምርጥ አባት ይሆንሽ ነበር። ላልወለዳት ልጁ በፍቅር ያበደ ነበር" ብዬ ከነገርኳት ዓመት እንኳን አልሆነምኮ። ለራሴ እንኳን በቅጡ ያልገባኝን ትርምስምስ ምን ብዬ ልንገራት?

"ደህና ነሽ? የምትፈልጊው ነገር አለ?" አለኝ አብርሃም። ለካ መኪናው ቆሟል። ስሙን ለማወቅ ግድ ያልሰጠኝ የሆነኛው ከተማ ደርሰናል።

"አይ ደህና ነኝ። ምንም አልፈልግም" አልኩኝ።

የምፈልገው ግን ከቅዳሜ በፊት የነበሩት ቀኖቼ ላይ መመለስ ነበር።
ስራ ቦታ ...... የአንድ ባንክ ቅርንጫፍ ሀላፊ የሆነች ፣ ባል የሌላት ፣ 'ይህቺ ሴት ቆማ መቅረቷ ነው' እያሉ ሲያዝኑልኝ ..... ገሚሱም ሲመክረኝ ገሚሱም 'ችግር ቢኖርባት ነው' እያለ ሲያማኝ ከስራዬ ውጪ ከማንም በጥብቅ ሳልጋመድ የምትውለዋን ያቺን ሴት .......

እቤት ስመለስ .......ከልጄ ጋር የቤት ስራዋን ስንሰራ፣ ስለጓደኞቿ ስታወራኝ ፣ በሳምንት ሁለት ቀን ፊልም አብረን ስናይ፣ በሳምንት ሁለት ቀን ተራ በተራ መፅሃፍ ስናነብ፣ ክፍሏ ገብታ ስትቀርብኝ ለመጥራት ሰብብ ስፈልግ፣ የቀረውን ጊዜ ጓዳ እኔ ምግብ ሳበስል እየመጣች የእድሜዋን ጥያቄ እየጠየቀች ልቤን ድክም ስታደርገኝ የምታሳልፈዋን ያቺን ሴት.....

ቅዳሜና እሁድን ...... ከልጄ ጋር ቤተሰቦቼጋ ሄደን በቀን ለማይቆጠር ጊዜ ቡና ስናፈላ፣ ጉንጫችን እስኪዝል የባጥ የቆጡን ስናወራ፣ የእማዬን ጣፋጭ ምግብ ቁንጣን እስኪይዘን ስንበላ ፣ አባዬ በልጅ ልጆቹ ሩጫና ጩኸት ሲያማርር እየሳቅን የምታሳልፈዋን ሴት ......

ሁሉ ባይኖረኝም ባለኝ የማመሰግን። ህመሜን ባልረሳውም ከህመሜ ጋር እንዴት ተከባብረን ተላምደን መኖር እንዳለን የተማርኩኝ ያቺን ሴት......

አርብ ከመተኛቴ በፊት የነበርኳትን ሴት መሆን ነው የምፈልግ የነበረው። እንደብዙ ሰውኮ ብዙ አልጠየቅኩም አይደል እንዴ?

"ደርሰናል። ግን እርግጠኛ ነሽ ልታገኚው ትፈልጊያለሽ?" ሲለኝ ነው አሁንም መኪናው መቆሙን ያስተዋልኩት። ከኋላ ብቻዬን ነበር የተቀመጥኩት።
855 viewsDAVE / PAPI, 08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-23 23:07:11 መጥፎ ሴት አይደለሁም። ግን ደግሞ መልዓክም አይደለሁም። የአሸናፊን ልጅ ልንከባከብ? ራሴን ፈራሁት። እኔ እኮ በእርሱ ምክንያት ማንንም የማላምን ደንባራ ሴት ሆኛለሁ። ሙሽራዋ ከአንድ ዓመት በላይ አብሯት ለመዝለቅ ያልፈለጋት ምንም የሆነች ዓይነት ሴት እንደሆንኩ እየተሰማኝ ታምሜያለሁ። እኔኮ በእርሱ ምክንያት ፍቅርንም ሰው ማመንንም ሰው መቅረብንም አጠገቤ እንዳይደርሱ አርቄ ቀብሬያቸዋለሁ። የእርሱን ልጅ ላሳድግ? እናቱ አይበለውና ብትሞት እናቱ እሆናለሁ? ራሴን ፈራሁት ......

"እማዬስ?" አለኝ ባባ ሳሎን ገብቼ የደነዘዘ ሰውነቴን ሶፋው ላይ እንደጣልኩት። 'እናትህማ እኔን ፍም ላይ ማግዳኝ ሆስፒታል ተኝታለች' ብለው ደስ ባለኝ።

"ምነው እማ? ምን ሆንሽ?" አለችኝ ልጄ ተከትላ ..... እንደአዲስ ክው ብዬ ደነገጥኩ .... ምንድነው የምላት???

ምንም ከማለቴ በፊት ባባ

"እማዬጋ ውሰጂኝ!" ብሎ እሪታውን አቀለጠው።

ይቀጥላል። ...........

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
379 viewsDAVE / PAPI, 20:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-23 23:07:11 አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #3

የእኔ አሸናፊ ሊሆን አይችልም! እሱ እንዲህ ሊደፍረኝ ድፍረቱ ሊኖረው አይችልም። የእኔ አሸናፊ ቢሆን ደግሞስ ለሚስቱ ማናት ብሎ ነው የሚነግራት? ምንስ ቢላት ደግሞ የአደጋ ጊዜ ተጠሪዋ አድርጋ ትፅፈኛለች? መቼም እህቴ ናት አይላትም ዘንድሮ ወንዱ ብሶበታል እናቴ ናትስ ብሏት ቢሆን? ወይ አክስቴ ………. አይሆንም እንዲሁ ራሴን ሳስጨንቅ ነው። አሸናፊ የሚባል ሀበሻ አሸን አይደል?

ለማንም ምንም ሳልተነፍስ ልጄንና ባባን እነእማዬጋ ትቼ ቦታው ደረስኩ። ለእነእማዬ ስሙን ብጠራባቸው ቄስ ጠርተው ነው እንዳልሄድ የሚያስገዝቱኝ። ልቤ ሲደልቅ በለበስኩት ሹራብ ላይ ይታያል። ሰዎቹን ምን እንደምጠይቃቸው አላውቅም። ብቻ መልሳቸው የእኔ አሸናፊ አለመሆኑን እንዲያረጋግጥልኝ አምላኬን እለምናለሁ። አብረሃምና ግሩም ሰዎቹ ቤት ተቀምጠው እየጠበቁኝ ነበር። አከራዮቹ ስገባ አስቀድመው ተነግሯቸው ስለነበር እንደሚያውቀኝ ሰው ሰላም አሉኝ። ‘ፈስ ያለበት’ ሆኖ ያውቁኝ ይሆን እንዴ ? ብዬ አሰብኩ።

“ይኸው እኛ ቤት መኖር ከጀመሩ አስራ ሁለት ዓመታቸው ነው። መጥቶ የሚጠይቃቸው ቋሚ ጓደኛ እንኳን የላቸውም እንኳን ቤተሰብ። ሁለቱም ቤተሰቦቻቸውን አያውቋቸውም። ምንድነው ስሙ ጠፋብኝ ……. ሁሌ ያወሩት ነበር ….. የሆነ የህፃናት ማሳደጊያ ነው አብረው ያደጉት።”

የውስጥ እጄን አላበኝ። አሸናፊ ማሳደጊያ ነው ያደገው:: ከዚህ በላይ እስኪነግሩኝ መጠበቅ ራሴን ማሰቃየት መሰለኝ።

"የአባቱን ስም ያውቁታል? አሸናፊ ማነው የሚባለው?"

"ማን ነበር አንቺዬ ? አሸናፊ ......" ብለው ሊያስታውሱ ሲታገሉ አባወራው ቀለብ አድርገው "አሸናፊ ታዬ ነው። እርግጠኛ ነኝ።"አሉ።

አፌ ውስጥ ሞልቶ የነበረው ምራቅ ደረቀ። ፀጥ አልኩ። የሰማሁትን እርስ በርሱ ሳጋባው ጭንቅላቴ ውስጥ ወዲያ ማዶ እጅግ ርቆ የተቀበረ ስም ትዝ አለኝ ሄለን!!

"ታናሽ እህቴ በያት! አብረን ስላደግን ሳናወራ እንግባባለን። በዚህ ምድር ላይ እንደርሷ የሚያውቀኝ ሰው የለም ነበር ያለኝ" ያኔ።

ራሷ ናት! አረብ ሀገር ነበረች ያኔ! በጠና ታማ ወደሀገር ቤት ስትመለስ ክንፏ እንደተሰበረች ወፍ እየተጥመለመለ በእንባ ሲነግረኝ አባዬን "ቤት ልገዛ ብር አንሶኝ ነው" ብዬ ዋሽቼ ብር ተቀብዬ ሰጥቼዋለሁ። ለአብሮ አደግ እህቱ ማን ያውቃል እኔንም ታላቅ እህቴ በያት ብሎ ይሆናል የነገራት። ምናለ ብትነቃ እና በጠየቅኳት

"ታውቂዋለሽ?" አለ ግሩም የፈሰሰ ፊቴን አይቶ

"መሰለኝ። አሸናፊ ታዬ የሚባል ሰው ከረዥም ጊዜ በፊት አውቃለሁ። የሚስቱ መታወቂያ ላይ ስሜን የሚያፅፍ አይነት መተዋወቅ አይደለም እንጂ ...."

"ምናልባት ቁልፍ ካላችሁ እቤታቸው የፎቶ አልበም አይጠፋ ይሆናል። እዛው እናንተ በቆማችሁበት ማየት ብንችል?" አለ አብርሃም

"የታሰረበትን እስር ቤት ታውቁታላችሁ?" ጭንቅላቴ ውስጥ ያሰብኩት ጥያቄ አይደለም። እኔም ከአፌ ሲወጣ ነው የሰማሁት። ብቻ ዓይኔን እያየ እንዲነግረኝ የምፈልገው ብዙ ነገር ነበረ

"እዚህ እያለ እንጠይቀው ነበር። ከ6 ወር በፊት ወደ ሸዋሮቢት ተዛውሯል። ከዛ በኋላ ጠይቀነውም አናውቅ። እሷም እግር ስናበዛ ደስ አይላትም።" አሉ ሰውየው የሆነ ቅሬታ ባለው ድምፅ

"የታሰረበትን ምክንያት ያውቁታል?" አልኩኝ መልሱ ምን እንደሚሰራልኝ ሳላውቅ

"ምኑን አውቀነው። ሚስጥር ነው እናቴ! እንድናውቅ አልፈለጉም። ሁለቱም እንደልጆቻችን ነበሩ። እሱ ከታሰረ በኋላ እሷ ጭራሽ ሌላ ሰው ሆነች። አንድ ጊቢ ሆነን የማንገጣጠም ሆንን" አሉ ሴትየዋ

"እንግዲህ ካላችሁ ቤቱን ልክፈትላችኋ!" አሉ ሰውየው ወሬውን መቀየር የፈለጉ ይመስላሉ።

እግሬ መቆም የሚችል ሁሉ አልመስልሽ አለኝ። አሁንም እሱ ባልሆነ እላለሁ ደጋግሜ

"ይቅርታ እኔ እዚህ ልቆይ እናንተ አልበም ካገኛችሁ አምጡልኝ እቤት አልግባ?" አልኩኝ ልምምጥ በሚመስል። የቤቱ አባወራ እና አብርሃም ሲሄዱ ግሩም አጠገቤ መጥቶ

"ይቅርታ በጥሩ የምታስታውሺው ሰው አይደለም መሰለኝ" አለኝ

"በጭራሽ!" ለጥሩ የቀረበ ምናምኒት ትዝታ እንኳን የለኝም። ..... ያልገባኝ ስሜን እንኳን ለማውሳት የሚያስችል ድፍረት እንዴት እንደኖረው ነው። እፍ እፍ ብሎ ቀብሮኝ የሄደ ሰው ነው:: " አልኩት ልክ ዛሬ የሆነ ይመስል እያርገፈገፈኝ። ለማያውቀኝ ሰው የማይነገር ስሜት እያወራሁ እንደሆነ ሲገባኝ

"ይቅርታ የማይባል አልኩ!" አልኩት መልሼ

"በፍፁም የማይባል አላልሽም። ማውራት ከፈለግሽ ጥሩ ሰሚ ነኝ::" አለኝ ትከሻዬን በአይዞኝ ደለቅ ደለቅ እያደረገ

"ማውራትስ የሚሆንልኝ ሰው አይደለሁም።" አልኩት። እነአብርሃም አንድ ያረጀ የፎቶ አልበም ይዘው ብቅ አሉ። ልቤ እሱ መሆኑን እያወቀ። ፎቶው ላይ ያለው ሰው ሌላ ሰው ቢሆን እላለሁ። እጄን ለመዘርጋት አልታዘዝልሽ እንዳለኝ ገብቶት ነው መሰለኝ ግሩም አልበሙን ተቀበላቸው። እንደማራገፍ ካደረገው በኋላ

"ዝግጁ ነሽ?" አለኝ ለመክፈት እጁን አዘጋጅቶ በጭንቅላቴ አይደለሁምና ነውን እንዳምታተሁ እየገባኝ። ወደላይም ወደጎንም ጭንቅላቴን ወዘወዝኩት። ገለጠው። ....... ራሱ ነው።

ትቶኝ ሲሄድ በአካል ሊነግረኝ እንኳን ያላከበረኝ አሸናፊ። ..... በብጣሽ ወረቀት እንደተወኝ : አብረን የገነባነውን ዓለም የኔ ዓለም አይደለም ያለኝ ..... አሸናፊ ! ትቶኝ ለመሄዱ ምክንያት እኔ ልጅ መውለዱን እናዘግየው ማለቴ መሆኑን አሳምኖኝ በፀፀት ያነደደኝ አሸናፊ ...... በብጣሽ ወረቀት የሶስት ዓመት ፍቅራችንን ....... ሙሽራዬ ተብዬ ደስታ እና ወዙ ሳይደበዝዝ የዓመት ትዳራችንን ....... እንደ ብናኝ ብትንንንን ያደረገው አሸናፊ !! ከሀገር ወጥቻለሁ አትፈልጊኝ ነበር ያለኝ። ...... ፎቶዎቹ ላይ ደስተኛ ይመስላሉ። ሰው እንዴት እንዲህ ክፉ ይሆናል? ሰው እንዴት እንዲህ ያለ ቅጥፈት ይቀጥፋል? እኔን ባይወደኝ ለእኔ ባያስብ ሰው የዘራውን እንደሚያጭድ እንዴት ነገውን አልፈራም? ትቶኝ መሄዱ ሳያንሰው ለትዳራችን መፍረስ ምክንያቷ እኔ መሆኔን አምኜ እንድተክን እንዴት ይፈርድብኛል?

"ሸዋሮቢት እሄዳለሁ!" አልኩኝ ሳላስበው። ማንም ምንም ሳይል ደቂቃ ከቆዩ በኃላ

"ዛሬ መሽቷል። ነገም ሰንበት ነው። ሰኞ በጠዋት እኔ አደርስሻለሁ ከፈለግሽ። እስከእዛ ድረስ ደግሞ ምን እንደሚፈጠር አይታወቅም። እናትየው ትነቃም ይሆናል።" አለኝ አብርሃም። እየሆነ ያለው ነገር ምን እንደሆነ ባያውቅም ሲኦል ነክ ነገር መሆኑ ሳይገለጥለት አልቀረም። ህመሜ እንደአዲስ ልቤን ሲሰቅዘኝ ታወቀኝ ልክ እንደያኔው ትቶኝ እንደሄደ ጊዜ ....... መንገር አፍሬ ብቻዬን ለወራት እንደቆሰልኩት ለማንም አገኘሁት ሳልል መታመምን በወደድኩ ......

"እቤትሽ እናድርስሽ?" አለ ግሩም መደንዘዜ ገብቶት። ያላለቀውን አልበም እየገጠመው። የእነእማዬ ቤት አቅጣጫ በየት መሆኑን ከማመልከት ውጪ ቃል ሳልተነፍስ እነእማዬጋ ደረስኩ። ባባ ከእንቅልፉ ነቅቶ ከጠዋቱ በተሻለ ነቃ ብሎ ከወንድሜ ልጆችጋ እየተጫወተ ነበር።
383 viewsDAVE / PAPI, 20:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ