Get Mystery Box with random crypto!

ወግ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @wegoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.51K
የሰርጥ መግለጫ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @leul_mekonnen1

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 29

2022-01-01 19:24:22 "አንተም ብትሆን ማለት ነው?"
"ዝግጁ ነኝ እያልሽኝ ነው?"
"አምነሽ ካልሰጠሽ ያክምሽ ያቁስልሽ በምን ታውቂያለሽ?" አላልከኝም? በስሱ ፈገግ አለ። ያልቸኮለ ፈገግታ .......
የምላችሁ ........ጨርሰናል።

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
1.1K viewsDAVE / PAPI, 16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-01 19:24:22 "ልጅነቴ፣ እድገቴ፣ ተስፋዬ፣ ፍቅሬ፣ ቤተሰቤ፣ የወደፊት ትዳሬ ብዬ በልቤ የተሸከምኩት እሱን ብቻ ነበር። ማግባቱን የነገረኝ ቀን ሰማይ ምድሩ ዞረብኝ። እሱ ጭራሽ ከዛ በኋላ ለሳምንት አይኔንም ማየት አልፈለገም። የምኖርበት ምክንያትም ተስፋም አልታይሽ አለኝ። የሆነ ቀን ማታ ራሴን ላጠፋ ሞከርኩ። እድለ ቢስ ነኝ አላልኩሽም? ሞት እንኳን እንደደህና ነገር ራሱን አዋደደብኝ! ለመሞት ይታይሽ? ሰው እንዴት ሞት እንኳን አይሳካለትም? ተረፍኩ!! ተደውሎለት መጣ! "
እሷ እየነገረችኝ ቀኑን በእርግጠኝነት አስታወስኩት። ማታ 3 ሰዓት አካባቢ ስልክ ሲደወልለት ደንግጦ ከተቀመጠበት ሲስፈነጠር። "አብሮኝ የሚሰራው ልጅ ራሱን ሊያጠፋ ሞክሮ ሆስፒታል ነው!" ነበር ያለኝ።
የዛን ቀን ባልደረባዬ የስራ እድገት አጊንቶ እራት ተጋብዘን ሄደን "ስራህ ምንድነው?" ብለውት በዛ ሳቢያ ተጨቃጭቀን ነበር። 'ሁልጊዜ ላንቺ ትንሽ እንደሆንኩ ነው የሚሰማኝ .... ሱፍ ለብሰው ለሚውሉ የስራ ባልደረቦችሽ እንጨት ስፈቀፍቅ ነው የምለው ብዬ አንቺን ላሳፍርሽ አልፈልግም!' ብሎኝ ተናድጃለሁ። ሱፍ ለበሰ የስራ ቱታ ለእኔ ለውጥ እንዳልነበረው ያውቅ ነበር። ሱፍ ለባሽ ከሚላቸው ማናቸውም ለደቂቃ ሀሳቤን ሰርቀውት እንደማያውቁ ያውቃል። ብቸኛ ምርጫዬ እንደሆነ ያውቃል። ብቸኛ በፍቅር የማውቀው ወንድ መሆኑንም ያውቃል።
እስከዛ ቀን ድረስ ሙያውን እንደሚወደው ነበር የማውቀው። የራሱን ፈርኒቸር ቤት ሊከፍት የሚያስፈልጉትን ማሽኖችና ጥቃቅን ወጪዎች መዝግበን አስቀምጠናልኮ! ትምህርቱን ቢጨርስ ደስ ይለው እንደነበር የነገረኝ ቀን እኔ አሁን እየሰራሁ አንተ ተማር እና አንተ ስትጨርስ ደግሞ በተራህ ማስተርሴን ታስተምረኛለህ ብዬው ነበር። ምንም መከፋት ባልነበረው ስሜት ነበር የሚፈልገው ፈርኒቸር ቤቱ ላይ መስራት እንደሆነ የነገረኝ። በእንዲህ ጭንቅላቴ በተሰፋበት ሰዓት ነበር ስልኩ የተደወለው። ሆስፒታል ሊያድር እንደሚችልም ሲነግረኝ ምናልባት እሱም እንደእኔ መጨቃጨቃችን ረብሾት ጊዜውን በዛውም ፈልጎት ይሆናል ብዬ ከማሰብ አልዘለልኩም። አብጠርጥሬ የምጠይቅበት ጥርጣሬ አልነበረኝም።
"እርሱ የሌለበት ህይወት መኖር እንደማልፈልግ ስነግረው 'እሷስ?' ነበር ያለኝ አንቺን 'በህይወቴ ማንም ሰው ያልሰጠኝን ክብርና ፍቅር ነው የሰጠችኝ። በምን ጥፋቷ ልቅጣት?' ነበር ያለኝ። የእውነቴን ነበር። እርሱ ከሌለበት የመኖር እንጥፍጣፊ ፍላጎት አልነበረኝም። ለሊቱን ሙሉ ያደረግሽለትን የሆንሽለትን እየነረኝ ነበር ያደረው። በየቀኑ እንደምንገኛኝ ነግሮኝ ድጋሚ ራስ ማጥፋቱን እንዳልሞክረው ቃል አስገብቶኝ ጠዋት ሄደ።
ያኔ ያላስተዋልኳቸውን እና ባስተውላቸውም ከዛን ቀን እራት ጋር እያያዝኩ ምክንያት የሰጠኋቸውን ለውጦቹ ምክንያታቸው ተገጣጠመልኝ። ከዛ ቀን በኋላ ተነጋግረን የተስማማን የመሰለኝን ልጅ የመውለድ ጉዳይ አንስቶ አላስፈላጊ ብስጭት እየተበሳጨ 'እኔ የሚሰማኝ ስሜት አይገባሽም!' ብሎኛል። 'አንቺ በፍፁም አትረጂኝም' የዛን ሰሞን ዜማው ሆኖ ነበር:: በትንሽ በትልቁ ይነጫነጭ የነበረው ጥሎኝ ለመሄድ ምክንያት እንድሰጠው የሚሰማውን ፀፀት ሊቀንስ መሆኑ ሳይገባኝ ልጅ ስላልሰጠሁት ነው ብዬ አምኜ ነበር ለማርገዝ የወሰንኩት።
በአንድ ጊዜ ቅናትም ጥላቻም ቁጣም እልህም ቁጭትም ..... አንድ ላይ የሚሄዱ ስሜቶች መሆናቸውንም እንጃ ብቻ ውስጤን ሞልተው ፊቴ ላይ ሲንቀለቀሉ እሷ እንኳን አይታዋለች። መበለጥ .....መታለል .....መከዳት ....መሸነፍ...
"ውደጂኝ አልልሽም ግን አትጥዪኝ። እኔ ህይወት ራሷ የቀጣችኝ ሰው ነኝ። እኔን ስለመረጠ እንደበለጥኩሽ ታስቢያለሽ? ያውም እኔ ከምሞትበትና አንቺ ከምታዝኚበት ምርጫ ሰጥቼው? በጥሩነትሽ በልጠሽኛል። ጊዜ አምጥቶ ከነልጄ እጅሽ ላይ ጣለኝ አይደል? ይበልጥ ቅጣቱ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ? አሁንም ማን እንደሆንኩ እያወቅሽ ደግ መሆንሽ? እሱ ይበልጥ ያማል።" ብላኝ ዝም አለች::
"አንዳንዴ የክፋቴ ውጤት ነው ብዬ አስቤ አውቃለሁ:: በመጨረሻ ተደላድዬ እግዜር ታርቆኛል ብዬ መኖር ስጀምር ያ ከይሲ መጣ!! የእግዚአብሄር ቁጣ ካልሆነ በከተማው ከሞላው ሱቅ እኔ ሱቅ ምን ያደርጋል? እድሌ ሲከፋ እንጂ ካልጠፋ ሰዓት አሹ ሊወስደኝ እዛው በቆመበት? .... በአንድ ቦክስ ከግድግዳ ጠርዝ ተጋጭቶ ሰው ሞቶ ያውቃል?? ለኔ ሲሆን የማይገጣጠም ነገር የለም!....... ከዛሬ በኋላ አይኔን ማየት ካልፈለግሽ ከነልጄ ከህይወትሽ እወጣለሁ እመኚኝ አደርገዋለሁ። " ብላኝ እንባዋን እንዳላይባት ዞረች::
"በልብሽ ትንሽዬ ርህራሄ ከተረፈሽ ግን እባክሽ ባባ ከእህቱ ጋር ይጠያየቅ። ለእኔ ብለሽ አልልሽም ለባባ እንዴት እንደምትሳሱለት አይቻለሁ። ይሄን ተስፋውን ይሄን ፍቅር አታሳጪው" ብላኝ መልሴን ሳትጠብቅ ወደውስጥ ገባች።

ከዛ ሁሉ እንደእሳት ከሚንቀለቀል ስሜትጋር ሀዘኔታስ ሲደባለቅ የጤነኛ ሰው ስሜት ነው? ባባ ትምህርቱ እንዳይስተጓጎል በሚል ለትምህርት ቤቱ የሚቀርብ ቦታ ቤት ተፈልጎ እቃዎቿ ተጭነዋል። ሲመሽ ተሰናብታን እና አመስግናን ልትሄድ ስትነሳ ባባ ሁላችንንም ለጤንነት ያልቀረበ ስሜት ውስጥ ከተተን። አንዴ የእህቱን እጅ ይዞ አብራው እንድትሄድ ያለቅሳል። ደግሞ መለስ ብሎ የእናቱን እጅ ይይዝና እንድትቀር ይወተውታል። እላዬ ላይ ተንጠልጥሎ 'መላ በዪኝ!' አይነት ተቁለጨለጨ። እናቱንም እኔንም እህቱንም ማንንም መምረጥ ቸገረው። አባዬ ላለማየት ሳሎኑን ለቆ ወጣ። የነበረኝ ቅጥ አንባሩ የጠፋ ስሜት ላይ ባባ ሊሄድብኝ መሆኑ አተረማመሰኝ:: ማት ሁሉንም ተቆጥቶ
"ምንድነው የማንገናኝ ነገር አደረጋችሁት። የአንድ ታክሲ ርቀት ላይ ናቸውኮ!" ብሎ ሁሉንም አረጋጋ። ለባባ 'ነገ እንገናኛለን! ብለን አባብለነው ሄዱ።
"እውነትሽን ነው? ነገ እንገናኛለን ያልሽው?" አለችኝ ልጄ
"ወንድምሽ አይደል? ልታገኚው በፈለግሽ ሰዓት መሄድ ትችያለሽ! እሱም መምጣት ይችላል።" ስላት ራሴን ሰማሁት። መጥታ አቀፈችኝ። የሚሰማኝን ስሜት ለይቼ እንኳን ሳልረግብ
"አባቴጋ መሄድ እፈልጋለሁ" ብላ ድንጋጤ አከለችልኝ። ድጋሚ አሸናፊን ላየው መዘጋጀቴን እርግጠኛ አልነበርኩም!! የዛን ቀን የማስበው ምን እንደሆነ እንኳን አላውቅም አንዱን ሀሳብ ሳነሳ ሌላውን ስጥል ነጋ! ከቀናት በኋላ ግሩምጋ ደውዬ ሸዋ ሮቢት ሊያደርሰኝ ይችል እንደሆነ ስጠይቀው
"ድሮም ከአማትሽ ጋር ንትርክ ስትጀምሪ ልትጀነጅኚኝ እንዳሰብሽ ገብቶኛል" ብሎ ቀለደብኝ። ከእናቱ ጋር በገንዘቡ ዙሪያ መነጋገራችንን ነግረውታል ማለት ነው።
ሳየው የምናደድ ፣ የምተክን ፣ እንባ የሚያንቀኝ፣ ብዙ ነገር የምለው ነበር የመሰለኝ። እንደዛ አይደለም የተሰማኝ። ዝም ያለ ስሜት! ምንም!ከልጁ ጋር ብቻውን እንዲሆን ትቼው ከግሩም ጋር ርቀን ቆምን።
"አንቺን እስካገኘሁበት ቀን ድረስ እንዳንቺ አይነት ቅን ሰዎች እንደዳይኖሰር ከምድር የጠፉ ነበር የሚመስለኝ። ክፋት፣ ፉክክር፣ ጥሎ ማለፍ ዓለምን በዝቶ እንደልክ ተቆጥሯል። መልካምነት ፣ ለሌላው ቅድሚያ መስጠት፣ መከባበር .....ቂልነት እየመሰለ መጥቷል። ፌቨን የምሬን ነው አንቺ እጅግ መልካምና ቅን ሰው ነሽ። በዚህ ደስ ልትሰኚ ይገባል። ግን ሰውን ከምትወጂው ከፍ አድርገሽ ራስሽን ውደጂ፣ ሌላውን ከምታከብሪው ከፍ አድርገሽ ራስሽን አክብሪው፣ ያኔ አልፎ ሂያጅ የሚሰብረው ልብ አይኖርሽም!" አለኝ ዓይኖቹ ርቀው እነአሸናፊን እያዩ
1.1K viewsDAVE / PAPI, 16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-01 19:24:22 አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #10

(የመጨረሻው ክፍል)

«ጥፋቱ የልጄ አይደለም። እራሷ ተንቀልቅላ ነው የገባችበት። ያን ሁሉ ብር መክፈላችን ልክ አይደለም! በዛ ላይ የዚህን ሁሉ ጊዜ የህክምና ወጪ ሸፍነናል።” ብለው የግሩም እናት ሀገር ይያዝልኝ ብለው ነበር መንቃቷን የሰሙ ጊዜ። ብዙ ጊዜ ነገር “ሁሉ ለበጎ ነው” የሚለው ቃል ያናድደኛል። የምወደው ሰው ሞቶ ወይ ታሞ ወይ የምሰራው ስራ ተበላሽቶብኝ ለበጎነቱ አይታየኝም። በእንዲህ ያለ ጊዜ ግን በጣም ፈገግ ብዬ ነገር "ሁሉ ለበጎ ነው!" እላለሁ።
ዶክተሩ 'ከዚህ በኋላ የመንቃት እድሏ ጠባብ ነው!' ያለን ጊዜ ነበር የሽምግልናውን ሂደት ያከናወነው። በሰዓቱ የሄለንን በህይወት ያለመኖር ታሳቢ አድርገን ባባ ትምህርቱን እስኪጨርስ ያለውን ወጪ ተምነው.... እናቱን ስለነጠቁት ካሳ እንዲሆን ተብሎ 500 ሺህ ብር ካሳ ስንጠይቅ የሄለን ያለመትረፍ አስደንግጧቸው ስለነበር በተለይ የግሩም እናት ሁለቴን አላሰቡትም ነበር። አባትየው የዛኔም 'ኡኡኡ ' ብለው ነበር። እቤት ሄደው ተማክረው (ቀልቤ እንደነገረኝ የግሩም ተፅዕኖ አለበት።) ብሩን ሊከፍሉ ተስማሙ። በባባ ስም በተከፈተ አካውንት ገንዘቡ በገባ በሳምንቱ ሄለን ስትነቃ ነው እንደአዲስ እሪሪሪሪ የሚሉት። እፊታቸው ፈገግታዬ ሲያመልጠኝ
"ሳቅሽ? ቱ! እንተያያለን! ገንዘቤን ትመልሷታላችሁ!" ብለው ተቀነጣጠሱ። ትልቅ ሰው ናቸውና መባለግ አልፈለግኩም ነበር ግን አበሳጩኝ። መጥተው 'ልጄ ከሚታሰር ቅበሪኝ!' ብለው እግሬ ላይ የወደቁ ሴትዮ የጭንቅ ቀናቸው ሲያልፍ ገንዘቤን ይላሉ?
"አስገድደን አላስፈረምኖትምኮ ፈቅደውና ጊዜ ወስደው አስበው የወሰኑት ውሳኔ ነው። በሽማግሌ በምስክር ፊት ተስማምቻለሁ ብለው ያደረጉት ነው። አይ ካሉ ይክሰሱኝ!" አልኳቸው ትቻቸው እየሄድኩ።
"ፀሎቴን ሰምቶኛላ! እግዚአብሔር ፀሎቴን ሰምቶኛላ? ጥሎ አልጣለኝም!" ነበር ያለችው ሄለን ከእንባ ጋር የምትይዘው አጥታ እየተቅበጠበጠች ምን ያህል ገንዘብ እንደተካሰች ስነግራት።
ከሆስፒታል የወጣች ቀን ቅዳሜ ቀጥታ እነእማዬጋ ነበር የመጣችው። ምሳ ተዘጋጅቶ። አባዬና እማዬ 'ጥሩ ሃሳብ አይደለም!' ብለው ነበር። እቤት ከገባችም በኋላ አሁንም አሁንም የእኔን ስሜት ይፈትሻሉ። ሄለን የሆነ ቀን ሆስፒታል ልጠይቃት ባባን ይዤ በሄድኩበት ባባ ስለእህቱ እየደጋገመ ሲያወራ ልጄ እንደሆነች እና የባባ እህት እንደሆነች ከነገርኳት በኋላ ብዙም አላወራችም። እነአባዬ ጥሩ ሀሳብ አይደለም ያሉት የገባኝ የልጄን ሁኔታ ሳይ ነው። ቃል አውጥታ ምንም ባትናገርም። ነገረ ስራዋ ሄለንን እንዳልወደደቻት ያስታውቅባታል። እንድትነነግረኝ ብወተውታትም 'ምንም' ከማለት ውጪ አትመልስም። ምናልባት አባቴን የወሰደችብኝ ሴት ናት ብላ ፣አሁን ደግሞ ተላምዳው ቀኗን በፍካት የሞላላትን ሁሌ እንዲኖራት ትመኘው የነበረውን ወንድሟን ልትወስድባት መሆኑ፣ ልታስበው ትችላለች ብዬ የማስበውን አስባለሁ።
"መጀመሪያ ላይ ማግባቱን አላውቅም ነበር።" አለችኝ ሄለን የምሳው ግርግር አልቆ እኔና እሷ በረንዳ ላይ ቁጭ ብለን ልጆቹ ጊቢ ውስጥ ሲተረማመሱ እያየን።
"አረብ ሀገር ከሄድኩ በኋላ በህይወት ለመኖር ፣ ለመስራት የምጓጓ የነበረው ተመልሼ መጥቼ ከእርሱ ጋር ለመሆን ነበር። ሌላ ምንም የምጓጓለት ነገር አልነበረኝም። ሰርቼ ብር አጠራቅሜ ከእርሱ ጋር ህይወት መጀመርን ሳስብ ነበር ማታ ተኝቼ ጠዋት ለመንቃት የምጓጓው። ህይወቱ የተበለሻሸው ለእኔ ብሎ ነው። ለእኔ ብሎ ባይሆን ይሄኔ የት በደረሰ። ታውቂያለሽ ሁሌም እድለ ቢስ ነበርኩ! ሁሌም መኖር ጀመርኩ ስል የሚገድለኝ አጋጣሚ ይፈጠራል። ታመምኩ። ህመሜ ምን እንደሆነ ሳይታወቅ ያጠራቀምኩትን ገንዘብ በህክምና ጨርሼ። ከነህመሜ ተጠርዤ ወደሃገሬ ስመለስ በመከራ ነበር አስፈልጌ ያገኘሁት።" ብላኝ ዝም አለች።
ጊዜውን አስታውሰዋለሁ። በህይወቱ ውስጥ አንድ የፍቅር ታሪክ ብቻ ያለው ሰው እንዴት የዚያን ታሪኩን ገፅ እያንዳንዱን ቀኑን ሊረሳ ይችላል? ተጋብተን በሰባተኛ ወራችን አካባቢ ነው።
ከስራ ስመጣ የእንጨት ብናኝ የለበሰውን የስራ ልብሱን ሳያወልቅ ሳሎን መመገቢያ ጠረጴዛው ጋር የእናቱን ሞት የተረዳ መስሎ ቅስስ ብሎ ተቀምጦ ነበር። ሁኔታው አስደንግጦኝ ኮቴን አውልቄ እየወረወርኩ
"ምን ሆነሃል? ምን ተፈጠረ? ንገረኝ ምን ሆነሃል?" እያልኩ ስወተውተው ቆይቼ
"ሄለን ብዬ የነገርኩሽን ልጅ ታስታውሻታለሽ? ማሳደጊያ ..... " ብሎ ሳይጨርስ አስታወስኳት።
ስለማሳደጊያው ሲያወራ ፊቱ በፈገግታ የሚፈካው ስለእሷ እና ስለእማሆይ ሲያወራ ብቻ ነበር። ያለችበትን ለማወቅ ፈልጎ ሊያገኛት ያልሞከረው ሙከራ አልነበረም። ከአረብ ሀገር መጣሁ ያለች ሴት ባገኘ ቁጥር እንደቂል ያውቋት እንደሆነ ይጠይቅ እንደነበር አስታውሳለሁ። በኋላ ላይ ተስፋ ቆርጦ ፍለጋውን ተወው። 'የሆነ ነገር ሆና ቢሆንስ?' ብሎኝ ያውቃል። እሷ ላይ በሆነው ነገር ሁሌ ራሱን ይወቅስ ነበር። 'ልጠብቃት ቃል ገብቼላት ነበር። ብቸኛ ቤተሰቤ እሷ ነበረች። እኔ በህይወት እያለሁ ማንም እንደማይጎዳት ቃል ገብቼላት ነበር። የማንም ባለጌ ሲደፍራት እንኳን ልጠብቃት አይዞሽ ብዬ ላባብላት እንኳን አጠገቧ አልነበርኩም' ነው ያለኝ ታሪኩን የነገረኝ ጊዜ
"ታማ ከአረብ ሀገር ተመልሳለች። ሆስፒታል ናት!" አለኝ።
"በእማዬ ሞት! ደህና ናት? ማለቴ ምንድነው ህመሟ? ትድናለቻ?" አልኩት አተካከዙ መጥፎ ሁኔታ ውስጥ እንደሆነች ለመገመት አይከብድም ነበር።
"አትድንም! ህክምናው ያለው አንድ የግል ሆስፒታል ነው። እሱም በትንሹ 430 ሺህ ብር ያስከፍላል። ድጋሚ ስትሞት ዝም ብዬ ላያት ነው።" ብሎ ሲሆን አይቼ እንደማላውቀው ደም ስሩ ተገታትሮ ነፍሱ ጣር ላይ ያለች ሰው መሰለ።
"መላ እንፈልጋለን! ከቢሮም ቢሆን እበደራለሁ! ወይም ከአባዬ እበደራለሁ! የሆነ መላ አይጠፋም! ብቻ ትዳን እንጂ የሆነ ነገር አይጠፋም!" ብዬ አባበልኩት። አባቴን ዋሸሁት! ቤት ልንገዛ ብር አንሶን ነው ብዬ አባቴን ዋሸሁት። እማዬን የምታልመው እስራኤል ሊወስዳት ብሎ ለዓመታት ያጠረቃመውን ገንዘብ አንስቶ ሰጠኝ። ብሩን ሰጥቼው ሳውዝ አፍሪካ ለስድስት ሳምንት ስልጠና በቢሮ ተልኬ ሄድኩ። ደስተኛ ነበር። 'የእህቴን ህይወት ነው መልሰሽ የሰጠሽኝ' ነበር ያለኝ። ከስልጠና ስመለስ ህክምናዋን ጨርሳ ወደቤት መግባቷን ሲነግረኝ ልጠይቃት በተደጋጋሚ እቅድ አውጥቼ አውቅ ነበር። አሁን ሳስበው ምናልባት እንዳገኛት እሱ ስላልፈለገ ይሆናል ብቻ ተሳክቶልኝ አያውቅም ነበር።
"ብሩን ከየት አምጥቶ እንዳሳከመኝ ያወቅኩት ቆይቶ ነው። እኔጋ ያለው ስሜት እሱጋም ያለ ይመስለኝ ነበር። ተሽሎኝ ከሀኪም ቤት የወጣሁ ጊዜ ለእኔና ለእሱ ብዬ ብር አጠራቅሜ እንደነበር ስነግረው ከታናሽ እህትነት ውጪ እንደሌላ እንደምንም እንደማያየኝ ነገረኝ። ማግባቱንና የታከምኩበትን ብር አንቺ እንደሰጠሽው ነገረኝ። አላመንኩትም ነበር። ምንም ስሜት ባይኖረው ማግባቱን ለቀናት አይደብቀኝም ነበር ብዬ አሰብኩ።" ብላ ስሜቴን ለማጣራት በሚመስል አየት አድርጋኝ ቀጠለች::
"....ወደላይ ወደታች ብታዪ ወደግራም ወደቀኝም ብትዞሪ አይንሽን የምታሳርፊበት አንድ ነገር ብቻ ኖሮሽ ያውቃል? ሊያውቅ አይችልም!" አለችኝ ዙሪያ ገባችንን እየቃኘች። ማት ባባን እና የሱን ልጆች ጨምሮ ሳሩ ላይ እየተንከባለለ እያጫወታቸው ፣ የማት ሚስት የእማዬን ፀጉር እያበጠረችላት፣ እቤት ውስጥ አባዬና የኔ ልጅ በሆነ ነገር እየተከራከሩ ድምፃቸው ይሰማል። ቀጠለችና
1.0K viewsDAVE / PAPI, 16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-31 11:59:41 ደጋግመን በጣም ብዙ ጊዜ ተያይተናል።
'የሆነ ቦታ የማውቅህ መሠለኝ ፡ መልክህ አዲስ አይደለም' ብዬ ራሴው ወሬ ጀመርኩኝ።
ሙሉ መልኩን ሳላይ ፡ ማስክ አድርጓል ኮ
ይጠብቅ የነበረው አጋጣሚ ይመስል ፡
"አይገርምም? እኔም እያልኩኝ ነበር በውስጤ ፡ የት ነው የማውቃት? እያልኩ" አለኝ።
እዚህ አከባቢ ነህ?
አይ ፡ አይደለሁም።
እሺ እዚህ አከባቢ ነሽ? ምናልባት መንገድ ላይ ተያይተን ከሆነ?
ኧረ አይደለሁም።
(መንገድ ላይስ ብንተያይ አሁን ማን ይሙት እንዲህ አስታውሰው ያስታውሰኝ ይመስል ?
አልኩኝ በሆዴ።)
እዚህ ሀገር ነበርክ?
ኧረ በጭራሽ።
እዚህ ሀገር ሄደሽ ታውቂያለሽ?
አላውቅም ኧረ።
እዚህ አከባቢ ይሆን የማውቅሽ?
ወደዛም ሄጄ አላውቅም።
ok ፡ እከሌ የሚባል ወንድም አለህ?
ወንድም የለኝም ፡ እም ፡ ለቤተሰቤ ከሦስት ሴቶች በኋላ የተገኘሁ ብቸኛ ወንድ ልጅ ነኝ።
ምናልባት የሆነች የማውቃት እከሌ የምትባል ልጅ አለች፡ እሷን መስለሽኝ ይሆን ?
እኔ እንጃ ፡ እንደዛ የምትባል ሴት በእርግጥ አላውቅም። ምናልባት መልኬን እሷን መስሎህ
ይሆን?።
እንደዚህ የሚባል መስሪያቤት ትመጣ ነበር? ምናልባት እዛ ብዙ ሰው ስለሚመጣ እዛ
አይቼህ ከሆነ።
ኧረ እኔ የተሰማራሁት በዚህ ስራ መስክ ነው፡ ወደዛ አከባቢ መጥቼ እንኳን አላውቅም።
.
.
.
.
በመሀል ሰው መጣ እና ፡ እሱም ወደ ውጭ ወጣ ፡ ጥያቄዎቻችንን በእንጥልጥል ተውነው
፡ ምናምን።
ከነበርኩበት ለመሄድ ተነስቼ ወጣሁ ። ከርቀት ለየሁት ፡ የጊቢው በር አከባቢ ከሰዎች ጋር
ቆሞ ሲያወራ ተመለከትኩት። እሱም አይቶኝ እንደነበር የገባኝ፡ አይኖቻችን ሲገጣጠሙ
ፈገግ ብሎ ሲመለከተኝ ማስተዋሌ ነው። እያወራሁ የነበረውን ስልክ ዘግቼ ወደሱ አመራሁ
"ልትሄጂ ነው እንዴ?" ሲለኝ አዎን ፡ግን ነገ እመለሳለሁ አልኩት። ወደእኔ ቀረብ ብሎ
እንደሚተዋወቅ ሰው እቅፍ አድርጎኝ ፡ እከሌ እባላለሁ ሲለኝ ስሜን ብቻ ነግሬው ነገ
እመለሳለሁ ብዬው ተለየሁት። ትንሽ ተደነባብሬ ፣ ተንተባትቤ ስሜንም በአግባቡ
አልነገርኩትም መሠለኝ።
ቆይ ነገ ታምሜ ባልሄድስ?
እሱ አሞት ነገ ባይመጣስ?
ድንገተኛ ለቅሶ ያጋጥመው ይሆን?
በተለየ ነገር መንገድ ይዘጋ እና መምጣት አይችል ይሆን?
የምሄድበት ምክንያት ሌሊቱን አልቆ ብቀርስ?
ምናምን ምናምን እያልኩ ሀሳብ ገብቶኝ አደርኩኝ።
ሰው እንዴት ስልክ አይለዋወጥም? መች ነው ፋራ የሆንኩት?

መልካም ቀን ቤተሰብ

@wegoch
@wegoch
@paappii

#ጠርሲደ ከበደ
1.4K viewsDAVE / PAPI, 08:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-30 15:58:23 ከተቀመጥኩበት ሳልነሳ ማት እና ግሩምጋ ደወልኩ።
"እግዚአብሄር ይመስገን!" ካለኝ በኋላ ወዲያው "መጣሁ!" አለኝ ማት ሳልነግረው ይገባው የለ? ግሩም ፈነጠዘ። ሆስፒታል ስደርስ ነቅታ ሰውነቷ ላይ ተሰካክተው የነበሩት ማሽኖች ተቀንሰው ቅልል ብሏታል።

"ልጄስ?" ነው ያለችኝ ገና ስታየኝ መልኬን ታውቀዋለች ማለት ነው? ወይስ ገምታ ነው ብዬ እያሰብኩ

"ትምህርት ቤት ነው!" አልኳት ባባ ትምህርት ከጀመረ ሁለት ሳምንቱ ነበር። ዶክተሩ 'ከዚህ በኃላ ልትነቃ የምትችልበት እድል እየጠበበ ነው።'ያለኝ ጊዜ ነው ትምህርት ቤት ግማሽ ሴሚስተር ላይ ያስመዘገብኩት። ዝም አለች። ከዛ ደጋግሜ "እንዴት ነሽ አሁን?" የምላት እኔ ሆንኩ። ማት እና ግሩም ሲገቡ ማናቸው በሚል ስታያቸው ማንነታቸውን ነገርኳት።

"ቤተክርስቲያን እየሄድኩ ነበር።" አለች ለግሩም በሚመስል አነጋገር።

"ይቅርታ በፍፁም አላየሁሽም ነበር!" አላት ቀጥሎ ከአፏ የሚወጣውን ለመስማት መጓጓቱ እያስታወቀበት።

"ከእጄ ላይ ሳንቲም ወድቆ እሱን ላነሳ ነበር!የመኪና መንገዱ መሃል መድረሴንም አላስተዋልኩትም ነበር።" አለች አሁንም ግሩምን እያየች .......ያቺ ያነሳኋት የአንድ ብር ሳንቲም ትዝ አለችኝ የዛን ቀን የቦርሳዬ ትንሽዬ ኪስ ውስጥ እንደከተትኩት ነው።

"የምሰራበት የነበረበት ሱቅ ባለቤት ስራ ልቀይር ነው ብሎ ሱቁን ዘግቶት ነበር። ስራ እየፈለግኩ እጄ ላይ የቀረው አንድ ብር ብቻ ነበር።" እንደነገሩ ቀለል አድርጋ እያወራችው ግን የሚጋባ መከፋት ነበረው ድምፅዋ

"በአንድ ብር ምን አደርግበታለሁ? ልጆች ሆነን ማሳደጊያ እማሆይ ወይኗ የምንላቸው እናት ነበሩ መፅሃፍ ቅዱስ የሚያነቡልን ስለአንዲት ሴት ያነበቡልንን ሁሌ የማስታውሰው ነበር:: በሀገሩ የሚበላ ጠፍቶ ድርቅ በነበረበት ዘመን የቀራትን ትንሽዬ ዱቄት በውሃ ለውሳ ጋግራ ለነብዩ ስላበላች ሴት ..... ቃል በቃል አላስታውሰውም!ያላትን ለእግዚአብሔር አገልጋይ ሰጥታ እጇን አጣጥፋ ሞቷን ስለጠበቀች ሴት ........ ያለሽን የመጨረሻ እንጥፍጣፊ አልሰሰትሽምና ብሎ አምላክ ስለባረካት ሴት ....." ብላ ዝም አለች። የሁላችንንም ፊት ተራ በተራ ካየች በኃላ

"አላዋቂ ናት ብላችሁ ታስቡ ይሆናል። የማደርገውን ሳጣ ያስታወስኩት ይሄን ታሪክ ነበር። በዛ ለሊት ተነስቼ ቤተክርስቲያን የምሄደው ያቺን የቀረችኝን አንድ ብር ለቤተክርስቲያን ሰጥቼ ልጄንም እኔንም እንደፈለግክ አድርገን ልለው ነበር። ከዛ ውጪ ምን ማድረግ እንደነበረብኝ አላውቅም ነበር። የማውቀው፣ ቸገረኝ የምለው ዘመድም ጓደኛም የለኝም ነበር።" ብላ አሁንም ዝም አለች። ማንም ምንም ለማለት አቅሙም ቃሉም አልነበረውም። ጉንጭሽ ላይ ካልተደፋሁ ብሎ መጣሁ መጣሁ የሚል እንባዬን መታገል ጀመርኩ። "አይዞሽ፣ እኔን!" ልላት እፈልጋለሁኮ ግን ቃል ከአፌ ከመውጣቱ በፊት እንባዬ እንደሚቀድም ስለገባኝ የባሰ ሆድ ላስብሳት አልፈለግኩም። ከሆነ ደቂቃ በኋላ

"አይዞሽ! ከአሁን በኋላ ቤተሰብ አለሽ! " አላት ማት እሷ ወደ እኔ አየች። ያን እንዳረጋግጥላት ይሁን አልገባኝም። የምለው ግራ ገባኝ እና እጇን ያዝኳት

"ከፈለግሽ ባባን በኋላ ከትምህርት ቤት ሲወጣ ላመጣው እችላለሁ!" ስላት ሳግ እያነቃት

"እሺ!" አለችኝ። ባባን እንደምትወስድብኝ ሳስብ የሆነ አንጀት የሚቆርጥ ህመም አለው ግን የመተው ዓይነት ህመም አይደለም...... ይከፋኛል ብዬ ያሰብኩትን ያህል አይደለም:: ልክ የሆነ ስሜት ሳይሆነው ልክ የሆነ ነገር ....... የሆነ በህመም ውስጥ ፈውስ ያለበት ነገር......

ይቀጥላል.......

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
1.1K viewsDAVE / PAPI, 12:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-30 15:58:23 አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #9

“በቅርብ ጊዜ …. ማለቴ አናቴ በነጭ ፀጉር ከመከደኑ በፊት ዝግጁ የምትሆኚ ይመስልሻል?”አለኝ ግሩም ፈገግ እያለ።

ማት እንዳለኝ ራሴው ነኝ የደወልኩለት። አዋቂዎች ያደርጉታል እንደተባልኩት የእራቱን ሀሳብ ተቀብያለሁ አልኩት። ስለብዙ ነገሮች ስናወራ ቆይተን።

"ግሩም አሁን ባለሁበት ሁኔታ ካንተጋ ለመሆን ዝግጁ አይደለሁም!" ብዬው ነው

"አናቴ በነጭ ፀጉር ከመከደኑ በፊት ዝግጁ የምትሆኚ ይመስልሻል?" የሚለኝ

"እንደማየው ከሆነ ካሁኑ ነጭ ፀጉር ጀምሮሃል! ሙሉ አናትህን እስኪከድነው ያለው ጊዜ ዝግጁ ለመሆን ያንሰኛል!" አልኩት እሱ በጀመረው ጨዋታ

"የእውነት ዝግጁ ስላልሆንሽ ነው ወይስ እንደአንዳንድ ሴቶች ደጅ በማስጠናት ምን ያህል ርቀት እንደምሄድ ልትፈትኚኝ ነው?"

"አይ እኔስ የእውነቴን ነው። ግን እንዳልካቸው ሴቶች ቢሆንስ?" አልኩት

"አታስዋሺኝ እኔ ትዕግስቱ የለኝም። ቀጥተኛ ሰው ነኝ! የተሰማኝን ፊትለፊት እናገራለሁ። ይሄ የልጅ አባሮሽ ጨዋታ እድሜዬም ባህሪዬም ነው ብዬ አላስብም። ለአባባል ነው እንጂ ጠብቀኝም ብትዪኝ ፀጉሬ ነጭ እስኪሆን አልጠብቅሽም አልዋሽሽም!" አለኝ እየሳቀ

"ሀቀኝነትህ ደስ ይላል"

"እኔ ስለሆንኩ ነው ወይስ ባጠቃላይ ማንንም ቢሆን ለመቀበል ዝግጁ አይደለሽም?"

"ለማንም ቢሆን ዝግጁ አይደለሁም! አንተ መሆንህ ደግሞ ይባስ ፈታኝ ይሆንብኛል።"

ለማውራት የሚከብድ ሰው ስላልሆነ ወይም ምክንያቴን ማወቅ ይገባዋል ብዬ እኔእንጃ ጥቃቅን ነገሮች ሲቀሩ ብዙውን ነገር ስለአሸናፊ አወራሁት። በዝምታ ሲሰማኝ ከቆየ በኋላ

"የሆነ ሰው በጥይት ተመቶ ቢቆስል ቁስሉ እያንገበገበው መጀመሪያ የሚያደርገው ሀኪምጋ መሄድ አይደል? ቁስሌ ሲነካ ስለሚያመኝ ብሎ የሚደማ ቁስሉን አቅፎ እቤቱ አይቀመጥም! ሀኪሙ ቀዶም ይስፋው፣ ምንም ያድርገው ግን አምኖ ቁስሉን ይሰጠዋል። ያኔ የሚፈጀውን ጊዜ ፈጅቶ ቁስሉን ያድንለታል። ያው ጠባሳው ሙሉ ለሙሉ ባይጠፋም!" አለ ትከሻውን እየሰበቀ።

"አይገናኝም! ሀኪሙ እንደሚያድነው ቀድሞ ነገር ያውቃል። ከርሱ ቁስል ሌላ ብዙ ቁስሎች እንዳዳነ ስለሚያውቅ ነው አምኖ የሚሰጠው!" አልኩት

"ያን ለማወቅ የሀኪሙን ፋይል ያገላብጣል? ያለፈ ታሪኩን ያጠናል? በፍፁም! የለበሰውን ነጭ ጋውንና ማዕረጉን አይቶ ያምነዋል። ምናልባት ሀኪሙምኮ የሆነ ቀን ተሳስቶ በሙያው ህይወት የሚቀጥፍ ስህተት ሰርቶ ያውቅ ይሆናል።"

"እና ሀኪሙን ነኝ እያልከኝ ነው?"

"አቁሳይ እንዳለ ሁላ ሀኪምም አለ እያልኩሽ ነው!"

ኑሮዬ ያለፉትን 15 ዓመታት (ከሆስፒታል ስልክ እስከተደወለልኝ ቀን ድረስ) ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ ምን እንደሚመስል የማውቀው ፣ የታቀደ ቀን ያለኝ ፣ ተመሳሳይ እና በአብዛኛው ተደጋጋሚ ነበር።

ያልተለመደ፣ አዲስ፣ አድቬንቸር ያለበት ቀን አልወድም። አልሞክርም። አዲስ ነገር ስለምጠላ አይደለም። የምሞክረው አዲስ ነገር ያለኝንም ረጭ ያለ ቀን ይዞብኝ ሄዶ የተሻለ ፍለጋ ያለኝን እንዳላጣ ስለምፈራ እንጂ። ስለዚህ ባለኝ ቀን አርፌ እውላለሁ። አዲስን ነገር በመሞከር ውስጥ የተሻለ ነገር ሊኖር እንደሚችልም ጠፍቶኝ አይደለም። የመሆን አጋጣሚው 0.00002 % ቢሆንም የባሰውን የምጋፈጥበት ዝግጁነት የለኝም! ስለዚህ ጨው የሌለበት አልጫ አልጫ የሚል ቀኔን እያመሰገንኩ እሰለቅጣለሁ።

"እንደውም ሀሳቤን ቀይሬያለሁ! ፀጉሬ እስኪሸብት እጠብቅሻለሁ" ብሎኝ ነበር ግሩም እየሳቀ የዛን ማታ ወደቤቴ ሲሸኘኝ። ራይድ ጠርቶ ነበር የሸኘኝ።

"እስከመቼ ነው መኪና የማትይዘው?" ስለው

"እሷ እስክትነቃ! ነቅታ ጥፋትህ አይደለም ካለችኝ የዛኑ ቀን ካለሽበት መጥቼ ወደምትፈልጊበት እሸኝሻለሁ።"

"ካልነቃችስ?"

"አላውቅም! ምን ያህል ጊዜ እንደሚወስድብኝ አላውቅም! ጊዜ እፈልጋለሁ" ነበር ያለኝ።

ከግሩም ጋር እራት መብላቴ ስለግሩም ያለኝን ነገር አይደለም የቀየረው። ባልገባኝ ምክንያት በዙሪያዬ ያሉትን ነገሮች የማይበትን መነፅር እንደቀየረው ገባኝ። እና ለማድረግ የማልደፍረውን ነገር ደፈርኩ። አቢጋ ደወልኩ! እስከዛሬ ያልነገርኳትን ቻው እንኳን ሳትለኝ መሄዷ እንዴት እንዳስከፋኝ፣ በህይወቷ እንዳልነበርኩ ስትረሳኝ የተሰማኝን መታመም ልነግራት እንጂ ልወቅሳት አይደለም።

'ህይወት የቅፅበቶች ጥርቅም ናት' ትላለች እማዬ። ቤተሰቦቼ በጣም ለጥቃቅን ነገሮች ትኩረት የሚሰጡ፣ ትንንሽ ለውጦችን ትኩረት ሰጥተው የሚከታተኩ ዓይነት ናቸው። ደስታም ይሁን ሀዘን። ለምሳሌ እማዬ ሰራተኛ መቅጠሬን ከዩንቨርስቲ የመመረቄን ያህል እኩል እንደትልቅ ክስተት እንደምትደሰትበት ፣ ከግሩም ጋር እራት መብላቴን ስነግረው ማት ስራ ቦታ መጥቶ የተሰማኝን ስሜት እንደሚያረጋግጠው ፣ 'ባባ ፖፖ ላይ ተቀምጦ ነው የሚሸናው' ስላቸው አባዬ እቤት ድረስ መጥቶ 'ወንዶቹ እንዴት እንደሚሸኑ ላሳይልሽ' እንዳለኝ አይነት .....ህይወት የትልቅ ክስተቶች ጥርቅም አይደለችም! ልክ ስለሰው ያለንን ነገር በጥሩም ይሁን በመጥፎ ለመቀየር አንድ ሰው እንጂ የሰው ልጅ ሁሉ እንደማያስፈልገው ....... በአንድ ሰው ምክንያት መላ የሰው ዘርን እንቀየማለን፣ እንፈራለን፣ እንጠላለን እንጠራጠራለን እንደዛው በአንድ ሰው ምክንያት ደግሞ መላ ህይወትን እንወዳለን ለመኖር እንጓጓለን ፍጥረትን ሁሉ እንወዳለን እንደዛ .....
የሚገርመው ያ አንድ ሰው ባደረጋት አንዲት ስህተት ወይም አንዲት መልካምነት ይሆናል እንደዛ ዓለማችን የሚገለባበጠው

"ይቅርታ አድርጊልኝ ፌቪዬ እንደዛ እንዲሰማሽ እንዳደረግኩ በጭራሽ አላውቅም! ልጆች ነበርንኮ!" አለችኝ አቢ ፀጥ ብላ ከሰማችኝ በኃላ .... ከዚህ ሁሉ ዓመት በኋላ ዛሬ የሆነ ያህል እያንዳንዱን ነገር ማስታወሴ የገረማት ትመስላለች። እንዳሰብኩትም የሆነ ሸክም ከላዬ ላይ የቀለለኝ ስሜት ተሰማኝ።

እንዲህ ነውኮ አይደል? የተቀየማችሁት ሰው፣ በእሱ ምክንያት እንቅልፍ ያጣችሁለት ሰው፣ ህመማችሁን ለዓመታት ያስታመማችሁበትን ቁስል የሰጣችሁ ሰው ጭራሽ መከፋታችሁንም ላያውቀው ሲችል? ልክ እሱ ከእናንተ ህይወት ሲወጣ ረስቷችሁ ህይወቱን እንደኖረው እናንተም ረስታችሁት የኖራችሁ ሲመስለው? ለልጄ የመከርኳትን ምክር ለራሴ መተግበር ነበረብኝ።

"አቢዬ ቂም አልያዝኩብሽም። ካልነገርኩሽ አይወጣልኝም ብዬ ስላሰብኩ ነው የነገርኩሽ። ከሰሞኑ የገባኝ እኔ ያለስስት እንደእህቴ ሊወድሽ የሚችል ትልቅ ልብ ስለነበረኝ እንጂ የወደድኩሽ አንቺ ስለሚገባሽ አልነበረም። ያኔ ቢገባኝ ደስ ይለኝ የነበረው ልቤ ፍቅሩን የተሳሳተ ቦታ ማፍሰሱ እንጂ መውደዱ ስህተት እንዳልነበር ባውቅ ነበር።" አልኳት። ስልኩን ዘግቼው አስብ የነበረውም ያንን ነው። በህይወቴ ውስጥ በብዙ ወድጃቸው በተመሳሳይ ሁኔታ በአካል አጊንተው እንኳን ሊሰናበቱኝ ላልፈለጉ ሁለት ሰዎች መውደዴ ስህተት ይመስል ራሴን ስቀጣ የኖርኩርኩት እኔ! ረስተውኝ ስለኖሩ መታመሜን እንደመሸነፍ ቆጥሬው በራሴ የምበሳጨው እኔው!

ደስ የሚል ስሜት ሲሰማኝ ከረምኩ። ቀኖቼ የተለመዱት ቢሆንም ስሜቴ ግን ይለይ ነበር:: (እንደዋዛ ቀናት ወራትን ተክተው በአንዱ ጠዋት ከሆስፒታል ተደውሎ ሄለን መንቃቷ እስከተነገረኝ ሰዓት።) የሚሰማኝን ስሜት መለየት ቸገረኝ። የሆነ ደስ የሚል ስሜት ከዛ ደግሞ የሆነ የተወናበደ ልቤን ክብድ የሚለው ስሜት ከዛ ደግሞ የመከፋትም ስሜት በአንድ ጉዳይ ሁሉም ስሜት። ለደቂቃዎች ስልኬን እንኳን ከጆሮዬ ሳላወርደው ቆየሁ። ድንዝዝ ያለ ስሜት .........
997 viewsDAVE / PAPI, 12:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-30 15:51:51
በር ላይ እንደመግቢያ የሚያገለግለው ፓስታ ፣ መኮሮኒ፣ ሩዝ ... ደረቅ ምግብ ፣ የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ፣ አልባስ ይሆናል ! ቀን 23/4/2014 በብሔራዊ ቴአትር ቤት ይቀርባል ! በለቱ ከጠዋት ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር በር ላይ ደም የሚሰጥ ይሆናል ። ቴአትሩ የሚቀርብበት ሰዓት 11:30 ይጀምራል

@wegoch
1.1K viewsLeul Mekonnen, edited  12:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-29 19:37:33 የአብዮት ፍሬ ነኝ 2

ዱርዬ ነው ፊቱ !

ብዙ አይነት ፈተና አውቃለሁ። የአምስተኛ ክፍል የሁለተኛዋ ክፍለ ጊዜ ፈተና ግን እንዴት ይገለፃል?

ሁለተኛ ክፍለ ጊዜ የእረፍት መንደርደሪያ ናት። የየሺ ጮርናቄ የሚጠበሰው በሁለተኛዋ ክፍለ ጊዜ ነው።

የጮርናቄ ሽታ ከሸክላ ጥብስ ሽታ በላይ ያማልላል...ከጭቅና ጥብስ በላይ ያነሆልላል። ምድረ ውሪ ነፍሳችን ዝቅ የምትልለት ውብ መዓዛ! በዛ ሰዓት ከገነት ፍሬ በላይ ለጮርናቄ ሽታ እንንበረከካለን። ከፈጣሪ አልቀን ለፓስቲ እንሰግዳለን። 

ወንድማችን ፓስቲ ሆይ

በሰማይ የምትኖር ብለን ለመፀለይ አይሸመቅቀንም እንደውም ማንም ሰባኪ መጥቶ ገነት ምን ትመስላለች ቢለን...ሰማዩም ...ምድሩም...ዛፉም...ድንጋዩም.. .ሳሩም ጮርናቄ የሆነ ቦታ ብለን የምንመልስ ይመስለኛል። 

ያቺ ሰዓት የቤት ልጆች ከፍንዳታ ልጆች ተለይተን የምንቁለጨለጭባት ክፉ ትውስታችን ናት።

አንድ ብር ከስሙኒ ማግኘት ተዓምር ነው...ምትሀት ነው...ድግምት መተት ነው ለኛ !

እነ ፍንዴክሶቹ እስጢፎና ቦጌ ለዚህ የታደሉ ናቸው ። በሁለተኛው ክፍለ ጊዜ አስፈሪው ሂሳብ መምህራችን ቢከሰቱ እንኳ እነ እስጢፎ በመስኮት ከመዝለል አይመለሱም። 

እኛ ሆዳችን እየተላወሰ ጂኦሜትሪ ምናምን እንማራለን ። የሌላውን ባላውቅም እኔ ግን በዛች ፔሬድ ትምህርት አይገባኝም።

እንኳን ጂኦሜትሪ ቀላሉ አማርኛ እንኳ ለኔ ፊዚክስ ይሆንብኛል። በሁለተኛው ክፍለ ጊዜ አንድ የአማርኛ መምህር የቆጡን አወርድ ብላ ቢጀምሩ የብብቷን ፓስቲ ጣለች ከማለት አልመለስም

የሆነውም ሆኖ ግን ዱርዬ ነው ፊቱ የዋህ ነው ልቡ ይሉት ዘፈን የገባኝ ያን ጊዜ ነው። 

ቸካዮቹ እነ አቤኒ (የሀብታም ልጅ ነው እኮ)

ጮርናቄ ገዝተው አካፍሉን ስንላቸው ፓስቲውን በርገድ ያደርጉና ምራቃቸውን እንትፍ ይሉበታል። ወሽመጥህ አብሮ ቁርጥ ይላል ።

እስጢፎ ግን የዋህ ነው...ከገዛት ፓስቲ ውስጥ አርባ አራቱንም ታቦት ጠርተን ቢሆን ያካፍለናል። ያቺን አንድ ጉርሻ ማን ወንድ አላምጦ ይውጣታል? እንደ ጫት ተርዚና ወጥረን ደቂቃዎችን እንቆያለን ። 

እንደውም ከኔ ጋር ከሚለምነው ቢኒያም ጋር አንድ ቀን ተጣልተናል።

ቢና ፓስቲዋን አንዴ ቆርሶ ውጧታል። እረፍት ጨርሰን ስንገባም ያላምጣል። ከኛ ተደብቆ ኪሱ ውስጥ ይዞ ይሆናል ብዬ በረበርኩት ወፍ የለም። 

ቀስ ብዬ ስሾፍ እጁን የትም ሳይሰድ አፉ ግን ያላምጣል። ከቆይታ በኋላ አንድ ነገር ገባኝ።

ቢኒ ጮርናቄዋን በእረፍት ሰዓት ቢውጣትም...መልሶ መላልሶ እያጋሳ እንደ ፈረስ መኖ እያመነዠካት ነበር።

ስነቃበት ደነገጠም ...አፈረም...እኔና ጓደኞቼ ደግሞ ዜብራው እያልን ሙድ ያዝንበት.. .እንደ ፈረስ አሽካካንበት.. .

ከዛች ቅፅበት በኋላ ቢኒ እኔን ሲያየኝ ብዙ አልመቸውም

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Mikael Aschenaki
984 viewsDAVE / PAPI, edited  16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-28 21:05:39 "ድንገት ከመሬት ተነስቶ እራት ልጋብዝሽ ብሎኝ ግን አይደለም ዴት የተደራረግነው?"
"ደብዳቤ ይፃፍ? የልብ ስዕልስ ይጨምርበት? መንገድ ላይ እየጠበቀ ሳታዪው ከጀርባሽ እየተከተለ ለአንድ ዓመት ይሸኝሽ? አንቺን ለማየት ደሞዙን 30 ቦታ ከፍሎ በየቀኑ ባንክ እየመጣ አስር አስር ብር በየቀኑ ሴቭ ያድርግ? "
(ቢጫ ሰውዬ ያለው 'አዲስ' እንደዛ ነበር ያደረገው። በመጨረሻ እሺ ብዬው ሁለት እራት እንኳን በስርዓቱ ሳንበላ ነው የተለያየነው።)
"For God sake ዴት ለማድረግ እየደረሰች ያለች ልጅ ባደረሽበት እድሜ እንደኮረዳ መሽኮርመም? እህቴ! ትልልቅ ሰዎች እንደዚህ ነው የሚያደርጉት በአዋቂ ደንብ ተገናኝተው ይነጋገራሉ። ይተዋወቃሉ። አብሮ የሚያስኬድ ነገር ካላቸው ይቀጥላሉ ካልሆነ ተነጋግረው መንገዳቸውን ይለያሉ!"
"እኔ ይሄ ጠፍቶኝ ነው? "
"ጠፍቶሽማ ነው!" ይንፈቀፈቃል። "ትልልቅ ሰዎች ሌላ የሚያደርጉት ምን መሰለሽ? አንደኛው እስኪደውል አይጠባበቁም! ደውዪና እራቱን መች እናድርገው ?በይው።"
"አላደርገውም! በፍፁም!"
"እህቴ? " አለኝ ሳቁን ጨርሶ እየተኮሳተረ አንድ አንዴ አንዳንዴ ሲያዝንልኝ በሚያወራበት ፊቱ «ብቻሽን ዘመንሽን ሁሉ ትኖሪያለሽ? የሰው ልጅ ደግሞ ቀርበሽ ሳታውቂው ወጥ ውስጥ ያለጨው እንደሚቀመሰው ቅምስ አድርገሽ አታውቂውም! እድሉን ስጪውና ሞክሪው!"
"ብወደውና ልቤን ቢሰብረውስ?"
"የፍቅር ቀመሩኮ ያ ነው እህቴ! ስትወጂ ሊሰብረው እንደሚችል እያወቅሽ አምነሽ ልብሽን ትሰጫለሽ! አንዳንዱ ይጠብቅልሻል። አንዳንዱ ደግሞ እንደፈራሽው ሰብሮ ይመልስልሻል። ደፍረሽ ካልሞከርሽው ግን ልብሽን እንደእንቁ ሊጠብቅልሽ የሚችለውንም ገፋሽው ማለት አይደል?"
"እሺ ይሁን እንበልና ብወደውኮ የባባን እናት የገጫትን ሰው ማለት ነው። አይበለውና ባትተርፍ እናቱን የቀማውን ሰው ዴት ማድረጌን ሲያውቅ ባባ ምን ይለኛል? "
"ታወሳስቢው የለ እንዴ?" አለኝ ግርም ብሎት እያፈጠጠ። ......
ይቀጥላል.....

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
940 viewsDAVE / PAPI, 18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-28 21:05:39 አታምጣ ስለው አምጥቶ ቆለለው #8
«ስትነቃ ውሳኔሽን ባትቀበልስ” አለኝ ማት። የግሩምን ጉዳይ በሽምግልና እንዲያልቅ መወሰኔን ስነግረው።
"አስቤዋለሁ ማትዬ ... ይህቺ ሴት ሱቅ ውስጥ ተቀጥራ ነበር የምትሰራው። የቤት ኪራይ ከፍላ ...ልጇን አሳድጋ ... የትምህርት ቤት ከፍላ .... ምን ዓይነት ህይወት የነበራት ይመስልሃል? ይህቺ ሴት አንድ ቀን የምትጎርሰው ብታጣ ሄዳ የምትጠጋበት ዘመድ እንኳን የላትም። ታዲያ ለዝህች ሴት የገጫትን ሰው በእስር ከማስቀጣት እና ለልጇ የወደፊት ህይወት ዋስትና የሚሆናት ተቀማጭ ገንዘብ ከማግኘት የቱ ይበልጥባታል?"
"እሺ ካሳው ምን ያህል ብር እንዲሆን ነው ያሰብሽው?"
"ለዛ ነው እኮ የፈለግኩህ! ጉዳዩን በቁም ነገር እንዲይዙት እፈልጋለሁ። የሽምግልና ሂደቱ በትክክል ይደረጋል። ሰዎቹ ሀብታም ነገር ናቸው። ጥሩ ሰዎችም ይመስላሉ! እናትየው ልጇ አይታሰርባት እንጂ ምንም ያህል ብንላት አታመነታም! ብቻ ለባባ የወደፊት ዋስትና የሚሆን ገንዘብ መጠን መሆን አለበት። ሽምግልናውን የሚይዙልን ሰዎች አዘጋጅልኝ! "
"እንደገባኝ ከሆነ ያሰብሽው ገንዘብ ትንሽ አይደለም። ባይስማሙስ? "
"ምንም ቢሆን በልጄ ጉዳይ እንደማልቀልድ ማወቅ አለባቸው።" ባባን 'ልጄ!' ብዬ መጥራቴን ያስተዋልኩት ማት ያንን የስስት ፈገግታውን ፈገግ ሲል ነው።
"እሺ መች እንዲሆን ነው ያሰብሽው?"
"ነገሩን እያሰነዳዳን ትንሽ እንቆይ። ማትዬ ትንሽ ልጠብቃት። ምንም እንኳን አሸናፊ ሃላፊነቱን ቢሰጠኝም፣ እሷም ስሜን ስትፅፍ አምናብኝ ቢሆንም ህይወቱ የሷ ነው። የሷ የወደፊት ነው። ምንም የሚያስቸኩለን ነገር የለም! ልጠብቃት!"
"እሺ አያድርገውና ብትሞትስ?"
"ውሳኔዬን የፈራሁት እሱን ሳስብ ነው። ያሰብኩት ገንዘቡ ለባባዬ እንዲቀመጥለት ነው። ራሱን ሲችል የሆነ ነገር ለመጀመር ይረዳዋል። እናቱን አይመልስለት ይሆናል። ቢያንስ ግን ለሆነ ነገር ይጠቅመዋል። ግሩም ቢታሰርም እናቱን አይመልስለትም። ግን ትልቅ ሆኖ ከገንዘቡ ይልቅ እናቴን ያሳጣኝ ሰው ቢቀጣልኝ ነበር የምፈልገው ቢለኝስ? ይቅር ባይለኝስ? ቢጠላኝስ?"
"እህቴ ያንቺ ልጅ ሆኖ አድጎ እንደሱ ይላል ብዬ አላስብም! ካንቺ ጋር አይደለም አድጎ አንድ ቀን አድሮ ያንቺ ልብ የማይጋባበትኮ አይኖርም! ትልቅ ሲሆን እንዳንቺ ይቅር ባይ፣ እንዳንቺ ጠቢብ፣ እንዳንቺ መልካም ነው የሚሆነው።"
"ሁሉም ልጆችኮ በእናታቸው አይወጡም!"
"ሁሉም ልጆች ግን እንዳንቺ ፍቅሯ የዓለምን ክፋት ሁሉ የሚያስረሳ እናት የላቸውም።"
"ባክህ እናት ሁሉ ለልጇ እንደዛ ናት።"
"ለልጇ አዎ! በዙሪያዋ ላሉ በሙሉ ግን አይደለችም። ልጆችሽ ለእነርሱ የምታደርጊውንና የምትሆኚውን ብቻ እያዩኮ አይደለም የሚያድጉት። በእያንዳንዷ ቀንሽ ለሌሎች የምታደርጊውን እና የምትሰጪውን ፍቅር ያያሉ። እነርሱም ሲያድጉ በደም ለተጋመዳቸው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ሁሉ ቅንና ፍቅር ሰጪ መሆን ትክክለኛው መንገድ መሆኑን ያውቃሉ። በልጅሽ ውስጥ ራስሽን አታዪም? "
"እኔእንጃ ማት አንዳንዴ እኔ እንደምትሏት ዓይነት ቅን ሰው ከሆንኩ፣ ሁሌ እንደምትለኝ ገራሚ ልብ ካለኝ ለምንድነው አምላክ ደስተኛ ሆኜ እንድኖር ያልፈቀደው?" አልኩት
ማለት የፈለግኩት የነበረው ግን ለመጀመሪያም ለመጨረሻም ጊዜ የወደድኩት ሰው ትቶኝ ሲሄድ ጥፋቴ ምን ነበር? ሙሉ ልቤን ሰጥቼ ፍርክስክስ ያለ ልብ መቀበል ፍራቻ ወንድ መልመድ ሸሽቼ ልጄን ብቻዬን ሳሳድግ የየትኛው ጥፋቴ መከር ነበር?
"የምትፈልጊውን አምላክሽን ለምነሽው ታውቂያለሽ?"
"አምላክ እኮ ነው። የሚያስፈልገኝን ከእኔ በላይ የሚያውቅ፣"
"እራሱ አምላክ ነው 'ጠይቁ ይሰጣችኋል አንኳኩ ይከፈትላችኋል' ያለው። ሳንጠይቀው በፊት የምንጠይቀውን ስለማያውቅ አይደለም። አምላክ የነፃነት አምላክ ስለሆነ በፈቃዳችን ነው የሚያደርግልን። ፈቃዳችንን ይፈልጋል። ባይሆን ኖሮ ስንቱን ልበ ድንጋይ እያጋጨ አይመልሰውም ነበር? ምክንያቱም ልኩና የሚያስፈልገው መልካም መሆን ስለሆነ! ግን ለምርጫችን ይተወናል። አምባገነን አይደለማ!"
"እንዴ? የምንፈልገውና የምንጠይቀው ሁሉኮ ልክ አይደለም። አንዳንዴ የማይበጀንን እንጠይቃለን። እርሱ ግን የቱ እንደሚበጀን ያውቃል።"
"እኔ የማምነው ለምሳሌ 'አምላኬ ሆይ ደስተኛ አድርገኝ!' ብለሽ ስትለምኚ ምናልባት ያንቺ ልመና ገንዘብ ሊሆን ቢችል እርሱ ደስታሽ ልጅጋ ከሆነ ያለው ልጅ ይሰጥሻል። የለመንሽው ደስታን ነውና ደስታሽን ታገኛለሽ። እኔ እንደዛ ነው የማስበው!"
"እና ስላልጠየቅሽ ነው ያልተሰጠሽ ነው የምትለኝ?"
"ያንቺ ከዛም ያልፋል እህቴ!" ሳቅ እያለ "አምጥቶ አልጋሽ ላይ ቢያስተኛልሽም ራሱ 'የእግዜር እንግዳ' ነው ብለሽ አልጋሽን ለቀሽለት ትሄጃለሽ! ቢሰጥሽም ለመቀበል ዝግጁ አይደለሽም።"
"ባል ነው የምፈልገው ወጣኝ?" አልኩት ፈገግ ብዬ። ሁሌም ሳልናገር በፊት ያሰብኩት እንዴት እንደሚገባው ግርም ይለኛል።
"እኔስ እንግዳ ተቀባይ ነሽ አልኩ እንጂ ባል ትፈልጊያለሽ ወጣኝ? እኔ የምለው እማዬ ባባን እንዳላመጣሽው ነገረችኝ ለማን ትተሽው ነው ስራ የገባሽው?" አለኝ። ስራ ስገባ እነእማዬጋ እየተውኩት ነበር የምሄደው።
"የምታይልን ልጅ ቀጠርኩ" ስለው የሆነ የምስራች የነገርኩት ነበር የሚመስለው። ደስ አለው።
"ምነው? ምንድነው የሚያስፈነድቅህ?"
"እህቴ ሰራተኛ ኖራት!" ብሎ አሁንም ይፍነከነካል።
"ታዲያ ምኑ ነው የሚገርመው?"
"እስከዛሬ ሰው ሳያስፈልግሽ ቀርቶ ነበር ሰው ያልኖረሽ? 'እኔ የማንን ጎፈሬ ሳበጥር ነው ሰራተኛ የምቀጥረው?' ያልሽንን አምነንሽ ዝም ያልን ነው የሚመስልሽ? አዲስ ሰው ወደ ህይወትሽ በምንም መልኩ እንዲገባ ስለማትፈልጊ ነው። ይሄንንማ ለእማዬ እስክነግራት...."
"ኸረ አይደለም! ደግሞ እማዬም እንደዛ ነው የምታስበው?" የምርም በዚህ መንገድ አስቤው አላውቅም!!
"አንቺ ብቻ ነሽ እንደዛ የማታስቢው" አለኝ አሁንም ፈገግታው ፊቱ ላይ እየተርመሰመሰ። ቀጠል አድርጎ "ግሩም ምን አለ?"
"ስለምኑ?" ድንብር አልኩ።
"ስለሽምግልናው ነዋ!"
"ደስ ነው ያለው!! ቅጣቱን አይደል በገንዘብ የቀየርንለት? ለምን ካሳውን እንደመረጥኩ ስነግረው 'እንኳን በሞትና በህይወት መሃከል ለመሆኗ ምክንያት ሆኜ፣ እንዲሁም ልንረዳት የሚገባት ሴት ናት!' አለኝ"
"ቆይ ቆይ ከዚህ ሌላ ምን አወራችሁ?"
"ምንም!" አልኩኝ ፍርጥም ብዬ
"አላውቅሽም እና ነው? ሌላ ነገርማ አለ! ምን አለ ስልሽ እንደፌንጣ አትዘዪም ነበር።"
"እራት ልጋብዝሽ!" አለኝ።
"እና?"
" ለምን? ስለው ላመሰግንሽ አለኝ! እስከአሁን ያመሰገንከኝ በቂ ነው እራቱ አስፈላጊ አይደለም አልኩት ..." ተናግሬ ሳልጨርስ ማት በሳቅ ይንፈቀፈቅ ጀመር።
"እንዴት ያለሽው ገልቱ ነሽ?" እያለ በሳቅ ይፈርሳል ። የማይሆን ነገር ስናደርግ ገልቱ ብቸኛዋ የአባዬ ስድብ ናት። እራት ልጋብዝሽ ማለት 'ላውቅሽ እፈልጋለሁ!' ማለት እንደሆነ ጠፍቶኝ አልነበረም። አፌ ላይ የመጣልኝ ለምን? የሚል ጥያቄ ነበር። እሱም እንደማቲ 'ምኗ ገልቱ ናት?' ብሎ መሰለኝ ላመሰግንሽ! ያለኝ!! ማት መሳቁን አላቆመም!!
"ማቲዬ በእማዬ ሞት እረፍ!"
"እሺ ይቅርታ!" ለመኮሳተር ይሞክርና ደግሞ ይስቃል። "እህቴ ይቅርታ አለመሳቅ ከባድ ነው። ለምን? ምን የሚሉት ጥያቄ ነው?" ይደክማል። "ቆይ አንቺ ከአሼ በኃላ ጭራሽ ዴት አድርገሽ አታውቂም? እንዴ (እንደማስታወስ እያለ) ማነው ይሄ ቢጫ መኪና የሚነዳው ቢጫው ሰውዬ ..." ይስቃል
915 viewsDAVE / PAPI, 18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ