Get Mystery Box with random crypto!

ወግ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @wegoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.51K
የሰርጥ መግለጫ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @leul_mekonnen1

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 28

2022-01-25 20:24:31 -ፅልመት-

ክፍል 1

እንደው ለበደለኩት ሲቀጣኝ እንጂ ካልጠፋ መንገድ በኮሮኮንች ምን ወሰደኝ? እንደው በድፍረት ለሰራሁት ጥፋት ቅምሻ ቅጣት ብሎ እንጂ ለምን በኮብልስቶኑ ታጠፍኩኝ ቀጥታ
መሄድ ስችል ? ድንገት መተጣጠፌ የድካሜ ሰበብ ሆኖኝ ጉሮሮዬን የሚያረሰርስ መጠጥ ፈለኩ በአንዱ እጥፋቴ ቅጽበት ሰዋራ ስፍራ ላይ ያለች ሆቴል አየሁ ወደ ሰዋራዋ ሆቴል ገባሁ
አንዱ ጥግ ቁጭ ከማለቴ ቅፅበት አስተናገጁ ሲወረወር መጣ ቀዝቃዛ በደሌ አዘዝኩ ድንገት የሆቴሉን ድባብ እና ስፋት በዓይኔ ስቃኝ ፤ ስመትር የማቀውን ባለኮፍያ ብራቡሬ ሹራብ የለበሰ ጀርባ አየሁ ሹራቡንም ጀርባውንም አውቀዋለሁ ። ግንባሬን ቁጥር ፤ አይኔን
ትኩር አድርጌ ተመለከትኩ ። ሹራቡን የለበሰችው ልጅ ስታሽካካ ከመስማቴ በፊት ነበር ሚስቴ እንደሆነች ያወኩት ። የሚስቴን ሹራብ ለብሶ እዚህ ሰዋራ ስፍራ የመጣው ማነው ? የሚስቴን ጀርባ የለበሰው ማነው? የሚስቴን ሳቅ አይነትስ የሚያሽካካውስ? አብሯት ያለው ጎረማሳ እያሳቃት ፤ አንገቱ ስር እየወሸቃት ነው ። ሁሉ ነገራቸው ሌላ ነገር እንዳዘለ ያስታውቃል።
አለም ሚዛኗ ተዛባባኝ ፤ ወበቀኝ ፤ ጥሜ ጠፋ ። ግንባሬ ሲወረዛ ታውቆኛል ።ሰውነቴ
ልፍስፍስ አለብኝ ። ሰው ለካ ዱብ'ዳ ሲገጥመው ይሰበራል እንጂ ያዙኝ ልቀቁኝ አይልም ። ወንበሬ ላይ እንዳለሁ እንስ አልኩ ፤ እንደው ኩርምት
የሚስቴን እኔ ራሴ የገዛሁላትን ሹራብ አይቼ ። ስንት ቀን ያሸውትን ፤ የተደገፍኩበትን ፤ከሰውነቴ ጋ የተፋተገውን ጀርባ በቅፅበት ብለየውም አላመንኩም ። ሳቋን የሰማው ጆሮዬን ማመን አልተቻለኝም ። የሆነ ሰው ሹራቧን ፤ ጀርባዋን ሳቋን ተውሷት መሆን አለበት! ስልኬን አውጥቼ "ቤቱሻዬ " ብዬ ሞባይሌ ላይ save ያደረኩትን የሚስቴን ቁጥር ደወልኩበት የሚስቴን ሳቅ፤ ጀርባ ፤ሹራብ የያዘችው ሴት ስልኳ ጠራ ፤ ከቦርሳዋ ስታወጣው እንቅስቃሴዋ ነገረኝ ወይ ገመትኩ ፤ ግን አልተነሳም ። ድብዝዝ አለብኝ ። መላቅጡ የጠፋ ውጅንብር ውስጥ ሰመጥኩ ፤ ተምታታብኝ ፤ እሪሪ ማለት መጮኽ ፈለኩ ግን ደግሞ አቅም አጣሁ እኔ ስልኳ ላይ ከደወልኩላት እሷ እኔ እንደደወልኩ ካወቀች እና ካላነሳች ቀጥሎ ለአስተናጋጁ ምልክት የሰጡት ይመስለኛል ቀልጠፍ እያለ እነሱ ጋ ሲሄድ አየሁት
ገባኝ ካለወትሮዬ በዚህ ሰዓት መደወሌ ቢፈልገኝ ነው ብላ ተለይታው ልትደውልልኝ ነው ። በቃ አስቻኩላው ነው አልኩ ። አስተናጋጁ ተመልሶ መጣ ፤ መልስ ይዞላቸው የመጣ ይመስለኛል።
ተነሱ ፤ ሲነሱ እንዳያዩኝ ፌቴን ወደ ሌላ ቦታ አዞርኩ አላስችል ብሎኝ ስዞር ፤ ይመጣሉ ብዬ በጠበኩት ተቃራኒ ፤ በጀርባ በኩል ገቡ ። ላመል
ያክል ከጎረምሳው ጋ አብራዋ ያለችው ወደ ጀርባውን በአይኖ ገልመጥ አድርጋ ሄደች።
ሌባ ደምቡ ነው ከመኖርያ ስፍራ ርቆ ሰዋራ ስፍራ ይገባል፤ ሹርብ ይለብሳል ጥግ ላይ ጀርባውን ሰጥቶ ይቀማጣል ሲንቀሳቀስ ጀርባውን አያምንም ገልምጥ ያደርጋል ። አዞዞሯ ደመነፍሳዊ ስለነበር አላየቺኝም
አስተናጋጁን ጠራሁት ። አንድ ያልጠጣሁት በደሌ ፊቴ እያለ ሌላ አንድ አምጣልኝ አልኩት ፤ ሊሄድ ሲል በዚህ ጋ መውጫ አለ እንዴ አልኩት ፤ ተያይዘው በገቡበት እጄን እያመላከትኩ ፤ የለም አልጋ ክፍል ብቻ ነው በዚህ ጋ ያለው አለኝ።
ደረቴ ስር ሲሸቀሸቀኝ ተሰማኝ ፤ አጥወለወለኝ ። ብዙ ጥያቄ መጠየቅ ፈልጌ ነበር ። አዘውትረው ይመጣሉ ወይ? ታቃቸዋለህ?? በየ ስንት ግዜ ፤ ስንት ሰዓት ላይ?? ማለት ፈልጌ ነበር አቃተኝ ።
ዝም ብዬ ትኩር ፍዝዝ ብዬ ሳየው ከአፉ እንቅስቃሴ በቀር የሚለውን አልሰማ ስለው ሄደ ።
አለም የምናስበውን እና የሆነብንን ትመስላለች ። አሁን ከሰዓት በፊት የነበረችው አለም ሰላም ነበረች ከመቼው አዘቀዘቀች ። ከመቼው ጤናዬ ታወከ ። ሁሉን ማመን አቃተኝ ፤ የመጨረሻ ብዬ ለአስተናጋጁ በምልክቴ ሂሳብ አልኩት
ሂሳብ ይዞ መጣ እና ድፍን ሁለት መቶ ብር ሰጠሁት ፤ በቶሎ ዘጠና አምስት ብር ይዞ
ተመለሰ ። መልሱን ያዘው አልኩት ። እጅግ አመሰግኗኝ ሊሄድ ሲል ። እንደምንም ራሴን አረጋግቼ ፤ እዛ ከልጅቷ ጋ የተቀመጠው ልጅ ቀጥሮኝ ነበር ፤ እመጣለሁ ብሎኝ ቀረ አልኩት ፤ ዝም ብሎ አየኝ ፤ አዳር ነው እንዴ አልጋ የያዘው አልኩት ፤ አይ አረ ጊዜያዊ ነው አለኝ!!
ፊቴን አዞርኩ ። በዘጠና አምስት ብር ጉርሻ ሚስቴ እንደምትማግጥብኝ አረጋገጠልኝ። በስተመጨረሻ አለማመኔ ድል ተነሳ !
አይኔ የሆነውን ሁሉ ክስተት ሲያስተውል ቆይቶ አለቀሰ። እምባዬን በጉንጬ በኩል
ወረወረው እስከዛሬ ከሷ ጋ እያበረ ከስሜቴ ጋ እየተማከረ የሚወዳት የሚሳሳላት የማይዋሻት አይኔ አለቀሰባት ። ነገዬ ፤ ኑሮዬ ፤እምነቴ ፤ ትዳሬ እጣፈንታዬ ገብቶት አይኔ ብዙ እምባ አመነጨ ።
ባልተከፈተው ቢራ አጠገብ የተከፋ ልቤን አቅፌ ኩርምት እንዳልኩ አንገቴን አቀርቅሬ ድምፅ ሳላወጣ እየተንሰቀሰቅኩ አለቀስኩ ።

ይቀጥላል

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Adhanom Mitiku
946 viewsDAVE / PAPI, 17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-24 22:01:56
የመንፈስ ጭሰት ታውቃለህ? ጨሻለው!

ብዥዥዥ እሽክርክርክር ቅብዥርዥርዥር ቅብጥርጥርጥር ያደርገኛል!

አሁን አንተ ራሱ ታወዛግበኛለህ ስታወራ አትሰማኝም!!
ዝም ስትል ግን ትጮኽብኛለህ!!
....
Ribka Sisay
....
@ribkiphoto
700 viewsRibka Sisay, 19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-23 14:01:11 በጣም "ነበር" ምወዳት


ሰው እንዴት በበአለ ልደቱ በጠዋት ተነስቶ ማልቀስ ይቃጣዋል ። ያውም ወንድ ልጅ ሆኖ ፤ በቃ እንባ እንባ ይለኛል ፤ ልክ አንድ ልጇን እንዳጣች እናት ወገብህ ላይ ነጠላህን አስረህ ፣ ቃላት እንደጉድ እያዥጎደጎድክ እሪሪሪሪሪሪሪሪሪ በል ይለኛል ። ግን ማልቀስ እንዴት ነው? ፣ እንባስ አይንን ከሚያክል ግድብ እንዴት ነው አምልጦ ሚወጣው? ፣

ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም ይባላል ፤ ከልቤ ያለቀስኩበት ጊዜ አስታውሳለው ፣ ከአይኔ እንባ የፈሰሰበትን ጊዜ ግን አላስታውስም ፤ታዲያ እኔ በጨጓራ ነው እንዴ ምኖረው? (ምናልባት ለመጨረሻ ጊዜ ያለቀስኩት ይቺን አለም ስቀላቀላት ሳይሆን አይቀርም)


ያዘንኩባቸው ጊዜያት ግን አሁን ድረስ ሳስታውሳቸው እንዳዲስ ያሳዝኑኛል ፤ ማልቀስ ግን አልችልም ፣ በቃ አልችልም ፤ ውሀው እንደ ደረቀ ዥረት ፣ የኔም የእምባ ቧምቧ ደርቋል ፣ ልቤ በቢላ እንደተወጋ እየደማ እንኳን አይኔ ቅርር እንኳን አይልበትም ፣ ምን አለመታደል ነው ፣ ከአበቦች መሀል አበባ ሆነህ ሳለ እንደ እሾህ መታየት።

ሰው በሙሉ የሀዘኑ መግለጫን እንባ እያደረገ የኔ አይነቱ በነሱ ፊት አረመኔ ድንጋይ ተደርጎ ይወሰዳል። ስንት አዞ ባለበት ያንተ እንባህ ስላሎረደ ብቻ አውሬ ተደርገህ ትቆጠራለህ።

በጣም ነበር ምወዳት ፣


ስለምታምነኝና ስለማምናት ሌሎች ከሚወዷት በላይ እወዳት ነበር። ጓደኝነት በመተማመን ላይ ሲመሰረት ከምድር ከፍ ይላል ፤ መተማመኑ ሲቋረጥ ደግሞ ጓደኝነቱ እንዳይተርፍ ሆኖ ከተሰቀለበት ይከሰከሳል።

የአንድን ሰው እምነት ሰብረህ ከምትጎዳው በላይ ፣ እምነቱን እየጠበክለት ያ ሰው እምነቱን እንደሰበርክበት ሲያስብ የምትጎዳው ጉዳት ይበልጥ ያቆስላል። ከዛ የሚከፋው ደግሞ ዳግመኛ ሌላ ሰው እንዳያምንብህም ፣ እንዲያምንብህም ማድረግ እንዳትችል ያደርግሀል።

በጣም ነበር ምወዳት ፣


"ከልቤ አምንህ ነበር " ነበር ያለችኝ ። የቱ ጋር እንደዋሸዋት አልገባኝም ። እኔን ግን ምን ያክል እንደጎዳችኝ አልገባትም። በ"ነበር " ውስጥ "ከዚ ቡኋላ አይኖርም" የሚል ቃል በውስጡ እንዳለ አልገባትም።
በእርግጥ ላይኖርም ይችላል ምክንያቱም እኔ አሁንም እወዳታለው ግን.....


በጣም ነበር እኮ ምወዳት


"የእውነትህን ስትምል በማነው ምትምለው?" ብላ ጠየቀችኝ
"የማያምነኝ አይመነኝ እንጂ በማንም አልምልም ፣ ግን ላንቺ በእናቴ ሞት እምልልሻለው" ነበር ያልኳት

ለማንም እኮ በእናቴ ምዬ አላውቅም ። ደስ የማይላትን ነገር ላላደርግ 'እናቴ ትሙት' ብዬ ነበር የማልኩላት። እና የትኛው ቃል ከብዶኝ ነው እናቴ እንድትሞት ምፈቅደው?

በፍፁም ቃሌን አላጠፍኩም ፣ ከዛም ብሶ ውሸታም ቀጣፊ እስከሚያስብለኝ ድረስ መካዴን አደለም ሰው ሆኜ እሬሳ ብሆን እንኳን እንዴት አይገባኝም።

በጣም ነበር ምወዳት

"እንዴትም ብንጣላ አኮርፍሽ ይሆናል እንጂ አልለይሽም" ብዬ ቃል ገብቼ ነበር።
ግን ይሄን ቃሌን እንዳልጠብቅ ቃሉን የማይፈፅም ከንቱ ሰው አደረገችኝ ፣ ማነው አላምንህም እየተባለ እታመናለው የሚል?

በሁለት ባላ እንደተወጠረ ገመድ ሆኛለው ፣ አንደኛው ቃሌ አንዱን እንዳፈርስ ይገፋፋኛል ፣ አንደኛው ደሞ ቃሌን እንድጠብቅ ያስገድደኛል ።

መተውም አለመተውም ግዴታ ሲሆን ከምጥ የከፋ ምጥ ይሆናል። ልክ መውለድም አለመውለድም የመጨረሻ ምርጫ ሲሆን ፣ ልክ ጥፍርህን በፒንሳ እየጎተቱ ' ድምፅህን እንዳታሰማ' እንደመባል አይነት ስሜት ላይ ገብቻለው።

በጣም ነበር ምወዳት

ከዚ ቡኋላ አምንሀለው ብላ በእናቷ ብትምልልኝ እንኳን እንደምታምነኝ አላምናትም ፤ መፅሀፍ ቅዱስ ብትመታልኝ እንኳን በፍፁም አላምናትም ፤ ልክ ሳይተማመኑ እንደሚኖሩ ሁለት ሌቦች መኖርን እመርጣለው ፤ ግን በማንም የማይተካ ልቤን ከሷ ውጪ ለማንም አልሰጥም ፣ ይሄን ደሞ ማንም እንዲያምነኝ አልሻም ፤ ብቻ ግን......


በጣም እወዳት ነበር ..........................

ወደፊትም መውደዴን ሳታምነኝ እወዳታለው።

ነገ ሁሉ ዛሬ መሆኑ አይቀርም ፣
ዛሬ ሁሉ ደሞ ትናንት መሆኑ የማይቀር ነገር ነው።

(ቤካ)
@wegoch
@wegoch
@wegoch
1.5K viewsDAVE / PAPI, 11:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-20 13:37:30 ሶፊያ ትባላለች የቀድሞ ፍቅረኛዬ ነበረች። ከተለያየን በጣም ብዙ ጊዜ ሆኖናል። እጅግ ከብዙ ጊዜ በኋላ ተደዋውለን ሻይ እየጠጣን ነው። በጨዋታችን መሃል ድንገት ለምን ግን ያኔ ተውሺኝ አልኳት ። ሳቀች ፤ ስትስቅ አይኗ ይጨፈናል ። ሰላማዊ በሆነ አስተያየት ካለምንም ወቀሳ መልሷን እየጠበኩ እንደነበር የተረዳች መሰለኝ ከሳቋ መልስ "እውነቱን ለመናገር ያኔ መተው ነበረብኝ ፤ ያን ውሳኔ የወሰነችው የድሮዋ ሶፊያ ናት"። አብራሪልኝ አልኳት ከስስ ፈገግታ ጋር ፊቴን አኮስኩሼ "ጭንቅላትህ ምክንያታዊ ሃሳብ አያፈልቅም ነበር ። የማይጥምህን ሃሳብ ፤ ያልወደድከውን አቋም ነፍስህ ተረጋግታ አትሰማም ። አንተ ያልፈለከው ካልሆነ ፤ ነፍስህ ትቅበዘበዛለች ሁሌ ከአንተ የፈለቀ ሃሳብ ትክክለኛ እና አዳኝ ይመስልሃል። Soft dictator ነህ ። አምባገነንነትህ በፍቅር ስለምትሸፋፍነው እና
ያፈጠጠ ስላልሆነ በቀላሉ አይገለጥም ።
ፍቅርህ እጅ መንሻህ ነበር መከራከርያ፤መደራደርያህ፤ማፅናኛህ ፤መፅናኛህ ፍቅር ነበር ። ፍቅር ከእውነት የሚበልጥ ይመስልሃል። አንዳንዴ ፍቅር ፤ አንዳንዴ እውነት እንደየሁኔታው እንደሚበላለጡ አልገባህም ።
በበነነው በተነነው ትቀናለህ ፤ እንዳላየህ የምታልፈው ነገር የለም። ሰው ደሞ ብስለቱ
የሚለካው እንዳላየህ በሚያልፈው እና እያወቀ በሚተወው ልክ ጭምር ነው። ስሜትህን ሆነ አስተውሎትህን አሁንም አሁንም ታንፀባርቃለህ። ከፍተኛ የሆነ Emotional intelligence ይጎልህ ነበር ። በዚህ ሁሉ መሃል አንደ አሁን ብስለት መገለጫ ባይሆን ራሱ በአሁን ማስተዋሌ በጭራሽ አልተውክም ነበር። አየህ ያኔ ሙሉ ሰው ፍለጋ ላይ ነበርኩ። ሙሉ የሚባል ሰው አለመኖሩን ለመረዳት ከብዙ ነፍስ ጋር ተዋሃድኩ ፤ ጉድለት ፤ እንከን ፤ ድክመት መልክ እና ይዘቱን እየቀያየረ ሁሉም ጋር እንዳለ ብዙ ቆይቶ ነው የገባኝ ። ጉድለት ይዞ ምሉዕ ፍለጋ መባተል ያለመብሰል ምልክት ነበር። አለመብሰል ነበር ያዳከረኝ ። ትላንት የገፋሁትን አይነት ማግኘት ቀላል አይደለም ። ሶፊያ እንዲህ አልነበረችም ፤ ጭንቅላቷ ሰልቷል ። እድሜ ይሆን ፤ንባብ ይሆን ፤ ከነፍስ ነፍስ መባተሏ ይሆን ብቻ ሃሳቦቿን የምትገልፅበት መንገድ ጭምር ተቀይሯል ።
ዋነኛ የመለያየት ምክንያት ፍፁም ነፍስ ፍለጋ መባተል ነው። ለድክመቶቻችን ሁሉ ጣት
ቅሰራ እና ማላከክ ፈይዳ የለውም ! አለመብሰል ስንቱን በረከታችንን አሳጣን ።

ቸር ሰንብቱልኝ

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Adhanom Mitiku
1.5K viewsDAVE / PAPI, 10:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-15 22:40:59
አደራዬን ከበላው ቆየው! አማቼ ሲያርፉ ልጃቸውን ከእነ ልጇ ተንከባከብ ብለውኝ ነበር።

ሞከርኩ። ግን ከልጆቼ ላስበልጠው አልቻልኩም። እሷንስ እንደሚስት ሾሜያታለው።

አሁን ብበድለውም ብክሰውም ለውጥ አይኖረውም!

የአብራክ ክፋዬ ስላልሆነ ርህራሄ የለኝም!
ወዝ በፊቱ ግጥም ሲል ያንገበግበኝ ጀመር።

እናቱ እሱን እሱን ስትል የእኔን ልጆች ዘንግታለች!

በእጄ ሰበብ ሳይሆን መላ ላበጅለት።
ከተማ እንደደረስን ገብያ መሃል ወስጄ እሰወርበታለው!

ለሳምንት ድምፄን አጠፋና ደውዬ ልጅሽ ጠፋብኝ እርምሽን አውጪ እላታለው!

ትንሽ የሚያሳስበኝ ያን ስትሰማ መነጫነጯ ነው። ለነገሩ ስታኮርፍም ታምራለች!!
......
Ribka Sisay
.....
@ribkiphoto
745 viewsRibka Sisay, 19:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-12 06:52:00
ልጄ ሆይ የእውነት ከምወድህ በላይ አስበልጬ ራሴን የውሸት እወደዋለው።
አሰፍስፈው ለሚጠብቁኝ መካን ጥንዶች በገንዘብ እቀይራቸዋለው። ጥሩ ስለሚንከባከቡክ እና ልብህም ስስ ስለሆነ ቶሎ ችላ ትለኛለህ።
አታስብ መሃል አናትህን መሳም እንደምትወድና ሲደባብሱህ እንቅልፍ እንደሚጥልህ ነግሬልሀለው።
ከእኔ የሆነልህ ይሄው ነው። ይሄንንና ጥሩ ምግብ ንፁህ ልብስ ቆንጆ መኝታም ታገኛለህ።

አደራ ልጄ እንዳየሀቸው ተቀበላቸው። እኔንም እንደ እሩቅ ዘመድ ዘንጋኝ!!
.....
Ribka Sisay
....
@ribkiphoto
1.4K viewsRibka Sisay, 03:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-11 14:11:40 (ዘመነ ጁንታ በወሎ)

ክፍል 1

ጆሮ የተኩስ እሩምታን ለምዷል ፣ አይን ሬሳ እና ደምን ከቁብ አይቆጥርም ፣ አፍንጫም በየጊዜው የሚሰነፍጠው የባሩድ ሽታ ጋር ተስማምቷል፡፡ከግለሰብ ኪዎስኮች ጀምሮ እስከ መንግስታዊ መስሪያ ቤቶች ሁሉም በየፈርጁ ተበርብረዋል፡፡ ፋብሪካዎች ወድመዋል፡፡ ብቻ ያቺ የወይና ደጋዋ ውብ ኮምቦልቻ እንደ ግንቦት ዛፍ ተራቁታለች፡፡

የወያኔ ጦር (ጁንታ) ወሎን ከተቆጣጠረ በኀላ ከኮሞቦልቻ EDDC (Ethiopia Domestic Distribution Corporation) ዘርፎ የተረፈውን ስንዴና ዘይት ለኮምቦልቻ አቅመ ደካሞች በማከፋፈል ህዝባዊነቱን እያሳየ ነው፡፡ ህህህ አይ ጁንታ!! እርዳታውም ተጠቃሚ የሚያደርገው ሴቶችን እና አቅመ ደካሞችን ብቻ ነው፡፡

በህጉ መሰረት ተረጅ አቅመ ደካማ ሴቶች ከካሜራ እና ከክላሽ ፊት መደዳውን ተኮልኩለዋሉ፡፡ የርዳታው አስተባባሪ ታጋይ ኪሮስ አብረሀ መዝገብ ይዞ ትግረኛ ይሁን አማረኛ በማያስታውቅ ቋንቋ ስማቸውን እየጠራ እርዳታውን እያጋፈረ ነው፡፡ በመሀል አንዳንድ የሙስሊም ስሞችን ሲጠራ ጓያ እንደሰበረው ሰው ይወላከፋል፡፡

ልክ እንደ አብዱ ዛራቅ

ከዚህ በታች ስማችሁን የሙጠራችሁ ሰዎች ቶሎ ቶሎ አቤት እያላችሁ ወደዛ እለፉ፡፡ ብሎ ወደ ስንዴ እና ዘይቱ ክምችት ሌባ ጣቱን ቀሰረ፡፡
ወይዞሮ ዘይነባ???
"አቤት"
እለፊ፡፡
ወይዘሮ የዝናሽ???
"አቤት ጌታዬ"
እለፊ፡፡
ቀጠለ.....ወይዞሮ ነፊሳ???
"አቤት" ቀጠን ያለ የወጣት ሴት ድምፅ ነው፡፡ ካቀረቀረበት መዝገብ ቀና ብሎ አያት፡፡ ዋይ!! አንቺ ዎጣት አይደለሽ እንዴ? ምነው ሂደሽ ካንዱ ሱቅ የማትዘርፊ??? በይ አሁን ሳልቶክስብሽ ከዚ ጥፊ!! አለ በ11 ቁጥር ምልክት የተቀነደበ ቅንድቡን ከፍ ዝቅ እያደረገ፡፡
ከዛም ወደ መዝገቡ ተመለሶ..... መጥራቱን ቀጠለ፡፡
ወይዞሮ ፍሬ ወይኒ???
"ዝምምምም" መልስ የለም፡፡ ከንደገና ፊደል እየቆጠረ በሎህሳስ ድምፅ "ፈ...ር...ሒ...ን" ብሎ አስተካክሎ አንብቦ "ዋይ ፈርሂን ነው እንዴ የሚል"..... ወይዞሮ ፈርሂን? ብሎ ተጣራ፡፡
"አቤት አለሁ...አለሁ" ብላ ወደ ዘይት እና ስኳሩ ስታልፍ...ቆይ ቆይ ሙን ያስቾኩልሻል? ቆስ ቦይ እስኪ፡፡
እእእ ስሙሽ እንደ ኮንክሪት ሙሽግ አስቾጋሪ ነው፡፡ ፍሬ ወይኒ ብለሽ የማትቀይሪ ለምድን ነው??? ብሎ ትዕዛዛዊ ምክሩን ሰጠ፡፡ እሺ ጌታዬ እርሰዎ እንዳሉት ይሆናል ብላ መንገዷን ቀጠለች፡፡
እሱም ስም ጥሪውን ቀጠለ...እሺ ወይዞሮ ፏጥማ? ወይዞሮ ፏጥማ?
እድሜያቸው የገፋው እማማ ፋጡማ በሰለለ ድምፃቸው "ለበይክ ጁንታው" አሉ፡፡ የተሰበሰበው ጀማ ግማሹ በድንጋጤ ነፍሱ ባፉ ሹልክ ልትል ደርሳለች፡፡ ከፊሉ ደግሞ በማማ ፋጤ የድንገቴ ቃል የሳቅ ሳግ ተናንቆታል፡፡
ዋይ!! ......ቀና ብሎ አይኑን እያጉረጠረጠ ከፍ ዝቅ አድርጎ አያቸው፡፡ እርሶ ሊረዱ መተው ጁንታ ይላሉ እንዴ???
እንግዲያ ምንዲን ነው የሚባለው እንቶ?? ብለው ጥያቄያዊ መልስ መለሱ፡፡ ዋይ ጁንታ ማለት እኮ ስድብ ነው፡፡ አሁን ብቶኩሱብሁ የማን ያለህ ሊሉ ነው? አለ፡፡ ተግሳፃዊ ቁጣ ጋር፡፡
መገን የኔ ነገር!! በቴሌቢጅን ጁንታ ቲሉ ብሰማ እኮ ነው ጁንታ ማለቴ፡፡ ሲ...ቆይ ታዳ ጁንታ እሚባሉት ማንኞቹ ናቸው አሉ፡፡ አጭር ምርኩዛቸው ላይ አገጫቸውን አስደግፈው ግራ በመጋባት፡፡ ጁንታ ማለትማ እኛ ነን፡፡ ግን እኛ አይደለንም፡፡ እኛ ለነፃነት የምንፋለም ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ነው የምንባል፡፡ በሉ ካሁን በኃላ ጁንታ እንዳይሉ ወደዛ ይለፉ አለ ወደ ስንዴው ድርድር ቀኝ እጁን እያወናጨፈ፡፡ እሺ አፉ በለኝ ጋሽ ጁንታ ብለው ጁንታነትን ጋሼ የሚል ማዕረግ ጨምረው በድጋሜ ጠሩት፡፡ ያኔ እንደ ምጥ ሳቅ እያማጠ የቆየው ጀማ አሽካካ "ሀሀሀሀሀሀሀሀ" ታጋይ ኪሮስም ሳይቀር በእማማ ፋጤ የዋህነት አብሮ ሳቀ፡፡ ሳቁ ጋፕ ሲል መልሶ ፊቱን ቋጠረና መጥራት ጀመረ፡፡
እሺ እንግዲህ...ፀጥታ ይከበር፡፡ እእእ ወይዞሮ ካሚል ሲራጅ??? ወይዞሮ ካሚል ሲራጅ?? "አቤት" ከሰልፈኞቹ መሀል ጎርነን ያለ የወንድ ድምፅ ተሰማ፡፡ ዋይ....እኖዚ ሰዎች ምን ኖክቷቾዋል፡፡ አንተ ዶግሞ እዚህ ሙንድን ነው ሙትሰራ? እኛ ዎንድ ሞች ጠራን? የሴቶች መረሀ ግብር አይደል እንዴ??? አለ እንደ ሀምሌ ደምና ፊቱን አጨፍግጎ፡፡

አቶ ካሚል መለሰ.....ኧረ ጌታዬ እናንተ ከመጣችሁ በኀላ ምን ወንድ አለ??? ጨርሰን ሴት ሁነናል እኮ፡፡

"ሀሀሀሀሀሀሀ" የእድምተኛው ሳቅ ድጋሚ አስተጋባ፡፡

@wegoch
@wegoch
@paappii

#በመሊኩ [ MAJNUN ]
1.4K viewsDAVE / PAPI, 11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 10:50:15
ያ ደግ ከመወለዱም በፊት በፅልመት ነበርን።

ሲወለድም የእልልታችን ድምፅ ሻክሮ ነበር።

ፍንደቃችንም ተቀዛቅዞ። ንጉሳችንም ደነበረ።

ጨቅላዎቻችንን ደጉን ለመጉዳት ሲል ቀጠፈ።

ከግዜያት በኋላ ግን ከደጉ የተሻለ ደስታ አልነበረንም።

ባለፈበት ሁሉ ሳር ቅጠሉ ይቦርቅ ጀመር።

እኛም ስለክብሩ ዳንኪራ ባንረግጥም ስናየው የውስጥ አካላችን ይዘል እና እልልልልልልልል ይል ነበር።

ከተማይቱ በደስታ አቅሏን ስታ ነበር።

ምክንያቱም ደጉን የመሰለ ንጉስ አብሮን ነበርና።

ማንም ሰውም ብቻውን አልነበረም። የሚስቅ እንጂ ከንፈሩን የሚነክስ ሰው አልተገኘብንም።

ፅልመቱም ተገፎልናል።

ስንራመድ እኛን የሚመስል በሄድንበት የሚሄድ በብርሃን የተበጀ የደጉ መልዕክተኛ ይጠብቀናል።

ኦ ደጉ ሆይ ስለተወለድክ አመሰግንሃሁ!

ኦ የደጉ እናት ሆይ እወድሻለሁ !

ኦ የደጉ ተንከባካቢ ሆይ አከብርሃለው!!

.........
የደጉ ጌታችን ልደት መልካም ልብ የምናተርፍበት ይሁንልን!

......
@ribkiphoto
1.3K viewsRibka Sisay, 07:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 09:46:15 (ፋራ ነኝ)

በመሊኩ [ MAJNUN ]

ከወሎ ኮምቦልቻ 23 ኪሎ ሜትር እርቀት ላይ የምትገኘው ደሴ ከተማ ከኢትዮጲያ ቀደምት ከተማዎች ውስጥ ግንባር ቀደም ነች፡፡ ኮምቦልቻም ያው ስሟ እንደ ደሴ ባይገንም ቀደምትነቷ እና ድሙቅነቷ እሙን ነው፡፡ ከጂኦግራፊ ቀረቤታዊ አቀማመጣቸው እና ከማህበራዊ ስሪታቸው ፣ እንዲሁም ከኢኮኖሚ ትስስራቸው አንፃር መንትዮቹ የሚል ቅፅል ስምም ተችሯቸዋል፡፡ ባንድም በሌላም መልኩ ግን የደሴ ስም ከኮምቦልቻ ይልቅ መናኘትን ተጎናፅፏል፡፡ አንዳንዶች ለደሴ ድምቀት እኛ ወሎዬዎች "የወሎ ሀፍረት"!! ብለን ስሙን ልንጠራው የማንሻውን የልጅ ሚካኤል(ራስ አልይ/መሀመድ አልይ) መንበር መቀመጫ መሆኗን እንደ አንድ አመክንዮ ያነሱታል፡፡

ብቻ ከድሮ ጀምሮ ደሴ የወሎ መዲና ነበረች፡፡ ባሁነኛውም የፌደራሊዝም ስረዐት ከወሎ መዲናነቷ ዝንፍ ሳትል እንደ ደመቀች ፣ ተጀብና ተከሽና ፣ አለች፡፡ ወደ ወሬዬ ልመልሳችሁ... ጁመዐ ማለዳ ከኮምቦልቻ ወደ ደሴ መንገድ ትራንስፖርት የሞተር ሳይክል ታርጋ ለማውጣት ማልጄ ወጥቻለሁ፡፡ ያው የደቡብ ወሎ ዋና ከተማ እንደመሆኗ መጠን ገዘፍ ያሉ መንግስታዊ እና ግለ-ሰባዊ ድርጅቶች መገኛም ነች፡፡ ከተለያዩ የወሎ ክፍለ ሀገሮች ግልጋሎት ለማግኘት ብዙ ሰዎች ስለሚመጡ ጉራው (ወረፋው) እንደ አንቻሮ ገበያ ደመቅቅቅቅቅ ይላል፡፡ በዛ ላይ መመላለስ ከያዝኩኝ ሳምንት ሆኖኛል፡፡ ለዛም ነው የደሴን ብርድ ሳልፈራ ማልጄ የወጣሁት፡፡ ብዙ ሰዉ ከሩቅ ሀገር ስለሚመጣ ላለመቆየት እና ላለመስተጓጎል ሲል ሙስና እየሰጠ ጉዳዩን ያስፈፅማል፡፡ እንደ እኔ አይነቱ ደረቅ አራዳ ደግሞ ሳምንት ታሽቶ ይሸኛል፡፡ ያም ገዱ ካማረ ነው፡፡

አቤት በየመስሪያ ቤቱ ያለ ሙስና እና ዘረፋ!! አሁን አሁንማ የምግቤት ስጋ ቆራጮችም ሳይቀር ሙስና ለምደው ደምበኛ ለይተዋል፡፡ ስጋ መብላትን በረጅም የእቅድ ፕላት ፎርሙ አካቶ በወር አልያም በአመት አንዴ የሚበላን ገሚስ ሀበሻ ሙስና ያልከፈለ እንደሁ አንጆ እና ጣንፊያ ያቀርቡለትና ከአንጆና ጣንፊያው ጋር የስጋ ቆራጩን ስጋ በልቶ ይወጣል፡፡ ብቻ በኛ ሀገር ውስጥ የሙስና እና የዶላር እድገት እንደ ፈረንጅ ልጅ ሆኗል፡፡ ኧረረረ የደሴ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ግን ይለያል፡፡ ደግሞ እኮ የሚገርመው ካንዱ የግድግዳ ጥጋት ከመስሪያ ቤቱ መተዳደሪያ ደንብ ዝርዝር ዝቅ ብሎ "በግርግር ውስጥ ኪስዎን ከሌባ ይጠብቁ" ፣ "ሙስናን በጋራ እንከላከል" ብለው ለጥፈዋል፡፡ ህህህ ቀልዳቸው እኮ አይጠገብም፡፡

አንዱ ሰራተኛ ከሰኞ ጀምሮ ጥርሱን ስሎ ሊበላ ሲያሰባኝ...ሲያሰባኝ ነገ ዛሬ እያለ ይሄው ሳምንቴ መጣ፡፡ በመጨረሻም ምርር ብሎኝ ወደ አለቃው ይግባኝ ብዬ ሄድኩኝ፡፡ አለቃውም ከኔ ሀልጋ ከፍ ከክላሴ ዝቅ ያለ ተሽከርካሪ ወንበሩ ላይ ቁጭ ብሎ "ምን ልርዳህ"? አለኝ የነፍሰጡር ሆድ የመሰለ ቀፈቱን እያሻሸ፡፡ ካነጋገሩ የወደላይ ሀገር ሰው (ጎጃሜ) ይመስላል፡፡ ኧረ እንደው ጌታዬ እባክዎትን ቢሮ ቁጥር 8 ካሰሩት ጅብ ያድኑኝ፡፡ እእእ ... ማለቴ ቢሮ ቁጥር ስምንት ያለው ባለ ሙያ ከስራ ዲስፕሊን ውጭ የሆነ አላግባብ ክፍያ ካላመጣህ ብሎ እያስተጓጎለኝ ነው አንድ ይበሉልኝ፡፡ አልኩኝ ሙስና ማለት ፈርቼ፡፡ "እህ እህህህ" ብሎ ጉሮሮውን ጠራርጎ ከተገደፈበት ወንበር ቀና አለና እሺ እንግዲህ ችግር የለውም፡፡ ወደዚህ መምጣትህ ጥሩ አድርገሀለል፡፡ አሁኑኑ ባስቸኳይ ቶሎ እንዲሰራለህ አደርጋለሁ፡፡ እንደውም ልደውልለት ብሎ ስልኩን አንስቶ መታ "ለካ ከጅቦች መንጋም እንደዚህ አይነትም ቀና ሰው አለ" ብዬ በእዝነ ህሊናዬ ስብሰለሰል "እህእህህህእ" ብሎ በዳግማዊ ጉሮሮ ጥርጊያ ከሀሳቤ መለሰኝ፡፡ እሺ ይሄው ደውዬለታለሁ፡፡ በቶሎ ይሰራልሀል አለኝ፡፡ ከተቀመጥኩበት ወንበር ተነስቼ ለቀናነቱ አላህ ይስጥልኝ ብዬ አመስግኜ ልወጣ ስል ሰልሶ ጉሮሮውን ጠራረገና ታዳ የደንቡን ውረድ እንጂ አለኝ፡፡ የደንብ? የደንብ? የደንብ ምን ነበር? አቤት??? አልኩኝ ግራ እየተጋባሁ፡፡ ቶሎ እንዲሰራልህ ላደረኩበት የሻሂ አምጣ ብሎ የደንብን ትርጓሜ ፈሰረልኝ፡፡ እህህህ??? የደምብ ማለት ሙስና ነው እንዴ? እዚህም ሙስና??? አልኩኝ ከፊቴ የተቀመጠው መልአክ በቅፅበት ወደ ትልቅ ጅብነት ሲቀየርብኝ ደንግጬ፡፡ ጉድ እኮ ነው!! በር ላይ ያነበብኩት የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች መተዳደሪያ ደንብ ላይ ሙስና የሚል ደንብ አላየሁም፡፡ ወይስ ሙስናም ህገ መንግስቱ ውስጥ ካለተፃፉት ህጎች ውስጥ አንዱ ሆኖ ኖሯል??? ከተኛበት አልጋ ላይ ማለቴ ከተቀመጠበት ወንበር ላይ ተነስቶ "ዉጣ!! የማነው ፋራ" ብሎ አምባረቀብኝ፡፡ ለካ አስር ግዜ ጉሮሮውን ሲጠራርግ የነበረው ይሄ ትልቅ ጅብ ጠቦት አገኘሁ ብሎ ሊበላኝ አስቦ ኖሯል፡፡ ሆሆሆ ሳይመታኝ ተነስቼ ልውጣ ብዬ ሾከክ እያልኩ በገባሁበት በር ወጣሁኝ፡፡ ከግቢ ውጭ ላንድ አፍታ ቆም ብዬ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ሳስብ ከመንገድ ትራንስፖርት ጀርባ ካለው ፀረ ሙስና ኮሚሽን ሄጄ ማመልከትን ሁነኛ መፍትሄ ብዬ ዘየድኩኝ፡፡ ወደ... ፀረ ሙስና ኮሚሽን፡፡

ፀረ ሙስና ኮሚሽን ደርሼ ወደውስጥ ዘልቄ ገባሁ፡፡ ግቢው በር ላይ የፖሊስ ፓትሮል ቁሟል ፣ አልፎ አልፎ ክላሽ የያዙ ፖሊሶች ተገትረዋል፡፡ እነሱን አልፌ ወደ ህንፃው ሳንቃ ስጠጋ ሰራተኞቹ ውጭ ላይ ይተራመሳሉ፡፡ ግራ ገብቶኝ እንደኔ ፋይል ይዞ ግራ የገባውን አንዱን ባለ ጉዳይ ምን እንደተፈጠረ ጠየኩት፡፡ የመስሪያ ቤቱ ሀላፊ በሙስና ወንጀል እጅ ከፍንጅ ተይዞ ወደ ፖሊስ ጣቢያ እየወሰዱት እንደሆነ ነገረኝ፡፡ እርፍፍፍፍፍፍ አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው አለ!! የፀረ ሙስና ኮሚሽን ስራ አስኪያጅ የሙስና ልማት አስኪያጅ ሆኖ ተገኘ፡፡ ጉድ አትሉም!! ሰዐቱ 10:30 ገደማ ደርሷል የደጋማዋ ደሴ ብርድ ከንፋስ ጋር እያፉጫጨ ነው፡፡ ከዛ በኀላ መቆየት አንደ ታይታኒኩ ጄያክ የብርድ ሲሳይ መሆን ነው ብዬ ወደ ወደ ኮምቦልቻ መሄድ ወሰንኩኝ፡፡

የምሽቱ ግር ግር ደሴ ላይ ደርቷል የደሴ ውብ ቀዘባዎች ወ ሸበላዎች ባስፓልቱ ላይ ይገማሸራሉ፡፡ የሸርፍ ተራ ወዝ አደሮች ጥፍንግ ቦንዳ ተሸክመው መንገድድድድድድ እያሉ እየጮሁ ይሮጣሉ፡፡ ወያላው ይጮሀል ፣ የመኪናው ጡሩንባ ያናፋል.... እኔ የሳምንት ልፋት ፣ ብክነት ፣ ቁጭት ፣ ብስጭት አዝሎኝ ወደ መናሀሪያ እራመዳለሁ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር የታክሲውን ሻተር ከፍቶ አንዱ ረዳት ኧኧኧ ቧንቧ ውሀ ነህ? ያለኝ፡፡ አይደለሁም ብዬው አለፍኩ፡፡ ሌላኛው እረዳት ፀጉሩን እየገመደ ኧኧኧ አባት አራዳ ነህ አለኝ፡፡ ዝም ብዬው አለፍኩ፡፡ እኔ ለራሴ ደክሞኛል ምን ይጨቀጭቁኛል ጃል!! ኧኧኧ አራዳ ነህ ብሎ ደግሞ ጠየቀኝ፡፡ " አሁንም ዝም" ሰውዬ ጆሮ የለህም እንዴ? አራዳ ነህ ወይይይይይ??? ያ...ረቢ ኑባሲ!! ሰውዬው የሚፋታኝ ነገር አይደለም፡፡

መለስኩለት............አይ ፋራ ነኝ፡፡


ህህህ አበቃ፡፡


@wegoch
@wegoch
@wegoch
1.4K viewsDAVE / PAPI, 06:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-04 08:38:34 ቁንጅናዋ ብዙ ሰው የሚስማማበት አይነት ነው ። ቆንጆ እንደሆነች ታውቃለች ፤ ግን ቆንጆ
ስትባል ደስ ይላታል።
ሴት ልጅ በየትኛውም እድሜ ቆንጆ መባልን አትጠላም ። ሴት ልጅ መደነቅ ድክመቷ ነው
መሰለኝ። በእርግጥ መደነቅ እና ትክክል መባል የሰው ሁሉ ድክመት ይመስለኛል።
ምንም እንኳን የገላዋ አሰራርም ለአድናቆት እንዲመች አድርጎ ያበጃጃት ቢሆንም
ሴቶች በሚወዷቸው እንደማይጨክኑ ፤ ኤልዳና እኔን እንዳላገኛት መንገድ አለመዝጋቷ
ምስክር ነው ።
እኔ ሞኝ የምባል አይነት ሰው ነኝ መሰለኝ። ለቀልድ እንኳን ሞኝ ስባል አራስ ነብር
የምሆነው ፤ በቃ ክፍ....ት ነው የሚለኝ ።
ሞኝነት ድክመቴ ባይሆን ሞኝ ስባል እስቅ አልነበር ? አሁን ቀጫጫ አይደለሁም ፤ ቀጫጫ
ብባል ግን እስቃለሁ እንጂ አልናደድም ስለዚህ ሞኝ ነኝ ማለት ነው እላለሁ ፤ አንዳንዴ
ደግሞ እንደዚህ ከተመራመርኩ እኮ ሞኝ አይደለሁም እላለሁ
ዘይገርም
አንዳንዴ ሰዎች ጭንቅላቴ ስል ሲሆንባቸው ትኩር ብለው ያዩኛል ። በቂላቂልነቴ save
አድርገውኝ ባይሆን ኖሮ እንዴት እንደዚህ አሰበ ብለው ሲገረሙብኝ አይናቸው ላይ መች
አስተውል ነበር !?
ሰው ድክመቱን ባያሻሽለው እንኳን ጥንጥም ይገባዋል ማለት ነው ፤ ያ ማለት ደግሞ he
might be denying the hard fact deliberately ።
ኤልዳና ጋ ብዙ ቀን እደውላለሁ ፤ ኤልዳና ሲሻት ብቻ ስልኬን ታነሳለች ። ከደወለችልኝ የሆነ
ነገር ፈልጋ ነው ።
ቢሆንም ደስስ ይለኛል
ኤልዳና ከእኔ ጋ ስታወራ አወራሯ ፆታዊ ነገር የለውም ፤ መሽኮርመም ሆነ ደርባባነት
አይታይባትም ፤ ምንም ፆታዊ ፍላጎት ስለሌላት ይሆን ?
አላውቅም !
አግኚኝ ስላት ሀገር እንደምታስተዳድር አይነት ነው ባተሌ መሆኗን የምትነገርኝ። የግል
university እያስተማርኩ ፤ ትልቅ ፕሮጀክት እየመራሁ እኔ እንኳ እንደእሷ ስለመባተል
አላወራም ።
ተሳክቶልኝ ኦር ፈልጋኝ ያገኘችኝ ጊዜ...
ነፃ መሆን አልችልም ፤ አክብጄ ስለማያት ጨዋታ አይመጣልኝም ።
ባገኘውት አጋጣሚ ቀልቧን ለመሳብ እባዝናለሁ ።
በቃ እዛው ከእኔ ጋ እያለች ከሌላ ሰው ጋ ስልክ ታወራለች ። ፊቴ ለምታወራው ወንድ ሲሆን
ደግሞ ደርበብ እሽኩርምም ስትል አስተውላለሁ ፤ሞኝ ስለምመስላት ይሄን የምረዳ
አይመስላትም ወይም ሳይታወቃት በደመ-ነብስ ነው ሁኔታዋ እና አነጋገሯ የሚቀየርባት ።
አንዳንዴ 'ለምንፈልገው ነገር አድራጎታችን ከእውቅናችን ውጪ ይሆን የለ' ።
ትንሽ ለመጫወት እሞክራለሁ ፤ ቀላል ወሬ ታወራልኛለች
ከዛ
የማይመለስ ብር ትበደረኛለች ፤ ከዛ እንቅ አድርጋ ትስመኛለች ደስስስስስ ይለኛል።
ጓደኞቿ ጋ ሆና ካገኘኋት በጣም እንደምወዳት እሷ ደግሞ ከምንም እንደማትቆጥረኝ ፤
ለብቻቸው የነገረቻቸውን በማስረጃ እያጣቀሰች እና እየቀለደችብኝ ታሳየቸዋለች ፤ እነሱ
ደግሞ አምነንሻል ፤ ገብቶናል ለማለት ያሽካካሉ።
አሁን እንደው የሚወደን ሰው ላይ እማኝ አስቀምጦ ማልመጥ ምን የሚሉት ስልጣኔ
ነው?? !!
ኮትህን የት ገዛኸው አለቺኝ አንድ ጓደኛዋ ሽሙጥ እንዳልሆነ እንዳያሳብቅ ፊቷን
እየተቆጣጠረችው
አይን አይዋሽ አይኗ ያስታውቃል ፤ ለበኋላ
የሚሆን ቧልት እያድቦለቦለች ነው
ዝም አልኳት
አሁን ሰው መርጦ እና ወዶ በለበሰው ኮት የለበሰው ሰው ፊት ማላገጥ ትክክል ነው??
ጓደኞቿ እኔ ላይ ያላቸውን ንቀት ወላጇ
የምወዳት ኤልዳና መሆኗን ነጋሪም መስካሪም አያስፈለገኝም
ተሰብስበው ሳገኛቸው ከሚጨንቀኝ ነገሮች አንዱ እጄን የት እንማደርገው ነው ። ኪሴ
ውስጥ እከተዋለሁ ወይ አጣምራለሁ ፤ አልያም የግራ አና የቀኝ ጣቶቼን አቆላልፋለሁ ፤
በእሱ ራሱ ይቀልዳሉ ።
ፍቅር ተአምራዊ መሆኑ ማሳያዬ
ይሄ ሁላ እየገባኝ አለመሸሼ
እኔ ለእሷ ክፉ አይደለሁ ። ከሁሉም ሰው በላይ ስለምወዳት አይደል የተበደረችኝን
እንደረሳሁ ሆኜ ሌላ ቀን እንደገና የማትመልስልኝን ገንዘብ የማበድራት ፤ ለዛውም ላይ ታች
ብዬ የማመጣውን ገንዘቤን !!
መውደዱ የእውነት እንደሆነ የሚታወቅ ሰው ላይ ይሾፋል???
ሰው ላይ መቀለድ አራድነት ነው ???
ስለማታውቀኝ ነው እኮ
ማጣጣል እንደማይጥለኝ ፤ ስንቴ በትግሎቼ እንደወደቅኩ ፤ ወድቄ ሳለሁ ቆሜ
ስለምታገለው እንደማሰላስል !
ለዚህ ነው ይሄ ሁላ ነገሯ እየገባኝ
ጊዜ ሃያል ነው ፤ አይኗ ሲከፈት ሞኝነቴ ጥበብ እንዳለው ትረዳለች ብዬ መጠበቄ።
የድንቁርናዋ ምንጩ አለማስተዋል እንደሆነ የምረዳላት።
ከብልግናዎቿ መሃል መልካምነቷን ለራሴ እንደምነግር አልገባትም ።
ክፉ ቀን ቢመጣባት አብራ ከምታላግጥብኝ ጓደኞቿ የበለጠ እንደምረዳት ፤ ከአጠገቧ
እንደማልጠፋስ አልገባትም ።
ሰው በረከቱ ላይ እንዴት ያላግጣል ? መወደድ በረከት አይደለምን?
ፍቅር የሚወዱንን ብቻ መውደድ አይደለም ።
ለዛ ነው የምወዳት። የቀን ጉዳይ ነው እንጂ ፍቅሬ አንድ ቀን ይጋባባታል ።
ያ አንድ ቀን እንዲመጣ
ትላንት ባልሞከርኩት መንገድ መምጣት አለብኝ ። ለተመሳሳይ አወዳዳቅ ተመሳሳይ
የአተጋገል ስልቶች ምክንያት ናቸው ። ጥበብ ማለት የሚፋለመንን መረዳት ብቻ ሳይሆን
መቅደምም ጭምር ነው። ከትላንት የተሻለ ውጤት መጠበቅ ያለብኝ ትላንት በሄድኩበት
መንገድ ካልመጣሁ ብቻ ነው ።
ማስታወሻ ፦
እጅ መስጠት ውስጥም ደማቅ ድል አለ!!!

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Adhanom Mitiku
1.6K viewsDAVE / PAPI, 05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ