Get Mystery Box with random crypto!

ወግ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @wegoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.51K
የሰርጥ መግለጫ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @leul_mekonnen1

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 26

2022-04-01 21:57:41
ለረመዳን እመጣለው አብረን እናፈጥራለን።

አላህ እራሱ ዱዓዬን የሚሰማኝ ከጎንሽ ስሆን ነው።

Ramadan Kareem Habibiti

................................

Ramadan Kareem Beteseb!
................................
@ribkiphoto
@wegoch
@wegoch
23.2K viewsRibka Sisay, edited  18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-26 12:22:24 አያቴ ረጅም ናት : ድሮ ያኔ ትንሽ ልጅ ( ትንሽ ልጅ ሆኘ አውቅ ነበር ?)
እና ያኔ እንግዲህ አጠገብዋ ቆሜ: ቀና ካልኩ : ሽንሽን ቀሚስዋን ገፋ ያደረገ ሆድዋ:
ከወገብዋ በላይ እንዳላይ እየጋረደኝ አንገቴን ወደ ላይ ሰቅየ : አገጨን ወደ ሰማይ አሹየ :
ሳይት : ሳያት አታልቅም ።
ጥቂት እራቅ እልና : እዚያ እ- ላ--ይ የደረሰ አንገትዋን አሻግሬ ፊትዋን እመለከታለሁ ።
ደርባባ ወይዘሮ ናት ። ቀሚስዋ እስከቁጭምጭሚትዋ ይደርሳል ።
አያቴ ?!
አቤት
ቀሚስሽ ለምን መሬት ይደርሳል ?
ረዝሞ ነዋ የኔ ልጅ ።
ታዲያ ለምን ረዘመ : እም ለምን እንኳን አታሳጥሪውም?
ካጠረ ነፋስ እንዳይገልጠኝ ብየ ነዋ ልጄ ።
ነፋስ ቢገልጠው ምን ይሆናል?
እህ! እንዲህ ናትና የዳውዶ መሃመድ ልጅ !
ሴት ልጅ: ንፋስ ቀሚሷን ገልጦባት :
ጭኗን ለመንገደኛ: ከሚያስጎበኝባት
ካፍንጫዋ ሥር : ንፍጧ ቢታይ ይሻላታል ።
አያቴ ምን ነው ያልሽው ?
ወዲህ ነው ልጄ
ወዲህ ? ወዴት ? ምኑ ?
ተይው ልጄ
ምኑን ነው ምተወው አያቴ ?
እርቦሻል እንዴ የኔ ልጅ ? ትላለች በሃዘኔታ
እምምም--- እርቦኛል እንዳልል አልራበኝም : አልራበኝም እንዳልል ደግሞ : ጓዳ ውስጥ
ያለ ወይ ቋንጣ ፣ ካልያም አይብ ፣ ወይ ቃተኛ ፣ ጭኮ ብቻ የሆነ ጎትታ የምታመጣቸው
ድብቅ ጣፋቅ ስንቆች አንዱ: እንዲያመልጠኝ አልፉልግም ።
"አልራበኝም ግን እበላለሁ ።" እላታለሁ ።
አዎ ልጄ: ልጅ ሆዴን አመመኝ እንጂ' ጠገብኩ ' አይልም ።--- እያለች ጓዳ ውስጥ ገብታ :
ከሆነ ቦታ የሆነ ነገር አንጎዳጉዳ: በትላልቅ መዳፎችዋ እና በእረጃጅም ጣቶችዋ የታፈሰ:
አንድ ሠሃን የሚሆን ቆሎ ይዛ :
'ዘርጊ እጅሽን ":- ትለኛለች ።
ዝርግት -
ውውውይ --- ትላለች አጫጭር ጣቶቼን ትንሽየ መዳፌን አይታ
"በቃ በቀሚስሽ ያዥው ። "
ቀሚሴን ከፊት በኩል እስከ ላይ ድርስ ስጎትት ---
"" አይ አይ ምነው--- " ብላ ሳጥኑን ታያለች ።
ከሳጥኑ ውስጥ ሰሃን አውጪ ልትል ፈልጋ ግን አንደበትዋ ተያዘ ።አላመነችኝም ። ሠሃን
ሲሰበር አትወድም የብረት ሰሃንዎችዋን መስጠት አትወድም ።
በይ በቀሚሽ ያዥዋ እንግዲህ። ትለኛለች።
እንደገና ቀሚሴን ከፊት በኩል ይዤ ወደ ላይ በሁለት እጄ አጥፍና : በቀሚሴ ጨርቅ :
ዘምቢል መሳይ የጨርቅ ጉድጓድ እሰራለሁ።
የተገለጡት ጉልበቶቼ እየታዩ : ቆሎውን እቀበላታለሁ ።
በማር የታሸ ሠነፍ ቆሎ ነው ቁርጥም አርጊያት እስኪ --- ትላለች።
አያቴ ቆሎው ግን ለምን ሰነፈ ?
ምንማለትሽ ነው ልጄ ?
ቆሎው ለምን ጎበዝ አይሆንም ነበር?
እርቦሻል እንዴ ልጄ ?
ሌላ ምን ልትሰጠኝ ይሆን እያልኩ
"አልራበኝም ግን እበላለሁ" አልኩ ።
እርቦሻል የኔ ልጅ : ሰው ሲርበው ነው ጥያቄ የሚያበዛው ።
ትለኛለች ።
የተገለጡ ጭኖቼ ሳያሳስቡኝ ቆሎየን ከነጨርቄ በአንድ እጄ ጨብጨ በሌላኛው እጄ:
ለጊዜው ኪስ ሆኖ በሚያገለግለው : ቆሎ ባዘለው የፊት ለፊት ቀሚሴ ጨርቅ ውስጥ
ያለውን ቆሎ እየዝገንኩ ፣ እየቆረጠምኩ ሌላ የጓዳ ሲሳይ እጠብቃለሁ ።
ግን በምን እይዘዋለሁ ? አያቴ ግን ለምን ሰሃን እትሰጠኝም ?
አያቴ
አቤት
ጭኔ እኮ ግን እየታየ ነው ። አልኩ በማስተዛዘን
አያቴ ጓዳ ውስጥ ሆና --- በረጅሙ ትመልሳለች
እህም- ይታያ :- የታየ እንደሆን ምን እንዳይሆን ? !

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Abeba Birhanu
1.4K viewsDAVE / PAPI, edited  09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-25 22:54:18
#ጦቢያ

#ዝክረ_አድዋ ልዩ ፌስቲቫል አድዋን በጦቢያ መድረክ ያድምቁ

በነፃ ሀሳብና በሰከነ መንፈስ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን እናድምቅ!

የመግቢያ ትኬት በሁሉም የቡና ባንክ ቅርንጫፎች ይገኛል።

የመግቢያ ዋጋ 200ብር
ለበለጠ መረጃ 0919787878

በነገራችን ላይ እኔም ስራዎቼን ይዤ እኖራለው
388 viewsRibka Sisay, 19:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-22 07:07:04
ሥዕል በማሳል ለ ወዳጅ ዘመዶ ስጦታ ያበርክቱ
በ+251984740577
ወይም @gebriel_19 ላይ ፎቶ በመላክ በ ተመጣጣኝ ዋጋ ማዘዝ ይችላሉ!
#ሥዕል_ብቻ የቴሌግራም ገፅ


@seiloch
@seiloch
1.3K views ገብርዬ, 04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-19 21:18:49 ድሮ አምስተኛ ክፍል ሳለን እርስ በርሳቸው የሚፎካከሩ ሁለት ዲያቆናት ነበሩ። ከአብነት ትምህርት የጀመረ ፉክክራቸው ወደ ዘመናዊ ትምህርቱም አምጥተውት ነበር። በተለይ የሽምደዳ ትምህርቶችን የሚችላቸው አልነበረም። ልጅ እያሱ የት ተወልዶ.. .የት እንደሞተ ከነቦታው ከነ ዓመተ ምህረቱ ዱቅ ያደርጉታል። (በነገራችን ላይ አንድ ቀን ልጅ እያሱ ሀይቅ ዳር ተቀምጠው ሲፍታቱ መኮንኖች ከሩቅ ሾፏቸው ። ያን ጊዜ ልጅ እያሱ በርጫ እያደቀቁ ብን ብለው በምርቃና ፏ ብለው ነበር። ከዛ በኋላ ቤተ መንግስት አካባቢ ልጅ እያሱ የእስላም ቅጠል ያላምጣሉ ተብሎ እንደተወራባቸው ታሪክ ይናገራል ልጅ እያሱ አንቱ ለመባል የማያበቃ ልጅነት ነበራቸው። ሀገራችን በዘመኗ ካጋጠሟት የህፃን ባህሪ ካላቸው ንጉሶች ቀዳሚውን ቦታ ይወስዳሉ። በተለይ ጢዝ ያላት እንስት ካዩ ቅቤ እንደላሰ እባብ ይቅበዘበዛሉ ይባላል ። ብዙው የንግስና ዘመናቸው ላይ ሲወሸክቱ ራስ ተፈሪ በርቀት ይጠባበቋቸው ነበር። ራስ ተፈሪ ቤተስኪያን ተመሳም አንስቶ በቤተ መንግስት ዘንድ እጅግ የተወደደ ምግባር ነበራቸው። በንግስና ዘመናቸውም ትንሽ እንኳ ሳት ብሏቸው ከማጀት ሴቶች አንዷን ቢመቻቹ ለፀፀት ቅርብ ናቸው። ከአልጋ ወርደው ደበሎ አንጥፈው ጌታ ሆይ አፉ በለኝ ይላሉ በፍጥነት። ልጅ እያሱ ግን አንዷን ቆንጆ እየቀመሱ የሌላዋ እንስት ገላ ያሻፍዳቸው ነበር )

ወደ ዲያቆናቱ ልመለስ.. .

እንዳለ ተብየው አንዲት ሸጋ ወዶ ጠየቀ። መጀመሪያ ይሄ የማርተሬዛ ሽልንግ የሚደብቅ ተረከዝህን አለስልስ ብላ ኩም አደረገችው ቆንጆዋ!

እንዳለ ከዚህ የሞራል ስብራት በኋላ ሰይጣን በጆሮው አንድ በቀል ሹክ አለው።

ጱጵ የሚል ድምፅ ከጎናችን ሰማን ። ደግሞ ለክፋቱ እኔ ከቆንጆዋ ልጅ ጎን ነው የተቀመጥኩት። ቆንጆ ይፈሳል ተብሎ ስለማይገመት ተሜው ሁላ አይኑን አጉረጠረጠብኝ። አፍንጫዬን በሹራቤ ስሸፍን ደግሞ ከሱ ብሶ ፈስ እንደሸተተው ሰው አፍንጫውን በጨርቅ ይሸፍናል እንዴ? ተባልኩ...ከ አምስት ደቂቃ ለጥቆ ቆንጆዋ ልጅ ሌላ ጋዝ ለቀቀች። ከመቅፅበት ደንግጣ ክፍሉን ለቃ ሮጠች። ዞር ስል ደብተራው እንዳለ ሆዱን እስኪቆርጠው ድረስ ይስቃል።

የፈስ ድግምት ለቆባት መሆኑ ያኔ ገባኝ :)

በዚህ እውቀቱ የቀናው ደብተራው ሸዋ ሌላ ጉድ ይዞ ከተፍ አለ ። 

የበቀል በትሩ አንዲት ምስኪን መምህራችን ላይ አረፈ ። ቲቸር አስካል መክራን ዘክራን አልሰማ ስላልናት ብዙ ጊዜ በአርጩሜ መከራችንን ታበላናለች። ተማሪው ግርፊያዋን ስለሚጠላ እሷንም አብሮ አይወዳትም ነበር። በተለይ ሸዋ ... የክፍል መልመጃ 3/10 ስላመጣ ክፉኛ ጥርስ ነክሶባት ነበር ። የታሪክ ትምህርትን እንደ ውሀ የሚጠጣው ጎበዝ ተማሪ የሂሳብ ትምህርት ግን አናቱን እንደ ሀበሻ አረቄ ይነካዋል። 

በተለይ ማካፈል የሚባል ስሌት በቀን ሶስት ጊዜ አስረድተውት በቀን አስራ ሶስት ጊዜ ይስታል

አሁን በምን ተዓምር ነው 19 /12.... 21 የሚመጣው ። መምህራችን በአዕምሮህ ነው ወይስ በእግርህ አውራ ጣት አስበህ ነው ይሄንን ውጤት ያመጣኸው ብላ ስትጣይቀው.. ." በ 16 ኪዳነምህረት ነች ። በ12 ሚካኤል ነው። እመቤቴንስ እንዴት ረሳታለሁ?" አለ አሉ
በዚህ ጥርስ የነከሰው ሸዋ ዛዲያ አንድ ከሰዓት ላይ አደናግር ድግምቱን አነብንቦ ክፍል ውስጥ እንትፍ እንትፍ አለ።

ቲቸር አስካልዬ እጇ ቄጠማ ሆነባት። እግሯ እንደ ህልም ሩጫ አልታዘዝ አላት።  ጠመኔው ተሰሌዳው እንዴት ታዋህደው?

አይነ አፋር ነች አይነ አፋርነቷ ጎልቶ አንገቷን ደፋች ።

ደግሞ ለዛን ቀን ያለወትሮዋ እንኳን ሂሳብ ዓ ነገር መፃፍ አትችሉም ብላ አማርኛም እያስተማረችን ነበር።

አማርኛ ብላ ለመፃፍ አገርኛ ብላ ስትፅፍ ሳቅንባት ። የግንባሯ ላቦት ተንዠቀዠቀ ። መልሳ መልመጃ ን ለመፃፍ መግለጫ ብላው አረፈች። ከተማሪው ሁሉ የሸዋ ሳቅ ጎልቶ ተሰማ ።

መጨረሻ ላይ የሰራችው ስህተት ሲታከል ደግሞ ክፍሉ በሙሉ እንደ አደዋ ማስጀመርያ መድፍ አጓራ!

አንብቡ አለችን ዓ ነገር ጥፋ.. .

ምድረ ውሪ ተሰሌዳው የጣፈችውን ጥሁፍ እኩል አነበበው።

"አበበ በሶ በዳ !"

ድንጋጤ ጨው አደረጋት ። የፃፈችውን ዞራ አነበችው ።

ቂ....ቂ...ቂ ...ቂ...ቋቂ

ሸዋንም ሳቁንም እኩል ጠላኋቸው :)

ሚካኤል .አ 

@wegoch
@wegoch
@paappii
1.0K viewsDAVE / PAPI, edited  18:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-17 07:31:07 @wegoch
@wegoch
@mehalu_aynegerm
1.3K viewsDAVE / PAPI, 04:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-17 07:31:07 ታሪክሽን አይቀይረውም ትላላችሁ?!

ናይና በምትባል አንዲት ከተማ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስጋችንን ተዋህዶ በሚያስተምርበት ግዜ ከሰራቸው ብዙ የማዳን ተአምራቶች የመግደላዊት ማርያም በእኔ ልብ ውስጥ ትልቁን ስፍራ ይይዝብኛል። "እንዴት?"
እንዴት ማለት ጥሩ እርግጥ ነው በአብ ልጅ ክርስቶስ የማዳን ምስጢር እውሮች አይተዋል፣ አንካሶች ሄደዋል፣ ለምፃሞች ነፅተዋል፣ ደንቆሮዎች ሰምተዋል፣ ድውያኖች ተፈውሰዋል፣ ሙታኖችም ተነስተዋል።

ታዲያ የሀጢያተኝቷ መግደላዊት ማርያም ነፍሳዊ ፈውስ ለምን የበለጠብኝ ይመስላችኋል? መልሱ አጭር እና ግልፅ ነው። እውር ስላልሆንሁ የማየቴ ጉዳይ አያሳስበኝም፣ አንካሳ ስላልሆንኩም የመሄዴ ግዜ አይናፍቀኝም፣ ለምፃም ስላልሆንሁ መንፃቴ አይደገኝም፣ መስማቴም እንዳያስጨንቀኝ ደንቆሮ አይደለሁ፣ ድውይም አይደለሁ ፤ አልሞትሁ። ግን ሀጢያተኛ ነኝና ለመግደላዊት ማርያም የተደረገ ፈውስ እኔንም ይናፍቀኛል። ለመግደላዊት ማርያም የተደረገ ተአምር መዳን ብቻ አልነበረም ለትልቅ ክብር መጨትም(መመረጥም) እንጂ .... ወይ ጉድ ዘመኗን ሙሉ ሰባት አይነት ሀጢያት በመስራት ረክሳ የኖረች ሴት የትንሳኤው አብሳሪ ትሆናለች ብሎ ማን ይገምታል?! ማንም ! "ሰዎች ፈረዱብኝ አንተ ግን አዳንኸኝ" እንዲሉ ......

ዛሬ ዛሬ የሰዎችን ሀጢያት መበርበር እና ለሰዎች ሀጢያተኝነታቸውን ለማሳየት መፍጨርጨር መፅደቂያ መንገድ እስኪመስል ድረስ የአኗኗር ባህላችን ሆኗል። የክርስቶስ ቃልም ተዘንግቷል "የቱ?" ነው ያላችሁት? "እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል።
በወንድምህም ዓይን ያለውን ጉድፍ ስለምን ታያለህ፥ በዓይንህ ግን ያለውን ምሰሶ ስለ ምን አትመለከትም?
ወይም ወንድምህን፦ ከዓይንህ ጉድፍ ላውጣ ፍቀድልኝ እንዴትስ ትለዋለህ? እነሆም፥ በዓይንህ ምሰሶ አለ።
አንተ ግብዝ፥ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ፥ ከዚያም በኋላ ከወንድምህ ዓይን ጉድፉን ታወጣ ዘንድ አጥርተህ ታያለህ።" ማቴዎስ 7፥1-5 የሚለውን ነዋ። እውነት ግን እኛ ፃድቅ ሆነን ነው?! ሌባው፣ ሱሰኛው፣ አመንዝራው ና ግፈኛው ላይ ለመፍረድ አፋችንን አሹለን የተነሳነው?!....

ይገርማችኋል መግደላዊት ማርያም ይህ ቀረሽ የማትባል ልቅም ያለች ቆንጆ ስለነበረች ሰዎች ያደንቋት፤ ወንዶችም ይከተሏት ነበር። እዩልኝ እንግዲህ ከይሲ ዲያቢሎስ የተጠናወታት ለምን እንደሆን... በሰዎች ጦስ... በከንቱ መወድስ.. በአጉል ትዕቢት እንድትሞላ አደረጓት ከዚያ ሰባት አጋንንት ሰፈሩባትና ሰባት አይነት ሀጢያቶችን በመስራት ዘመኗን ፀንታ እንድትኖር ሆነች። ግን ማርያም መግደላዊት ሁልግዜም መዳንን ትሻ ነበር፣ ውስጧ ሁሌም ያለቅስ ነበር፣ በኢየሱስ እግሮች ላይ ያዘነበችው እንባ ዝም ብላ የዛን ቀን ያማጠችው አይደለም፤ በዘመናት የፈውስ ጥማቷ የተጠራቀመ እንጂ።

ስንቶቻችን ነን አውደምህረት ስር እየተወሸቅን ሀጢያታችንን በነጠላችን ልንሸፍን የምንሞክር?
ስንቶቻችንስ እንሆን በተጠና የአኗኗር ስልታችን በሰወች ፊት ፃድቅ ለመሆን "እኔ እኮ እንዲህ ነኝ" በሚል ዲስኩራችን ስንደነቋቆር የምንኖረው?
አይ ሞኝነት ፅድቅ እንደሆን በእግዚአብሔር የምትፈተሽ ረቂቅ ምስጢር ነች እንጂ እኛ በምንፈልመው ፊልም መች ሆነ ብለን ነው
እግዚአብሔር ደሞ ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ ነው።

ስንቶችስ ይሆኑ ለኛ ሀጢያታቸውን ብቻ እያሳዩ ልባቸው የእግዚአብሔር ማዳን በመሻት ታማ በመአልት እና በሌት ምህረትን በመሻት አይናቸው እዥ እስኪያነባ የሚያለቅሱት?!

በዛን ዕለት ኢየሱስ ክርሰቶስ ወደ ፈሪሳዊው ቤት የገባው በፈሪሳዊው ግብዣ ነበር። ያን ፈሪሳዊ ልብ ብላችሁ ካያችሁት እኛል ይመስላል። እሱ የፈለገው ምህረትን አልነበረም፤ ምህረትን መፈለግማ ሀጢያተኛ ነኝ ብሎ ማሰብን ይጠይቃላ። የፈሪሳዊው ፍላጎት ከክርስቶስ እኩል በአንድ ማዕድ መብላት ብቻ ነበር። መግደላዊት ማርያም ግን ክርስቶስ በዛ እንዳለ ባወቀች ግዜ የመዳን ፍላጎቷ ንሮ ወጣ ለጌትነቱ እጅ መንሻ ይሆናት ዘንድ የአልባስጥሮስ ሽቱ አመጣችለት። ክብሩን ለመግለፅም እግሮቹን በእባዋ አርሳ አጥባ በጠጉሯ ጠረገቻቸው፤ የአድነኝ ተማፅኖዋንም ቃል ሳታወጣ እግሮቹን በመሳም አቀረበች። ፈሪሳዊውም ይህን ሲያይ የክርስቶስን የማዳን ሀይል ባላመነ ልቦናው "ይህስ ነቢይ ቢሆን፥ ይህች የምትዳስሰው ሴት ማን እንደ ሆነች እንዴትስ እንደ ነበረች ባወቀ ነበር፥ ኃጢአተኛ ናትና ብሎ አሰበ።”
የልብን የሚያውቅ ኢየሱስም የስምዖንን ሀሳብ ስላወለቀት "እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ኃጢአትዋ ተሰርዮላታል፤ ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል።”
ብሎ በቸርነቱ ከእራስ ጠጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ የሞሉትን ሰባት የአጋንንት ነገድ አስወጣላት።
እንዲህ ነበር ያላት "ሀጢያትሽ ተሰርዮልሻል፤ እምነትሽ አድኖሻልና በሰላም ሂጂ!" ኡህህህ እንዴት የሚያረካ ቃል ነው። አያችሁ ግን ሰው ከግብሩ ይልቅ በእምነቱ ሲድን.....። እኛ ምናምኒት እምነት የሌለንስ ምን ይውጠን ይሆን?! ማመን ያቃተን ግን የዋሃዎች ስላልሆንን እኮ ነው። እምነት ማደሪያዋ የዋህ ልብም አይደል....።

ታዲያ የመግደላዊት ማርያም ታሪክ መች እዚህ አበቃና፤ እንደውም ከዚህ ጀመረ እንጂ። ጌታ ፈውሶ ብቻ አልተዋትም። እንደምን ይተዋት? እምነቷ ፅኑ ነው! ከሀጢያት ሸክሟ ነፃ ካወጣት በኋላ ከ36ቱ ቅዱሳት እንስት አንዷ ትሆን ዘንድ መርጦ ተከታዩ አደረጋት። ማርያም መግደላዊትም ከዚያን ዕለት ጀምሮ ፍፁም ተቀየረች። ጌታን እስከ እለተ ህማሙ ድረስ በሌሊትም በመአልትም በቅንነት አገለገለችው። ጌታችን ስለኛ መከራን በተቀበለባት በዚያች ዕለተ ዐርብም ከጠዋት ጀምራ እስከ ማታ ከጎኑ ነበረች፤ ከግርፋቱ እስከ ስቅላቱ እያለቀሰች ተከትላዋለች። በእግረ መስቀሉ ስር ተደፍተው ሲያለቅሱ ከነበሩ እንስቶችም አንዷ እሷ ነበረች። አቤቱ ምህረትህ የጎበኘውን ምንኛ ባረከው...!

የማርያም መግደላዊት ሐዋርያዊትነት መች በዚህ ያበቃና...... እሁድ ሌሊት ገናም ሳይነጋ መቃብሩን ታይ ዘንድ፤ ሽቱም ልትቀባ ወደ ጎለጎታ ገሰገሰች። ፍፁም የአምላክ ፍቅር በልቧ ሰርጿልና የሌሊቱ ግርማም ሆነ የአይሁድ ጭፍሮች አላስፈሯትም። ጌታችንም ከፍጥረት ወገን የመጀመሪያ ትንሳኤውን ያየች ትሆን ዘንድ አደላት። አቤት መባረክ!
የዛን እለትም በመቃብሩ ራስጌ እና ግርጌ ገብርኤል እና ሚካኤልን ቆመው አየቻቸው፤ ዘወር ስትል ደሞ የክብር ባለቤት የሆነው ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አየችው። አላወቀችውምና በእናቱ ስም "ማርያም" አላት "ረብኒ(መምህር ሆይ)" ብላ ሰገደችለት። ጌታም "ሄደሽ ለደቀመዛሙርቴ ንገሪያቸው" ብሎ የትንሳኤው ሰባኪ አደረጋት። አቤት የፀጋዋ ብዛቱ...... ሰው የተጠየፈውን እግዚአብሔር ምንኛ ወደደው!......

እናንት በሀጢያቴ የምትጠቋቆሙ፣ ገዝፈው በሚታዩአችሁ የእኔ ሀጢያቶች ውስጥ አንሰው የሚታዩአችሁን የራሳችሁን ሀጢያቶች እያተናነሳችሁ የምትኖሩ እናንተ፣ እናንት እግዚአብሔር ቤት መሄዴ የማይዋጥላችሁ አጉል ዶጋ አዋቂ ነን ባዮች፣ የልቤን ሳታውቁ በግብሬ የምትፈርዱብኝ እናንተ ፤ እናንት ሁሌም ከአይኔ ጉድፍ ልታወጡ የምትጥሩ አጥርታችሁ ማየት ያልቻላችሁ በሙሉ..... የማርያም መግደላዊትን ታሪክ የቀየረ ጌታ የሰናፍጭ ታክል እምነት በልቤ ያቆጠቆጠች ቀን የማይምረኝ ነው የሚመስላችሁ?።

በሏ..! ..ታሪክሽን አይቀይረውም ትላላችሁ?!
1.4K viewsDAVE / PAPI, 04:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-15 13:54:47 አስቱካ አስወጣችልኝ

ይህ ማለዳ ፈገግታዬን ነጥቆኛል ቀኑ የእኔ እስካይመስለኝ ድረስ ገና በጠዋቱ ድብርት ተጫጭኖኝ ነበር ስታሽ አርፍጄ ቢሮ የገባሁት፤ እንደገባሁ ዲስክቶፔን አብርቼ ዩቲዩብ ዘንዳ ጎራ አልኩኝ እጄ ኪይቦርዱ ላይ አስቴር አወቀ "ናፍቆት" ብሎ ፃፈ አይምሮዬ እንዳላዘዘው ስለማውቅ ትንሽ ግርምት ብጤ ጫረብኝ ግን ያው መከረኛ ልቤ በል እንዳለው አላጣሁትም።

አስቱካም ያን መረዋ ድምጿን ታንቆረቁረው ገባች.......ግዜው ይርዘም እንጂ
መች እረሳሃለሁ?
በሆነው ባልሆነው
እናፍቅሃለሁ
አሃ..... አልሁ አሁን ቢያንስ ለምን እንደደበረኝ እየገባኝ ነው። በውሃ ቀጠነ፤ አየር ወፈረ የሚናፍቀኝ ያው እሱው ነው፤ ሌላ ማን አለ?
አሱ መሆኑን ሳውቅ ደሞ የእሱን ነገር ማሰቤ አይቀር አይደል፤ የእሱን ነገር በአሰብኩ ቁጥር እንደሆነ ልክ እንደ በውቄ ፈገግታ ነው የሚቀድመኝ። ግን የአሁኑን ፈገግታዬን ድብርቴ ደመናማ ፈገግታ አደረገብኝ። ኤጭ!
"በሰጠሽኝ ፀጋ መጠን የሰራሽኝ ጉድ አያልቅም፤
እኔ ባንቺ ትዝታ እንጂ በተራቢ ቀልድ አልስቅም።"
የሚለውን ስንኝ በውቄ ባይፅፈው ኖሮ እኔ እፅፈው እንደነበር ምንም ጥርጥር የለውም። ከስንኙ በላይ ደሞ ይህች ትህምክቴ ይበልጥ አስፈገገችኝ መሰል

አይ እሱ..... አሁን ምን ልሁን ብሎ ነው የሚናፍቀኝ? ..... ቆይ ለምን አርፎ አይቀመጥም? ለምን አይተወኝም?
አሁን በስጨትጨት ማለትም ጀምሬአለሁ።

አስቴር ይህን የፍቅር ትንታግ ልታቀጣጥለው ታጥቃ የተነሳች ይመስል ቀጥላለች
"በል ይግረምህና
ዛሬም እወድሃለሁ
እንጀቴን አስሬ
ይሄው እኖራለሁ"...
አሁን የምር አናደደችኝ ሆሆ.. ይቺ ሴትዬ ደሞ ልታሳብደኝ ነው እንዴ?! ለምንድነው እሱን የሚገርመው ? እራስሽ ይግረምሽ ዛሬማ አልወደውም እሺ! አልሁ ጮኽ ብዬ ሆሆ... ብቻዬን ማውራት ጀመርሁ።

ቀዝቀዝ ብላ ቀጠለች ደሞ አለሳልሳ ወደ ልቤ ልትሰርግ
"ርቄ ሄጃለሁ ሁሉን ትቼ
ትዝታን በልቤ አስቀርቼ
ምነው የምቀጣ የምቸገር
ከቶ ምን ይሆን ያንተ ፍቅር....
እውነት ነው አልሁ አሁን ደሞ ለራሴ ብቻ በሚሰማ ድምፅ። 'ርቄያለሁ፣ ሁሉን ርግፍ አድርጌ ትቻለሁ፤ በትዝታ ብቻ እንገበገባለሁ። ግን ለምን? ለምን እንደዚህ ልቀጣ? ምን አጠፋሁ? ምን በደልሁ? ......ከነዛ ሁሉ የመለያየት ግዚያቶች በኋላም እንዲህ የሚያደርገኝ ፍቅርህ ምን ቢሆን ነው ይህን ያህል? ....... አሁን ልክ እንደ ሀምሌ ሰማይ አይኔ እንባ ቋጥሯል።

"ተማምነው ተዋደው
አብረው የኖሩት
ሲለዩት ይከብዳል
እንደ'ግር እሳት
እንደ'ግር እሳት"....
አረ ተይ ግን አስቱካ ተይ አታቀጣጥዪኝ ተይ... መከረኛው አይኔ የቋጠረውን እንባ ማዝነብን ያዘው። "አይኔ አበሳ አየ" አለች ያች ሙሾ አውራጅ..... እውነትም እነደ'ግር እሳት አልሁ ሲቃ በተናነቀው ድምፀት......

አስቱ ምን ተዳዋ ሳይወጣልኝ እንደው አትተወኝ....
"በልቤ ወድጄ
በአፌ የሚቀብጥህ
ትቼ የማልተውህ
እኔው ነኝ ወዳጅህ".........
አሁን ዋሸሽ አስቱ ምንም እንኳን እስካሁን በልቤ ብወደውም፤ ትቼዋለሁ! በአፌም ብረግመው ነው እንጂ አላቀብጠውም፤ ችዬ ባልረግመውም ብቻ አላቀብጠውም። በቃ! ደሞ አሁን እኔ ወዳጁ አይደለሁም፤ ወዳጅነት እንዴት ነው እንዴ?!!! እልህ የተቀላቀለበት ልቅሶና ማጉረምረም.....

"አይቻልም እና
ያንድ አንድ ሰው
ናፍቆት
መውደድን በወጉ
ፍቅር ያስማሩት".....
ታሪኬንማ እንደዚህ አትገልብጪው እንጂ?
እሱ እኮ ነው የፍቅር መምህሬ፤ ማለቴ የነበርው..... አሉሁና ስቅስቅ ማለት ጀመርሁ።.......

ታዲያ እሷ ምን ገዷት እኔ ብነፋረቅ ይባስ ብላ ደገመችዋ...
"ርቄ ሄጃለሁ ሁሉን ትቼ
ትዝታን በልቤ አስቀርቼ
ምነው የምቀጣ የምቸገር
ከቶ ምን ይሆን ያንተ ሚስጥር"......
የልቅሶ ሲቃ በተናነቀው ድምፄ አብሬአት ማንጎራጎር ገባሁ። በጉንጮቼ የሚወርደው የእንባ ጎርፍ ፤ ፊቴ ላይ ያሉ አካላቶቼን ይዟቸው እንዳይሄድ ሰጋሁ እና እንባዬን ለመገደብ ሞከርሁ።

"የልቤ ምሰሶ ዘንጉ ተሰበረ
የማይመነጠር ምሽግ የነበረ
ምሽግ የነበረ"......
ልቤ ፍስስ አለብኝ ምሰሶ ተሰብሮም የለ... አሁን ለመንሰቅሰቅ የሚሆን አቅምም ከዳኝ ትክዝ ቅዝዝ ብዬ የእባዬ ቋት ያጠራቀመውን የጨረሰ ይመስል አልፎ አልፎ የምትንጠባጠብ እንባዬን ማበስ ያዝሁ .......

"በፅኑ ትዝታ በራቀው መንገዴ
እስቲ ላሰላስልህ ደሞ እንደልማዴ"......
ልቤ ወዲየው ተነስቶ የኋሊት ጋለበና ወደ አብሮነታችን ግዜ ደረሰ። አሁን ትዝታዬ ፈገግታዬን ሊመልስልኝ ነው .....

"ይኸው ልቤ ጥሎኝ ተነስቶ ሲሄድ
'ባንተ መወስወሱን አድርጎ ልማድ
አድርጎ ልማድ"......
የዘወትር ልማድ አደረገው እንጂ ስል ልቤ ከደረሰበት ትዝታ ፈገግ ሲሰኝ ተሰማኝና ወደ በውቄ ግጥም ተመለስሁ................
"የአሳሳምሽ ለዛ ቀርቶ እንደ እንጎቻ የሚጥመኝ፥
የቧጨርሽኝ የነከሽኝ አገርሽቶ ቁስሉ ሲያመኝ፤
ፈገግታ ነው የሚቀድመኝ።"
ወደ ፈገግታዬ ተመለስሁ፤ ብርሃናማ ፈገግታ ፈግጌ ቀኔን ከዚህ ጀመርሁ።

@wegoch
@wegoch
@mehalu_aynegerm
1.3K viewsDAVE / PAPI, 10:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-14 10:45:45 እንጃ
-----------------------------

ከአመታት በፊት የተለየሁት ባህር ማዶ ይኖር የነበር አንድ ወዳጄ ዘንድሮ አይጠገቡ መንግስት ባደረገለት ጥሪ መሰረት ወደ ሀገር ቤት እንደመጣ ስልኬን አፈላልጎ ደወለልኝ እና ከአመታት በፊት በጀማ ብዙ የሳቅ ድግሶችን ካ'ሳለፍንበት ሰሜን ሆቴል ተቀጣጥረን ተገናኘን።

በጣም ተራርቀን ነበር ምንም አይነት ሶሻል ሚዲያ ላይም አውርተን አናውቅም። ምሳችንን ካዘዝን በኋላ እንዴት ትዝ አልኩህ ግን? ስል ጨዋታ ማስጀመሪያ የሚመስል ጥያቄ ሰነዘርኩ እርሱም ከአፌ ቀበል አድርጎ "አይ ፀጊ አንቺ በቀላሉ የምትረሺ ሰው ነሽ? አልመች ብሎኝ እንጂ ብዙ ግዜ ነው ስልክሽን አፈላልጌ ላገኝሽ እፈልግ የነበረው" አለኝ።

እኔ በቀላሉ የማልረሳው ለምንድነው? ከአይን የራቀ እኮ ከልብ ይርቃል፤ እኔ አሁን በመራራቃችን ምክንያት እረስቼህ ነበር። የግዜ እና የቦታ መራራቅ አይደለም ጓደኝነትን ትዳርን ያረሳሳ የለ አልኩት። ጠፍቶ በመክረሙ ምንም ጥፋተኝነት እንዳይሰማው ለማድረግ በማሰብ። "የአንቺ ግን ሌላው ቢቀር ይሄ ግልፅነትሽ እና ተጫዋችነትሽ የሚረሳ አይደለም።" አለና ደመና ያጠላበት ፈገግታ አስፈገገኝ።

እንዲህ ስንጨዋወት ምሳችን መጣ ባርከን መብላት እንደጀመርን ትክ ብሎ አያየኝ "እኔ የምልሽ ፀጊ ቅዝቅዝ ብለሻል ተጫዋች ነበርሽ እኮ ወይስ የተራራቅን አይነት ስሜት ተሰማሽ?....ነው ወይስ ማደግ ቀልድ እና ሳቅሽን ቀማሽ?...."ሲል ፈገግ ብሎ ጠየቀኝ።
ባክህ እኔ ቀልድ አቁሜአለሁ፤ በዚህ የኑሮ ውድነት ብቀልድስ ማን ይስቅልኛል¿¡ አለኩት የተውኩትን ቀልድ ለማምጣት እየሞከርኩ። ሳቅ ቅርቡ የሆነው ወዳጄም ከትከት ብሎ ከሳቀ በኋላ ኮስተር ለማለት እየሞከረ "የምሬን ነው ፀጊ ምን ሆነሻል?..." አለኝ።

ምን መሰለህ ቀልድ (ቧልት) ከብዙ ሰው ጋር አቀያየመኝ። ቀልድ ለመፍጠር በማደርጋቸው ሙከራዎች ውስጥ ብዙ ቀን እንቅልፍ አልባ ሌሊት አሳለፍኩ፤
ለምን መሰለህ ብዙ ሀበሻ ተጫዋች ሰው ይወዳል ግን ተጫዋች ሰው አያከብርም።
ተጨዋቾች ከሆንክ ስሜት አልባ ያደርግሃል ኩፍስ ለሚለው ወይም ዝም ከሚለው ጓደኛህ ያነሰ ቦታ ይሰጥሃል።
በቤተሰብህ በብሄርህ በገዛ ፊትህ እና በኑሮህ ስታላግጥ አላማህ እሱን ማሳቅ ማጫወት እንደሆነ አይገባውም፤ ይደፍርሃል። በቀልዶችህ መሃል ማስተዋል፣ ማክበር፤ መውደድ የምትቀላቅል አይመስለውም።

በቀልዴ ምክንያት ቁምነገረኛነቴ፣ አንባቢነቴ እና ሰው አክባሪነቴ ሲፌዝበት ያስተዋልኩበት ግዜ ጥቂት የሚባል አይደለም። ማህበረሰባችን ብዙውን ግዜ ከሚጫወት አዋቂ ሰው ይልቅ ዝም ለሚል አላዋቂ ሰው የበለጠ ቦታ ይሰጣል።

ታዲያ ቧልተኝነቴ ካደፋፈረኝ፣ ካስተቸኝ፣ ካስገመገመኝ እና ካስናቀኝ ስራ አይደል አይከፈለኝ ፤ አያሾመኝ ብዬ በሂደት እርግፍ አርጌ ተውኩት! አልኩና የምፀት ሳቄን ፈገግሁ። በትኩረት ሲያዳምጠኝ ቆይቶ እንዲህ አለ "ባለማስተዋላችን ስንት ድምቀቶቻችንን ይሆን ያጣናቸው?!"

ለዚህ ጥያቄው መልሴ እንጃ ብቻ ነው።

እንጃ
#በፀገነት

@wegoch
@wegoch
@mehalu_aynegerm
1.4K viewsDAVE / PAPI, 07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-10 22:46:44 አንድ ወፈፌ ወንደላጤ ጎረቤት አለኝ። ቀን ቀን ፍፁም ሰላማዊ ሰው ነው። አንገቱን ሰብሮ ሰላምታ ሲሰጥ በከንፈሩ አፈር ቅሞ ለመመለስ ትንሽ ነው የሚቀረው :)
እንደውም አከራያችን እትዬ ዘነብ አንዳንዴ "ልጄ ተው እንዲህ አለቅጥ አታጎንብስ ዲስክህ ይንሸራተታል " ይሉታል።
እሱ ፈገግ ብሎ በሀፍረት ያቀረቅራል ። ጭራሽ የሆነ ጊዜ ላይ ቤቱ ቡና አፍልቶ ጠራን !
በጠባብ ክፍሉ ውስጥ እንደ በግ ኮኮር ተራርቀው የሚገኙ የቤት እቃዎቹን እየገረመመን ተሰየምን።
እትዬ ዘነብ ደግሞ እንደ ሀረር ሰው ቀጥታ ነው ንግግራቸው...ያ ሁሉ የግቢው ሰው በተሰበሰበበት
"አንተ ምነው እቃህን በወግ ብትሰድረው?... " አሉት ... ትንሽ ቆየት ብለው ደግሞ...
"እግዚኦ ያ ምንድነው ሀይላንድ ውስጥ ያለው?" ብለው ጮኹ!
ናደው በድንጋጤ "የቱ ?" ብሎ መለሰ። ሀይላንዱን እኮ አፍጦ እያየው ነው !
"ሀይላንድ ላይ ነው እንዴ የምትሸናው?"
ደነገጥን!
እትዬ ደግሞ አንዳንዴ የሆነ ነገር አይተው ላሽ ቢሉ ምናለበት?
" ኸረ ቢራ ነው እትዬ! ኸረ እንደውም ልቅዳሎት " ብሎ ተነሳ...
እትዬ ሀይላንዱን ሰገራ እንደነካው እንጨት ተጠይፈው ...
"አንተ ሂድ ! ምን ያለው ሰላቶ ነው ባካችሁ?
ላስቲኩን እየው እስቲ? ጎዳና ተዳዳሪ መስሏል እኮ! "
እኛ ለሱ ተሸማቀቅን።
ናደው ወሬውን ለማስቀየስ መሰል... ጀበናውን በእጁ እንደያዘ.. ."አህ ...ህ " ብሎ አቃሰተ ።
"ምነው?" አልኩት እሱ በቀደደው አዲስ ወሬ ለማፈትለክ ...
"ብርድ መቶኛል መሰለኝ..አንዳንዴ ትከሻዬን ይወጋኛል "
"በዚህች ስስ አንሶላ ተሸፍነህ እየተኛክ እንኳን ብርድ መጋኛም ስላልመታህ ፈጣሪን አመስግን " ብለው ቀጠሉ እትዬ.. .
"ስማ ምነው እኔ ቧንቧ ቆጠረብኝ አልኩህ እንዴ? ኣንሶላህን ለቅለቅ አድርግ እንጅ!
አሁን ይሄ አንሶላ ነው ወይስ መሀረብ? ኤድያ!
ከዛች ቀን በኃላ ናደው በማለዳ ተነስቶ አዲስ አልጋ ልብስ ገዝቶ መጣ ... ከሾላ ገበያ ገዝቷት የመጣውን አልጋ ልብስ ለግቢው ተከራይ ሁሉ እያዟዟረ አሳየን።
ሽንጉርጉር አንሶላውን ለሞራሉ ስንል አደነቅንለት ...
እኔ በተለይ ከሱሳ ሱስ አስተርፎ ባዘጋጃት ገንዘብ ይሄን በማድረጉ አሳዘነኝ።
ናደው ቀን ቀን ሰላማዊ ይሁን እንጅ ምሽት ላይ ፍፁም ሌላ ሰው ነው ። ጫቱን ቅሞ.. .አረቄውን መጦ.. .ሀሽሹን በልዞ ሲመጣ ያስፈራል።
ቀን ለሰላምታ መሬት ካላስኩኝ የሚለው ልጅ ምሽት ላይ ደረቱን ገልብጦ የሰማይ ከዋክብትን ልግመጥ ይላል ።
ብቻውን እያወራ ይንገዳገዳል.. .ትንሽ ራመድ...ራመድ ይልና የቤቱን ደረጃ በእንፉቅቁ ይወጣል ።
ለዛን ቀንም ... ለገዛት አንሶላ የፍንጥር ራሱን ሊጋብዝ ፀሀይ ከማዘቅዘቋ በፊት ሹልክ ብሎ ወጣ ።
ከሰዓታት በኋላ እንደልማዱ ደረቱን ገልብጦ መጣ...ደረጃውን በዳዴ ወጥቶ የጠባብ ክፍሉን ቁልፍ ከፈተ ።
ከበሩ በስተግራ ያለችውን ማብሪያ ማጥፊያ በመከራ ተጭኖ አንፖሉን ለኮሰ....
ቤቱ በብርሀን ተሞላች ።
በቅፅበት እሪታውን አቀለጠው ....
"ነብር ...ነብር ....ነብር አልጋዬ ላይ ኡ....ኡ....ኡ..... "
የግቢው ተከራይ ንቅል ብሎ ወጣ ። ይሁንና ከእትዬ በስተቀር የሱን ክፍል የተጠጋ ሰው የለም።
ናደው በተዓምር ይሁን በአስማት የግቢውን አጥር ዘሎ ወጣ ...
እኔ ክፍሌ ውስጥ ሆኜ ድምፄን አጠፋሁ ። ድካም ተጫጭኖኝ ስለነበር.. .ግርግሩን እየሰማሁ እንቅልፍ ይዞኝ እብስ አለ ። ማልዶ
"አሁኑኑ ቤቴን ለቀህ ውጣልኝ!" የሚለው የእትዬ ጩኸት እስኪያባንነኝ ድረስ የት እንዳለሁ አላውቅም።
"ሰውኮ ይሳሳታል እትዬ "
የቤቴን መስኮት ከፍቼ የሁለቱን ግብግብ አያለሁ ... እነ አስኩቲ ጥግ ላይ ሆነው አፋቸውን በመዳፋቸው ሸፍነው ይስቃሉ ።
ሰው ሊባረር ሲል እንዴት ደስ ይላቸዋል? የሚል ንዴት ውስጤን እያንገበገበኝ ነበር ።
እነሱም እኮ ተከራይ ናቸው!
ይሄ በእትዬ የተመዘዘ ሰይፍ ነገ እነርሱ ላይ እንደማያርፍ ምን ዋስትና አላቸው? እያልኩ ተብሰከሰኩ.. .
"ስማ ሚኪያስ !" አሉኝ እትዬ ወደ መስኮቴ ተጠግተው.. .
"ሰላም አይደለም እንዴ እትዬ?"
"ምን ሰላም አለ ? ይሄ ቀውስ ማታ የሰራውን አልሰማህም?"
"ኸረ እንደውም! " ... ካድኩኝ...
"ኸረ እንኳን ያልሰማህ። ይሄ ምናምኑን አጭሶ መጣና ቀን የገዛውን አልጋ ልብስ ዘንግቶት ..."
"አልጋ ልብሱን ረስቶ ምን?"
"አልጋ ልብሱ ላይ ያለውን የነብር ምስል አይቶ አልደነበረ መሰለህ?
አልጋዬ ላይ ነብር ብሎ አንባረቀ እኮ!
ደግሞ እንደ ጤነኛ ሰው አንገት ይሰብራል...አንገቱን ነበር መስበር።

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Mikael aschenaki
692 viewsDAVE / PAPI, 19:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ