Get Mystery Box with random crypto!

ወግ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @wegoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.51K
የሰርጥ መግለጫ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @leul_mekonnen1

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 32

2021-12-23 12:39:56 አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #2

"የገጨሃት ቦታ ውሰደኝ ምናልባት ሰፈሯ ሊሆን ይችላል። ምናልባት ስልኳን እዛ ጥላው ሊሆን ይችላል። የሚያውቃት ሰው ሊኖር ይችላል!"

በውስጤ ምናልባት ጎዳና ላይ ቢሆንስ የምትኖረው ብዬ አስቤያለሁ ጮክ ብዬ አላወራሁትም እንጂ ምናልባት ከነአካቴው ስልክም አልነበራት ይሆናል። መታወቂያዋ ላይ ያለውን ቀበሌና የቤት ቁጥር ተከትዬ ቀበሌ ሄጄ ቤቷን ፍለጋ አስቤዋለሁ። ቀላል እንደማይሆን ግልፅ ነው። ቀበሌ አልወድም!!

"በፍፁም እኔ አልነዳም። ህም ...በጭራሽ መሪ አልይዝም። ታክሲ .....ራይድ ይጠራ" ሲል አሳዘነኝ ማንም ትኩረት ሰጥቶ እሱን ያየው የለም እንጂ እሱም ከባድ ድንጋጤ ላይ ነው። አሁንም እጆቹ እየተንቀጠቀጡ ነው። ሲያወራ መሸሻ ያጣ አይነት ዓይኖቹ መሬቱን ይምሳሉ። ይሄን እያለኝ ድርብብ ያሉ የሴት ወይዘሮ የሚያነክስ እግራቸውን በጌጠኛ ከዘራ እያገዙ የሚራመዱ ሰውዬ አስከትለው ወደ ክፍሉ ገቡ።

"ኪያዬ ......ደስ አላለኝም ! በለሊት አትጓዝ እያልኩህ ...." እያሉ እያገላበጡ ሲስሙት እና ደህና መሆኑን ሲያረጋግጡ ልጃቸው ተገጭቶ እንጂ እሱ ገጭቶ አይመስልም። እሱም እናቱን ሲያይ የሆነው የልጅ መሆን ካቀፍኩት ህፃን አይለይም ነበር። በኋላ እሱም ገብቶት ነው መሰለኝ ከእናቱ እቅፍ ወጥቶ በማፈር ሲያየኝ ነው ገና ሰው እንኳን መኖሩን እናትየው ያዩት።

"እባክሽ ልጄ አንድ ልጄ ነው በሽምግልና እንጨርሰው? (ባጌጠ ልብሳቸው እግሬ ስር ሲንበረከኩ ክብራቸው አላሳሰባቸውም። እናት ናቸዋ! ደንግጬ ደነዘዝኩ። ካሰብኩት በላይ ውጥንቅጥ ውስጥ እንደተዘፈቅኩ ገባኝ። ከተንበረከኩበት ላነሳቸው እየሞከርኩ ከአፌ ግን ቃል አይወጣልኝም።) ካሱ የምንባለውን እንክሳለን። እናትየው እስኪሻላት ህፃኑንም ቢሆን ወስጄ እንከባከባለሁ። እባክሽ ልጄን አሳልፈሽ አትስጪብኝ?"

ለደቂቃ ህፃኑን ሰጥቻቸው ጭልጥ ብዬ መጥፋት ሁሉ አሰብኩ። ባባ ቀልቡ የነገረው ይመስል ጭምቅ አድርጎ አቀፈኝ። የተገጨችው እህቴ ብትሆን ምንድነበር የምወስነው? ብትሞት የእነሱ ካሳ የህይወት ካሳ ይሆናል? እሺ ጥፋቱ የሷስ ቢሆን? እንዳለው እሷ ብትሆንስ ዘው ብላ የገባችበት? ኸረ ምን አይነቷ ሴት ናት ግን እዚህ ጣጣ ውስጥ ዘፍቃኝ ማን እንደሆነች እንኳን የማላውቃት

"እባኮትን ይነሱ። እኔ ለራሴ ዞሮብኛል።"

የተፈጠረውን አስረዳኋቸው። አባትየው መታወቂያው ላይ ባለው አድራሻ ቤቱን ሊያፈላልጉ ሀላፊነት ወሰዱልኝ። ማን እንደሆነች እና ከእኔጋር የሚያዛምዳትን ነገር እስክደርስበት ባባ እኔጋ እንዲቆይ ወሰንኩ። እነርሱም የሚያስፈልገውን ሊያሟሉለት እና ሊጠይቁት ቃል ገቡልኝ። አንድ ላይ በእነርሱ መኪና እናትየው እየነዱ አደጋው የደረሰበት ቦታ ሄድን:: ምንም ነገር የለም። ከአልፎ አልፎ ሂያጅ መንገደኛ ውጪ በአካባቢው ማንም አይታይም። የመኖሪያ ሰፈርም አይደለም። ዓይኔ መሬቱ ላይ ካለ አንድ ብር ሳንቲም ላይ አረፈ። ደም ነክቶታል። ለምን እንዳነሳሁት አላውቅም ግን አነሳሁት። የሷ ይሆን? በእጇ ይዛው ነበር? ወድቆባት ልታነሳ ስትል ይሆን መኪናውን ያላየችው? ወይስ ሌላ ሰው የጣለው ሳንቲም ነው? ስልኬ ሲጠራ ባላወቅኩት ምክንያት ደንግጬ ዘለልኩ

"አይዞሽ አይዞሽ" አሉኝ እናትየው መደንበሬን ሲያዩ

"እማ በጠዋት የት ሄደሽ ነው? " ልጄ ናት። ቤቴን ረስቼዋለሁ። ሰዓቱን ረስቼዋለሁ። ዛሬ ቅዳሜ መሆኑንም እረስቼዋለሁ።

"መጣሁ እናቴ! ለባብሰሽ ጠብቂኝ" አልኳት ቅዳሜ ጠዋት ሁል ጊዜ እናትና አባቴ ጋር ነው ቁርስ የምንበላው።

እነርሱ ስልክ ተቀያይረን እቤት አድርሰውኝ ተመለሱ። የማልዋሸው በዛው ቢጠፉስ ብዬ አስቤያለሁ። ሰው ለማመን ቅርብ አይደለሁም። የመኪና ታርጋቸውን መዝግቤ መታወቂያቸውን ፎቶ ኮፒ አደረግኩ።

"እማ ትልቅ ሰው የሚበላውን ምግብ ይበላል ኸረ ጥርስኮ አለው" ትለኛለች ልጄ ለባባ ምግብ ምን ልስጠው ብዬ ስባዝን እየሳቀችብኝ። ልጄ 15 ዓመቷ ነው። በስንት ዓመቷ ምን እንደበላች ጠፍቶኛል። ለመጨረሻ ጊዜ ገላዋን መች እንዳጠብኳት ረስቼዋለሁ ..... ባባን አጣጥቤ እነእማዬጋ ተያይዘን ሄድን::

"እግዚአብሄር የሆነ ነገር ሊያስተምርሽ ነው ይሄን ህፃን ወደ ህይወትሽ ያመጣው" አለችኝ እናቴ የሆነውን ሁሉ ከነገርኳቸው በኋላ። ከቤተሰቡ አንድ ሰው እንኳን ድንገት ቢያውቃት ብዬ አስቤ ነበር:: ማንም አያውቃትም። (እናቴ ምን ማለቷ እንደሆነ አውቃለሁ። ማግባት አለብሽ ልጅ መድገም አለብሽ ነው ቅኔው። ወንድሜ በሚያስቀና ትዳር ሶስተኛ ልጁን ሰልሷል። የእኔ ያለባል መቅረት ያሳስባታል:: )

"እማ ደግሞ እግዚአብሄር እኔን ስለሚወደኝ እኔን ለማስተማር ይሄን ህፃን አይቀጣም! የሆነችን ሴት በመኪና አስገጭቶ ለኔ ትምህርት አይሰጥም። እነርሱምኮ ፍጡሮቹ ናቸው እኔን ለማስተማር ህይወታቸውን የሚያዘባርቅባቸው አሻንጉሊቶች አይደሉም!!" አልኳት። ወንድሜና አባቴ ተያይተው ጨዋታውን ቀየሩት። ከእማዬጋ እንዲህ አይነት ወሬ ከጀመርን ማባሪያ የሌለው ጭቅጭቅ እንደሆነ ያውቃሉ:: እዛው ቤተሰቦቼ ቤት ሆኜ ወደ ከሰዓት ስልኬ ጠራ ባባ ኩርምት ብሎ ከተኛ ሰዓታት አልፈውታል።

"አብርሃም ነኝ"

"አብረሃም? አብረሃም?"

"የግሩም አባት! ልጅቷን የገጫት ልጅ አባት... "
"እእ ....እሺ "

"የምትኖርበትን ቤት አግኝተነዋል። አከራዮችዋን አናግረን የእሷ ቤት መሆኑን አረጋግጠናል።"

"በዚህ ፍጥነት? እንዴት? ያውም በቅዳሜ?"

"ብዙም አስቸጋሪ አልነበረም:: የቤት ቁጥሩ የአከራዮችዋ ቤት ነው:: ደግሞስ የልጄ ጉዳይ አይደል? ይልቅ መምጣት ሳይኖርብሽ አይቀርም። ከባሏ ውጪ ማንም ዘመድም ሆነ የቅርብ ሰው እንደሌላት ነው የነገሩን።"

"ታዲያ ባሏ እያለ እኔን ምን ቤት ናት ብላ ነው የፃፈችኝ?"

"ባሏ ከታሰረ ሁለት ዓመት አልፎታል።"

"እሺ እኔ ምን ቤት ነኝ መታወቂያዋ ላይ የተገኘሁት? ወይ ፈጣሪ ! "

"እኔ ምን አውቄው ብለሽ? (እኔ አልፃፍኩሽ የሚል አንድምታ ባለው ለዛ) ምናልባት በባለቤትዋ? እስር ቤት ያለ የቅርብ ሰው ወይ ዘመድ የለሽም?"

"በፍፁም ኸረ እኔ ጭራሽ የታሰረ የሩቅም ሰው አላውቅም። "

"ምናልባት አከራዮችዋ ከሚነግሩሽ ነገር ፍንጭ ልታገኚ ስለምትችዪ ብትመጪ መልካም ይመስለኛል:: ብዙ አመት ኖራለች አብራቸው.... እ.... ባለቤቷ ... አሸናፊ ይባላል ነው ያሉኝ .......እንደው ካወቅሽው "

ከጀርባዬ የሆነ ነገር ማጅራቴን በሀይል የደለቀኝ ነገር መሰለኝ .........ጭው አለብኝ። አይሆንም። እሱማ አይሆንም! ሊሆን አይችልም።... ስም ተመሳስሎ ነው.... ማሰብ ተሳነኝ!!

"ምነው ሴትየዋ ሞተች እንዴ?" ትለኛለች የወንድሜ ሚስት ......

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
1.4K viewsDAVE / PAPI, 09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-21 13:49:29 አታምጣው ስለው .... አምጥቶ ቆለለው (ርዕስ ነው)

የስልኬ ጥሪ ነው ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ። ከንጋቱ 12:10

"ከሆስፒታል ነው የምንደውለው!! ዶክተር ፈቃደ እባላለሁ።"

"በየሱስም! እናቴ ምን ሆነች?" ብድግ ብዬ ቁጭ አልኩ:: ማታ ስኳሬ ከፍ ብሏል ስትለኝ ነበር።

"ወይዘሮ ሄለን አበራ አደጋ ገጥሟቸው ...."

"ሄለን አበራ? በስመአብ! (ልቤ ጉሮሮዬጋ ደርሳ ነበር ምልስ ብላ አቃፊዋ ውስጥ ስትገባ ታወቀኝ) ምነው እያጣራችሁ ብትደውሉ? በዚህ ጠዋት ያልታመምኩትን ሴትዮ በድንጋጤ ልትገሉኝ ነው እንዴ? ተሳስታችኋል!! እኔ ሄለን አበራ የምትባል ሴት አላውቅም! "

"ወይዘሮ ፌቨን አዳነ አይደሉም?"

"ነኝ!" አሁን ግራ ገባኝ። ስልኬን ቢሳሳት ስሜን ግን አስተካክሎ ሊጠራ አይችልም።

"የአደጋ ጊዜ ተጠሪ ተብለው የተመዘገቡት እርሶ ኖት!" ከአልጋዬ በደመነፍስ ወረድኩ

"እህ እኔ እንዲህ የምትባል ሴት አላውቅማ? ቆይ የሆነውን አስረዳኝ ምን አይነት ሴት ናት? ምን አይነት አደጋ ነው የገጠማት?"

"የመኪና አደጋ ነው። ለጊዜው conscious አይደለችም:: ቦርሳዋ ውስጥ ባገኘነው መታወቂያ ላይ የእርሶን ስልክና ስም ነው ያገኘነው።"

"እሺ መጣሁ!" አልኩኝ ነገሩ ምንም ስሜት ሳይሰጠኝ ..... አደጋ ደርሶ ነው እየተባልኩ ከዛ በላይ ጥያቄ ማብዛት ክፋት ነገር መሰለኝ። የእኔን ስም የአደጋ ጊዜ ተጠሪ ብሎ ሊመዘግብ የሚችል ዘመድ አሰብኩ ........ ምናልባት በቤት ስሟ የማውቃት ዘመድ ..... ጭንቅላቴ እዚህም እዛም እየረገጠ የተባልኩት ሆስፒታል ደረስኩ እና የተባለውን ዶክተር አገኘሁት። የተባለችው ሴት የተኛችበት ክፍል ወሰደኝ። ሰውነቷ በአብዛኛው በፋሻ ስለተጠቀለለ የማውቃት ሴት እንኳን ብትሆን መለየት አልችልም ነበር።

"የማውቃት አይመስለኝም!" አልኩት ግራ ገባቶኝ። ከጋውን ኪሱ መታወቂያዋን አውጥቶ ሰጠኝ። ሲገለባበጥ ሌላ ምስል ያሳየኝ ይመስል እያገለባበጥኩ አየሁት። በፍፁም አላውቃትም! ስሜና ስልክ ቁጥሬ ግን የመታወቂያው ጀርባ ላይ ቁልጭ ብሎ ተፅፏል። እድሜ 30 .... ቆንጅዬ ወጣት ናት። ፎቶዋ ላይ ጥርሷን ሳትገልጥ ፈገግ ብላለች። በወፋፍረሙ ተገምዶ ደረቷ ላይ የተዘናፈለ ፀጉር አላት ..... በፍፁም አይቻት አላውቅም።

"ማነው ሆስፒታል ያመጣት?" አልኩኝ ትክክለኛ ጥያቄ ይሁን ሳልረዳ

"አደጋ ያደረሰባት ሰው ነው ይዟት የመጣው። መጠበቂያ ክፍል ተቀምጧል ልታገኚው ከፈለግሽ? " ብሎ መልሴን ሳይጠብቅ በሩን ከፍቶ ወጣ ተከተልኩት የተባለው ሰው ከዶክተሩ ጋር ወደክፍሉ ስገባ ሲያየኝ ዘሎ ከመቀመጫው ተነሳ ..... አጠገቡ ተቀምጦ የነበረ በግምት የ4 ዓመት የሚሆን ህፃንም ተከትሎት ብድግ አለ።

"ቤተሰቧ ነሽ? ምን ማድረግ እንደነበረብኝ አላወቅኩም ነበር! እጄን ለፖሊስ ልስጥ? እሰጣለሁ በቃ! (መላ አካሉ ይንቀጠቀጣል።) ከየት መጣች ሳልላት ነው ዘው ብላ የገባችብኝ በቦታው የነበረ ሰውም አልነበረም። አልነጋምኮ .... የሞተች መስሎኝ ነበር !" ድንጋጤው እንዳለ ነው የለበሰው ጥቁር ሱፍና ነጭ ሸሚዝ በደም እንደተነከረ ነው። እጆቹ ላይ የቀረውን የደረቀ ደም ሊጠርገው ግድ ያለው አይመስልም ወይም ከነጭራሹ ደም እጁ ላይ መኖሩንም አላስተዋለውም። ግራ ገባኝ። ምንም በማላውቀው ክስተት ውስጥ የተነከርኩት እኔ ምን ልበል? አይኖቼ ህፃኑ ላይ መንቀዋለላቸውን ሲያይ

"ልጇ ነው። አብረው ነበሩ። እማ ብሎ ሲጮህ ነው ያየሁት እኔ እንጃ ምን እንደተፈጠረ። እሱ የእግረኛ መንገድ ላይ ነበረ። ቤተክርስቲያን እየሄዱ መሰለኝ ነጠላ ለብሳ ነበር። .... ቤተክርስትያን ለመሄድ ራሱ በቅጡ አልነጋም ነበር:: "

ምን እንደማደርግ ሳላውቅ ህፃኑጋ ተጠግቼ በርከክ አልኩ። ደነበረ። ትንንሽ እጆቹን ልይዛቸው እጄን ስዘረጋ ሰበሰባቸው።

"ስምህ ማነው?" አልኩት እናቱን መኪና ሲገጫት በአይኑ ካየ ሁለት ሰዓት ላልሞላው ህፃን የእኔ ጥያቄ ምኑ ነው? እኔስ ምኑ ነኝ? ዓለምስ ራሱ ምኑ ናት?

"ባባ" አለኝ የደረቁ ከንፈሮቹን እያላቀቀ

"ባባዬ እኔን ታውቀኛለህ?" አልኩት የማይጠየቅ ጥያቄ እንደሆነ እያወቅኩ። በአሉታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ።

"አባትህ የት እንደሆነ ታውቃለህ?" አሁንም በአሉታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ። ግራ ገባኝ! ይህቺ ሴት ማናት? ለምንስ ነው የማላውቃት ሴት መታወቂያ ላይ የእኔ ስም የሰፈፈረው?

"ዶክተር እሷ ያለችበትን ሁኔታ ንገረኝ? ትድናለች አይደል? " እንድከተለው ምልክት ሰጥቶኝ ወደ ቢሮ ይዞኝ ሄደ። ያለችበት ሁኔታ አሳሳቢ እንደሆነ ለመገመት አልተቸገርኩም።

"ተጨማሪ ምርመራዎች አዝዣለሁ። ውጤቶቹ እስኪመጡ እርግጠኛ የሆነ ምላሽ ልሰጥሽ አልችልም። ጭንቅላቷ በሃይል ተጋጭቷል። እንዳልኩሽ ሁሉም ውጤት ሳይመጣ ብዙም ማለት አልችልም።"

"የምትድን ይመስልሃል ግን? የምትነቃ ይመስልሃል?"

"ይቅርታ ይሄን አሁን መናገር አልችልም።"

"እሺ እኔ ምን ላድርግ? አላውቃትምኮ? ህፃኑንስ ምን ላድርገው? ምን ጉድ ውስጥ ነው የገባሁት?"

"የማታውቂያት ከሆነ ሆስፒታሉ ለፖሊስ የማሳወቅ ግዴታ አለበት" አለኝ። አላውቃትም ያልኩትን ግን ያመነኝ አይመስልም።

"እሺ የገጫትስ ሰውዬ?"

"ቤተሰብ ቢገኝ ወይ በሽምግልና ያልቃል ወይ ይከሱታል። እንደምትዪው የማታውቂያት ከሆነ ጉዳዩን ለፖሊስ ማሳወቅ ግዴታችን ነው። ሰውየው የማምለጥ ሀሳብ የለውም። ሲገጫት ማንም አላየውም ጥሎ መሄድ ይችል ነበር። ይልቅስ ያላነሰ ብር ከፍሎ የግል ሆስፒታል ሊያሳክማት ፈቃደኛ ከሆነ በህግ ይዳኝ በሽምግልና ቤተሰብ ነው የሚወስነው።"

ሁሉንም ጥዬ መሄድ ፈለግኩ። ምን አገባኝ እና ነው እዚህ ጣጣ ውስጥ የምገባው ብዬ ..... ወደመጠበቂያው ክፍል ስመለስ ህፃኑ የምስራች የምነግረው ይመስል ከተቀመጠበት ዘሎ ተነስቶ በተስፋ አይን አይኖቼን ሲያየኝ እግሬ የሚቀጥለውን እርምጃ መራመድ አቃተው:: አጠገቤ ደርሶ ትንሽዬ ፊቱን ወደ ላይ አንጋጦ እያየኝ ሊያለቅስ ጉንጩ እየተንቀጠቀጠ

"እማዬስ?" አለኝ:: እንባው ከፊደሎቹጋ ከአይኑ እየወረደ..... ከሱ ብሼ እንደህፃን ማልቀስ አማረኝ:: አቅፌ ብድግ እያደረግኩት በዛች ቅፅበት አብሬው እማገዳለሁ እንጂ እሳት ውስጥ ጥዬው እንደማልሄድ አወቅኩ። ...

ይቀጥላል ........

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
1.0K viewsDAVE / PAPI, 10:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-21 06:32:59
ስለ ሰማይ ብዙ እንደማውቅ እንዳይሰሙ....ጥያቄያቸው ያዝለኛል...

ደመና የት ነው ሚቀመመው...

የዝናብ ጥንስስ መች መች ነው ሚወጣው...

ንፋስን የት ነው ሚያራግቡት...

እያሉ ሲነዛነዙ ሰምቻለው...እንዳያቁብኝ ቤተኝነቴን የሩቅ ወዳጅ የመሬት ዘመድ ብመስላቸው ይቀለኛል።
Ribka Sisay
......
@ribkiphoto
639 viewsRibka Sisay, 03:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-20 22:39:46 ገና አስፓልቱን ተሻግሬ ሳልጨርስ ድርድር ብለው የቆሙት መኪኖች ተለቀቁ.. ዘጭ ዘጭ እያልኩ ቂጤን እያናጋሁ ተሻገርኩ። እዛና እዚህ አራርቄያቸው የምተኛቸው እግሮቼ ብቸኝነት
ተመችቷቸው ዳሌያቸው እያደር ይሰፋል። ጎንበስ ብዬ ከሁለት ወር በፊት ይሰፋኝ የነበረ አሁን አጣብቆ የያዘኝን ሱሪ አየሁ ለንፋስ ቦታ የለውም። አፍ ቢኖረው ድረሱልኝ የሚል ያህል ከአካሌ ጋር ተዋድዷል። ምናልባት ሳወልቀው በሌሊት ተምበርክኮ ለጅንስ አምላክ ስቃዩን ያስረዳ ይሆናል። እንጃ... <<ምን እያየሽ ነው?>> አለኝ ካቀረቀርኩበት ጥቁር ከፋይ ጫማው ብቻ የሚታየኝ ሰው ... መንገድ ላይ የሚያዋራኝ አይደለም የሚያየኝን <<ምናገባህ>> ብለው ከእብድ ይቆጠርብኛል ብዬ እንጂ ደስታዬ ነው። ለጥያቄው ምላሽ የሚሆን በነገር አካሄድ ትከሻውን በሀይል ገፍቼው አለፍኩ። ውስጤ እጁን የሰቀሰቀ ወጠምሻ ፤ከልስልስ ገላዬ ስር ጉንጩን በፀብ የጫረ ነገረኛ ወንድ ያለ ይመስለኛል...ሁሌም። <<ኧረ ተይ እንተዋወቃለን >>አለኝ ያው ድምፅ ሮም የተሰራችበትን ግዜ ያህል ፈጅቼ ላየው ዞርኩ ... እሱ ነው። ረጅም፣ የቀይ ዳማ ፣ ትናንሽ አይኖች፣ የፊት ጎልማሳ የሌላቸው ልጅ እግር የጥርስ ቤተሰቦች፣ ኪንኪ ፀጉር፤ ጥቁር ኮት ያጠለቀ ሰፊ ትከሻ፣ ጥቁር ሰአት ያጠለቀ ደብዳቤ የፃፈልኝ እጅ፣ ለስላሳ ሽቶ የሚያተን ኩሩ ገላ ሁልጊዜም ከሚንደኝ ሳቁ ጋር ... እራሱ ነው።
-
አስታውሳለሁ ግቢ እያለሁ ከድርድር ሴት ጓደኞቼ መሀል በሚያማምሩ ትንንሽ አይኖቹ ይፈልገኝ ነበር። ሳያምረኝ ቀርቶ ሳይሆን እንደሁሉም ሴቶች እንዳልወደው እየፈራሁ <<መጣ መጣ>> ሲሉ ገና አይኔን በሌላ አቅጣጫ እጥል ነበር። እንደማላየው ሲያውቅ ይሆን ወይ የእውነት ደስ ብዬው አንድ እለት ግቢ በር ላይ ቆሜ ከቦርሳዬ መታወቂያ ፍለጋ ሳምስ<<የኔ ባሪያ>> ብሎኝ ገባ። ያን ለት በቤተስኪያን ደጆች ሳልፍ ሸብረክ የማይለው ጉልበቴ ሙሉ ቀን ከዳኝ። ብዙ የውበት አድናቂ አልነበርኩም ስኖር እንደሰማሁት ወንድ ልጅ ከጉማሬ መለስ ካለ የሚል ድግግሞሼን ያነገብኩ ነብርኩ። አንዱ ነገር ሲያምረኝ ሌላ የምጥልለት ብዙ መልክ አውቃለሁ። እንደእሱ ግን ምንም የማላወጣለት ሰው ማንንም አላውቅም። ቆንጆ ሲባል፤እንኳን ወንዱን ሴቷንም በእሱ ውበት ማንፀር ጀመርኩ። OCR ፊት ለፊት ፀሀይ ያጋለው ድንጋይ ላይ ከጓደኞቼ ጋር ስኮለኮል የሚሉትን መሳት፤ከአጀንዳቸው መራቅ ጀመርኩ። ስለእሱ አስባለሁ .... አንዳንዴም ስለሁለታችን፤ ስንተቃቀፍ፣ የምወደውን ቀለም ሲጠይቀኝ፣ አልጄሪያን ጥብስ ፍርፍር ሲያጎርሰኝ ሂሂ.. ከምናቤ ስባንን ግን በቀኝ ሲመጣ በቀኝ invisible gawn ለብሼ የምጠፋ ነበርኩ።
he was like a movie... a quantin tarentino movie .. that uma thurman and jhon travolta dancing scene ..He was that guy from adele's song "when we were young" and every actor in the movie that blows up a car and walks away in slow motion. . Every A- list celebrity from the
cover of vog megazine, He is that guy in every movie every women leaves her lawfull husband for, a hybrid of idris elba and michael ealy. He is a trap, a test, a temptation , you will never pass. And i fall for him over and over and over and over again.
-
It was at a party
ሳቅ፣ ስካር፣ ነፃነት ፣ ሀላፊነት የሌለው ደስታ፣ እና ጅምር ወጣትነት የሞላው ፓርቲ ...የሲጋራ ጢስ ያፈነው እዚህም እዛም የሚተዋወቁ ከዚህ ሲወጡ unprotected sex ሊደራረጉ የሚፈልጉ ፊቶች። በጆኒ አበሻዊ የሚወዘወዙ ጠያይም ፊቶች፣በጀንትልማን it is happening again ዳሌያቸውን የሚያዘልሉ ውብ ሴቶች ... አረንጓዴ ሜንት ጂን፣ የጓደኛዬ ሽኔል ሽቶ እና የእሱ stare የሞላበት ምሽት...<<አሁን ቢመጣ ምንድነው የምለው?፣ ምንድነው የምለው?፣ ምንድን ነው የምለው?፣ ምንድነው የምለው?፣ ምንድን ነው የምለው?፣ ምንድን ነው የምለው>>.. እያልኩ መልሱን ሳላገኝ መጥቶ በረጅም ቁመቱ የቤቱን ጭላንጭል ብርሃን ጋርዶ እጁን ለዳንስ ዘረጋልኝ...እየተርበተበትኩ በጓደኞቼ የድጋፍ ሳቅ ተነሳሁ... የትግስት በቀለ ና የኔ ገላ ጀመረ... እጆቹን ወገቤ ላይ አድርጎ ወደእሱ አስጠጋኝ፣ ከቁመቱ ቀንሶ ሸብረክ ስላለልኝ ለሚያምር ፊቱ
ቀረብ ብያለሁ። አይምሮዬ ውስጥ ከማውቃቸው ፊቶች ጋር አነፃፅሬ ይበልጥ የመሰለኝን አንስቼ በቀስታ <<ሲያምረኝን ትመስላለህ>> አልኩት
ወደጆሮዬ ተጠግቶ ሶስት ፊደሎችን በማይገባቸው ከባድ ትንፋሽ ጠቅልሎ ተነፈሰልኝ
<<ታድሎ!>>ሊያጨስ እጅ ለእጅ ተያይዘን ደጅ ወጣን... መንገዱ ያምር ነበር ... ጭር ያለ ...የመንገድ መብራቶቹ ብርቱካንማ ደብዛዛ ብርሃን እየተፉ ቆመው ኑ አንዳች ታሪክ ስሩብን በሚል ጭንቅላታቸውን ያዘነበሉ ይመስላሉ። ወገቤን ይዞ ወደ ራሱ አስጠጋኝ በሁለቱ እጆቹ ፊቴን አቅፎ በሚያምሩት ግን ሰስቼ ባልነገርኳችሁ ከንፈሮቹ ትንፋሽ እስኪያጥረኝ ጉርስ ሳም
አደረገኝ። ሰፊ ትከሻው ውስጥ ሰረግኩ ሰመጥኩ።
-
እንዴት አለቀ? እኔንጃ.. it was a slip,not a walk... it was one step back not break up , it was never good bye, It was i ll see you.
-
<<ራስሽ ላይ መመሰጥ ጀመርሽ?>> ያችን ፈገግታውን ከርጋታ እና ከበላይነት ስሜት ጋር ብልጭ እያደረጋት ...መኪናዎቹን እንደተሻገርኳቸው አይነት አሯሯጥ ሮጬ ላመልጠው ፈለግኩ...He is that ሽቦ that says ዴንጀር የሀብታም አጥር ላይ... he was a caution for a wet floor፣ he was that ጦር in a heart but not from cubid. He is a story that has to begin with <> run baby girl, run፨

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Bez brown
991 viewsDAVE / PAPI, 19:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-17 10:20:43 @wegoch
@wegoch
@wegoch

አቅራቢ፡ ናርዶስ
ፀሃፊ፡ ህይወት እምሻው
527 viewsDAVE / PAPI, 07:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-17 09:13:37 #የሐኪም_ቤቱ_መስኮት

ሁለት ሰዎች በአንድ ሆስፒታል ክፍል ውስጥ አልጋ ይዘው ተኝተዋል። ሁለቱም በጠና ታመው በአምላክ እጅ ተይዘዋል። አንደኛው ሳንባው የቋጠረውን ውሀ ለማድረቅ ሲባል ለሰአታት ያህል አልጋው ላይ ቁጭ እንዲል ይደረጋል። አልጋው የሚገኘው በክፍሉ ብቸኛ ከሆነው መስኮት አጠገብ ነው።

ሌላኛው ህመምተኛ ደግሞ በተቃራኒው ለሰአታት በጀርባው እንዲተኛ ይደረጋል። እነዚህ ህሙማን በቆይታቸው ብዙ ተጨዋውተዋል። ስለ ቤተሰቦቻቸው ፣ ስለ ኑሯቸው፣ በወታደር ቤት ስለሰጡት አገልግሎት፣ የእረፍት ጊዜያቸውን የት እንደሚያሳልፉ... ወዘተ አውርተዋል።

ከመስኮት አጠገብ ያለው ህመምተኛ ቁጭ በሚልበት ሰአት ወደ ውጭ እየተመለከተ ሁሉን ነገር በጀርባ ለተኛው ሰው ይገልጽለታል።

".....በሚያማምሩ ዛፎች የተከበበ ሀይቅ ይታየኛል፣... በሀይቁ ላይ ዳኪዬዎች ይዋኛሉ...... ህጻናት ደግሞ ከወረቀት የሰሩትን መርከቦች በሀይቁ ዳርቻ በማስቀመጥ ይጫወታሉ... ፍቅረኛሞች በአንድ እጆቻቸው አበባ በሌላው ደግሞ ተቃቅፈው ሀይቁን ይዞራሉ፣... ከሀይቁ ባሻገር ውብ የሆነ ከተማ ይታየኛል....." በማለት ዘወትር የሚያየውን ሁሉ ይተርክለታል።

በዚህ አይነት ሁኔታ ሳምንታት አለፉ።

አንድ ማለዳ ነርስዋ ገላቸውን ልታጥብ ውሀ ይዛ መጣች። ከመስኮት አጠገብ ያለው በሽተኛ ግን በህይወት አልነበረም። በጣም ደነገጠች። ጓደኛውም እንዲሁ አዘነ። ነርስዋ አስከሬኑን በቶሎ እንዲያነሱ ሰዎች ጠራች። ያ ብቻውን የቀረው በሽተኛ አልጋውን ከመስኮቱ አጠገብ ሊወስዱለት ይችሉ እንደሆነ ጠየቀ። ወሰዱለት። በመስኮት ለማየት በጣም ቸኩሏል። ቀና ብሎ ወደ ውጭ ተመለከተ። ከመስኮቱ ባሻገር ያለው ነጭ ቀለም የተቀባ ግድግዳ ብቻ ነው።

ደነገጠ!!!

"ምን ሆንክ?" አለቸው ነርስዋ። "ሰዉዬው ብዙ አስደሳች
ነገሮችን በዚህ መስኮት አሻግሮ ይመለከት ነበር" አላት። "ኧረ ሰዉዬው ማየት የማይችል አይነስውር ነበር አለችው።" ልብ የሚነካ ነገር.... ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ።

ለካስ እሱን ለማስደሰትና የመኖር ተስፋ ለመስጠት ነበር ያን ሁሉ ነገር ፈጥሮ የሚያወራው።
====================================
አንዳንድ ሠዎች እንዲህ ናቸው እነሡ እየሞቱ የሠውን የሕይወት ብርሃን ያለመልማሉ። የሠው ህይወት ማዳን ባንችል እንኳን ቢያንስ ለሠው ተስፋ እንስጥ ይሄም የመልካምነት አንዱ ገፅ ነውና።

ከእግረኛ ወጎች ላይ የተወሰደ

@wegoch
@wegoch
@paappii
746 viewsDAVE / PAPI, 06:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-14 20:40:21 አዞዎቹ (The Crocodiles) እና የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ
-----
ክፍል ሶስት
-----
ከላይ እንደጠቀስኩት በያኔው የተማሪ ንቅናቄ ግንባር ቀደም መሪዎችና ሌሎች የንቅናቄው ተሳታፊዎች ላይ ከሚቀርቡት ክሶች መካከል አንዳንዶቹ መሠረተ ቢስ ናቸው። አንዳንዶቹ ከመሠረተ ቢስነታቸው ባሻገር ጨዋነት የጎደላቸው ናቸው። ከነዚህ ክሶች አንዱ ተማሪዎቹን የሲ.አይ.ኤ እና የሌሎች የውጭ ሃይሎች ቅጥረኛ አድርጎ ማቅረብ ነው። በዚህ ክስ የሚታወቁ ሰዎች በዚህ ብቻ ሳያበቁ ተማሪዎቹ እርስ በራሳቸው በሴራ ተጠላልፈው ይገዳደሉ እንደነበሩ ሲጽፉ ታይተዋል። ለምሳሌ አንዱ ፕሮፌሰር "ተስፋዬ ደበሳይ እንዲገደል ሁኔታዎችን ያመቻቸው ጓደኛው የነበረው ክፍሉ ታደሰ ነው" በማለት ጽፈው ነበር። ይሁንና በጽሑፉ ውስጥ ስማቸው እንደ መረጃ ምንጭ የተጠቀሰው ዶክተር ነገደ ጎበዜ ፕሮፌሰሩ የጻፉት ታሪክ ሐሰት ነው ብለው በማስተባበል የተስፋዬ ደበሳይ አሟሟት ኢህአፓዎች ከጻፉት የተለየ እንዳልሆነ መስክረዋል።

በሌላ በኩል የያኔው ዘመን የተማሪ ንቅናቄ መሪዎች የኤርትራ የነፃነት ድርጅቶች ቅጥረኞች መሆናቸውን የሚጽፉ ሰዎች በዝተዋል። ዛሬም እንደዚህ እየተባለ ሲጻፍ እያነበብን ነው። እነዚህ ሰዎች ለክሳቸው እንደ ማስረጃ ከሚያቀርቡት ሰበቦች ዋነኛው የአዞዎቹ ቡድን አባላት ከሆኑት ተማሪዎች መካከል አንዳንዶቹ የትግራይ እና የኤርትራ ተወላጆች መሆናቸው ነው።

ይህ ግልጽ የወጣ ዘረኝነት እንጂ አሳማኝ ምክንያት ሊሆን አይችልም። ለምሳሌ የኢህአፓዎቹ ዘርዑ ክሕሸን፣ ተስፋዬ ደበሳይ፣ ብርሀነ እያሱ፣ ጸሎተ ህዝቅያስ፣ ዮሴፍ አዳነ ወዘተ የትግራይ ተወላጅ ቢሆኑም ከሌሎቹ የኢህአፓ አባላት በተለየ ሁኔታ ለኤርትራም ሆነ ለትግራይ የሰሩት ነገር የለም። የኢህአፓ አባላት በእነዚህ መሪዎቻቸው ላይ አሁን የምንሰማውን ክስ ያቀረቡበት ወቅት የለም። በአንጻሩ ግን ህወሓት በ1969 መጨረሻ በኢህአፓ ላይ ጦርነት ሲያውጅ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ብዙ የኢህአፓ አባላት ግንባር ቀደም ሆነው የህወሓትን ጦር ተፋልመዋል። ህወሓት ደርግን አሸንፎ ሲመጣም እነዚያ የትግራይና የኤርትራ ተወላጆች ህወሓትን መቃወማቸውን ቀጥለዋል። ሰዎችን በብሄር ብቻ እየፈረጁ ባልሰሩት ነገር መውቀስ ከዘመናችን ታላላቅ በሽታዎች አንዱ ነው። ሁሉም ለዚህ በሽታ መፍትሔ መፈለግ አለበት።
*
አነሳሴ የአዞዎቹን ቡድን በመጠኑ ማስተዋወቅ ቢሆንም ሌላውንም ቀላቅዬ በሰፊው አቅርቤላችኋለሁ። አሁን ወደ መነሻዬ ልመለስና ጽሑፌን ላብቃ።

"አዞዎቹ" በዚህ ዘመን በአብዛኛው በህይወት የሉም-ከላይ እንደጠቀስኩት፡፡ ብዙዎቹ የሞቱት በአብዮቱ አፍላ ወቅት ነበር፡፡ አንዳንዶቹ በወታደራዊው የደርግ መንግሥት ተይዘው ነው የተረሸኑት፡፡ ከፊሎቹ ደግሞ ከደርግ አሳሾች ሲሸሹ ነው የተገደሉት፡፡ ጥላሁን ግዛውና ዋለልኝ መኮንንን የመሳሰሉት ግን ቀደም ብለው በአጼ ኃይለ ሥላሤ መንግሥት ወታደሮች ተገድለዋል፡፡ አንዳንዶች በዚያው ዘመን ዱር ገብተው ሲዋጉ ህይወታቸው አልፏል፡፡ እንደ ዶ/ር እሸቱ ጮሌ፣ ዘሩ ክሕሸን እና አብዱል መጂድ ሑሴንን የመሳሰሉት በህመም ምክንያት ሞተዋል፡፡ በዚህ ዘመን በህይወት መኖራቸው የሚታወቀው የአዞዎቹ ቡድን መሥራች አባላት

1. ገብሩ ገብረወልድ (በአሜሪካ ሀገር የሚኖሩ)
2. አበራ ዋቅጅራ (አሜሪካ የሚኖሩ)
3. ኢያሱ ዓለማየሁ (ፈረንሳይ ሀገር የሚኖሩ)
4. አብዲሳ አያና (አውሮጳ የሚኖሩ) የመሳሰሉት ናቸው።
*
አፈንዲ ሙተቂ
መጀመሪያ ታህሳስ 2/2006
እንደገና ተሻሽሎ ታሕሳስ 3/2014 ተጻፈ።

(እንደ ማስታወሻ፡ እነ ኃይሌ ፊዳ፣ ተስፋዬ ደበሳይ፣ ሰናይ ልኬ፣ ነገደ ጎበዘ፣ ክፍሉ ታደሰ፣ ክፍሉ ተፈራ የመሳሰሉት አብዮተኞች የአዞዎቹ ቡድን አባላት አልነበሩም፡፡ እነዚህኛዎቹ ትምህርታቸውን በውጪ በሚከታተሉበት ወቅት ነው ወደ ንቅናቄው የገቡት)፡፡

@wegoch
@wegoch
@paappii
739 viewsDAVE / PAPI, 17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-14 20:29:34 አዞዎቹ (The Crocodiles) እና የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ
-----
ክፍል ሁለት
-----
ጸሐፊ: አፈንዲ ሙተቂ
----
በሌላ በኩል የአዞዎቹ ቡድን ጀማሪ አባላትም ሆኑ ብዙኃኑ የዚያ ዘመን ተማሪዎች በኃይለ ስላሴ እና በደርግ መንግሥት የጸጥታ ሃይሎች እጅ በሚወድቁበት ጊዜ ብዙ የጭካኔ ድርጊቶች ተፈጽመውባቸው እንኳ ሚስጢር አያወጡም ነበር። የደርግ የጸጥታ ሃይሎች በተማሪው እንቅስቃሴ የተወለደው "ኢህአፓ" የተሰኘው ድብቅ ፓርቲ አባላት ሚስጢር የማያወጡና ለዓላማቸው የሚሞቱ ቆራጦች ስለሆኑባቸው ነው ከፍተኛ ጭካኔ የተቀላቀለበትን የቀይ ሽብር ዘመቻ የጀመሩት (ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም የኢህአፓዎቹን ቆራጥነት በትዝታ መጽሐፋቸው በግልጽ አድንቀውላቸዋል)።

በሁለተኛ ደረጃ የአዞዎቹ ቡድንም ሆነ ሌሎች የተማሪዎች ንቅናቄ አባላት ለብዙ ዘመናት ህዝብን ቅር ሲያሰኙ እና ለአመጽ ሲያነሳሱ የነበሩ መሠረታዊ ችግሮችን በክህደት የማያድበሰብሱ በመሆናቸው ይታወቃሉ። የንቅናቄው ተሳታፊ ተማሪዎቹ ግፋ ቢል የሚያደርጉት ነገር ጥያቄዎቹን በሶሻሊስታዊ ዐይን እያዩ መተንተን እና ከሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ጋር አመዛዝኖ መልስ ለመፈለግ ነው።

ለምሳሌ፣ የኤርትራ ጥያቄ፣ የብሄረሰቦች ጥያቄ እና የሀይማኖት እኩልነት ጥያቄ ከ1950-1960 ባለው ዘመን በተማረው ማህበረሰብ ዘንድ በሹክሹክታ መነሳት ጀምረው ነበር። ይሁንና የዚያ ዘመን ኢንተሊጀንሲያ ትምህርቱ በአብዛኛው ምዕራብ ቀመስ በመሆኑ በጥያቄዎቹ አመላለስ ላይ ከሃይለ ስላሴ መንግስት የተሻለ አቋም አልነበረውም። ብዙዎቹ "እነዚህ ችግሮች በተጨባጭ በሀገራችን የሉም፣ ቢኖሩም እንኳ መሠረታዊ አይደሉም" እያሉ ይክዱ ነበር።

"አዞዎቹ" የተሰኘው የግንባር ቀደም አብዮተኛ ተማሪዎች ቡድን ሲመጣ ግን እነዚህ ጥያቄዎች የተማረው የህብረተሰብ ክፍል ዋነኛ የውይይት ርእስ ሆነዋል። በተለይ ደግሞ "የብሄረሰቦች ጥያቄ" ከሁሉም በላይ ገንኖ በመውጣት የአብዛኛው ተማሪ የውይይት አጀንዳ ሆኖ ነበር። በመጨረሻም አዞዎቹ እና ሌሎች ብዙ ተማሪዎች የተስማሙበት አቋም በዝነኛው ዋለልኝ መኮንን ብዕር በጽሑፍ ተቀነባብሮ በመጽሔት ወጥቷል (ልብ በሉ! ዋለልኝ ጽሑፉን በራሱ ስም ቢያቀርበውም ከሌሎች ጓደኞቹ ጋር በሰፊው ተወያይቶ እና እነርሱንም ወክሎ ነው ጽሑፉን የጻፈው። ጽሑፉ በአዞዎቹ ቡድን ስም ቢቀርብ ኖሮ ቡድኑ ይጋለጥ ነበር)።

እዚህ ላይ አንድ ነገር ያዙልኝ። በአሁኑ ዘመን በርካታ ሰዎች "የብሄር ብሄረሰቦች ጥያቄ የሚባል ነበር አልነበረም። ወያኔ ለአገዛዝ እንዲመቸው የፈጠረው አርቲፊሻል ጥያቄ ነው" ይላሉ። ይህ አባባል መሠረት የለውም። ብሄሮች ለመብትና ነፃነት መታገላቸው ከወያኔ በፊትም ነበረ። ከተማሪዎች ንቅናቄ መጀመር በፊትም ጥያቄ ነበር።

የብሄረሰቦች ጥያቄን በጽሑፍ በማቀናበርና በመጽሔት በማሳተም ብዙዎች ስለጉዳዩ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ያደረጉት ደግሞ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ነበሩ። በኢትዮጵያ ታሪክ በተደራጀ መልክ የፖለቲካና የለውጥ ትግል የጀመሩት ቀደምት ፓርቲዎችና ቡድኖች በሙሉ (ኢብነግ፣ ኢህአፓ፣ መኢሶን፣ ኦነግ፣ ግገሓት፣ ህወሓት፣ ሶወሊ፣ ወዘተ) "የብሄረሰቦች መብት መከበር አለበት" ይሉ ነበር። እነዚህ ድርጅቶች በዕድሜአቸው ከወያኔ ይቀድማሉ። ጥያቄውን ያነሱት በሀገሪቱ ውስጥ ያለውን እውነታ ተንተርሰው ነው።

በጥያቄው አመላለስ ላይ መነጋገርና ሁሉንም የሚያስማማ መልስ መፈለግ ይቻላል። "ጥያቄውን ያመጣው ህወሓት ነው" ማለት ግን ታሪክንና ነባራዊ እውነታን መካድ ነው።
-------
በአዞዎቹ እና በሌሎች የተማሪው ንቅናቄ አባላት ላይ ብዙ ትችቶች ይቀርብባቸል። ከትችቶቹ መካከል አንዳንዶቹ ተገቢ ናቸው። ሌሎቹ ግን ከእውነት የራቁ ናቸው።

ለምሳሌ አዞዎቹም ሆኑ የግራ መስመር ተከታይ የሆኑ የዚያ ዘመን ተማሪዎች በሙሉ በአመለካከት መለያየትን እንደ መብት አይቀበሉትም። በአመለካከት የተለዩትን ሰው በጠላትነት በመፈረጅ በፕሮፓጋንዳ ሽብር ያጨናንቁታል። በመጽሔት ብዙ ይጽፉበታል። ከማህበራዊ ኑሮ ያገልሉታል። ይህ ባህሪያቸው ስር እየሰደደ ሄዶ በ1968-1970 የታየውን ከባድ ትራጀዲ ወልዷል። በአውሮጳ ጓደኛሞች የነበሩት ሃይሌ ፊዳ እና ተስፋዬ ደበሳይ ወደ ሀገር ቤት ከተመለሱ በኋላ ደመኛ ጠላቶች ሆነዋል (እርግጥ ሁለቱም የአዞዎቹ መስራች አባላት አልነበሩም። ሆኖም ጓደኞቻቸው የአዞዎቹ ቡድን አባላት ነበሩ)። የመኢሶን አባል የነበረችው ዶ/ር ንግሥት አዳነ ከአንድ ማህጸን ከእርሷ ጋር የተወለደውን ዮሴፍ አዳነ የተባለ ወንድሟን ከቢሮው አስይዛው እንዲገደል አድርጋለች። የመኢሶኑ ግርማ ከበደም ነፍስ ጡር የነበረችውን ወይዘሮ ዳሮ ነጋሽን ከአስራ ስድስት ሰዎች ጋር አስገድሎ ሬሳቸው በራስ መኮንን ድልድይ ላይ እንዲጣል አድርጓል። ኢህአፓዎች በበኩላቸው የመኢሶን መሥራች አባል የነበረውን ዶ/ር ፍቅሬ መርእድን በጠራራ ጸሐይ "ባንዳ" በማለት ገድለውታል። ሸዋሉል መንግሥቱ የተባለችው ታዋቂ ገጣሚና ጋዜጠኛም የቀበሌ ሊቀመንበር ሆና ስለተመረጠች ብቻ "ባንዳ" ተብላ በኢህአፓ ስኳድ ተገድላለች (ኢህአፓዎች "ሸዋሉል ገዳይ ጓድ እየመራች ብዙ ወጣቶችን ስለረሸነች ነው የተመታችው" እያሉ ቢጽፉም ይህንን የሚያረጋግጥ ማስረጃ አልተገኘም)። ከዚህ እልፍ ሲልም የኢህአፓ መሥራችና የመጀመሪያ ዋና ጸሐፊ የነበረው ብርሃነ መስቀል ረዳ ከጓዶቹ ጋር በሃሳብ ባለመጣጣሙ ምክንያት ከድርጅቱ ሲወጣ ራሱ የመሠረተው ድርጅት ሞት ፈርዶበታል። እርሱም "የእርማት ንቅናቄ" የተሰኘ የኢህአፓ አንጃ በመፍጠር በሌሎች ጓዶቹ ላይ ሞት ፈርዷል (ሆኖም እነርሱ ሳይገዳደሉ ደርግ ቀደማቸውና ሁሉንም ሰብስቦ ረሸናቸው)።

የዚያ ዘመን የተማሪ ንቅናቄ አባላት ሌላው ችግራቸው በሁሉም ረገድ የሚያሳዩት ችኮላ እና አለመስከን ነው። ብዙዎቹ ከሰላሳ ዓመት ያልበለጡ ወጣቶች በመሆናቸው ለመደመጥ እንጂ ለማዳመጥ ዝግጁ አልነበሩም። ከላይ እንደተገለጸውም በሃሳብ የማይጣጣሙትን ሰው "ባንዳ" ፣ "ትሮትስካይት" ፣ "አናርኪስት"፣ "ቀኝ መንገደኛ" እያሉ በጠላትነት ይፈርጁታል። ዛሬ የምናየው በችኮላ የመፈረጅና ቅጽል እየሰጡ የማጥላላት አድራጎት ከዚያ ዘመን የተወረሰ መጥፎ ልማድ ነው።

@wegoch
@wegoch
@paappii
774 viewsDAVE / PAPI, 17:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-13 21:52:49 አዞዎቹ (The Crocodiles) እና የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ
--------
ክፍል አንድ
------
ጸሐፊ: አፈንዲ ሙተቂ
---------
በቅርቡ ታሪካቸውን የለጠፍኩላችሁ ዋለልኝ መኮንን እና ማርታ መብራህቱን የመሳሰሉ ፋኖችን የወለደው ታሪካዊው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ነበር። ያ ንቅናቄ አጨራረሱ ላይ ተደነባብሮ የተነሳለትን ዓላማ ሙሉ በሙሉ ከታሪክ መድረክ ላይ ቢወርድም በአጀማመሩ ላይ የብዙዎችን አድናቆት አትርፏል። በዚያ ንቅናቄ የተሳተፈው ትውልድ በቆራጥነቱ፣ በአብዮታዊነቱ፣ በህዝባዊነቱ፣ በተራማጅነቱ፣ በአንባቢነቱ፣ በቀስቃሽነቱ ብዙ የተባለለት ነበር።

የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ሲጀመር አንድ ወጥ መልክ ነበረው። በሂደት ግን የግራ መስመር ተከታዮች የሚበዙበት ክንፍ ከሌሎቹ የበለጠ በመንቀሳቀስ የንቅናቄው አቀጣጣይ ለመሆን በቅቷል። እነዚያን የግራ ርእዮት አቀንቃኞች በስውር ሲመራ የነበረው ደግሞ “አዞዎቹ” የሚባለው የስር-ነቀል ለውጥ (radical change) ደጋፊ የተማሪዎች ቡድን እንደነበር ሰነዶችና የንቅናቄው ተሳታፊዎች ይጠቁማሉ፡፡

የ“አዞዎቹ” ቡድን ምስረታ የተጠነሰሰው ገብሩ ገብረ ወልድ በሚባለው የያኔው የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤ ዩኒቨርሲቲ (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) ተማሪ ነበር፡፡ ዘመኑም በ1955 ገደማ ነው፡፡ ገብሩ ገብረወልድ ቀደም ባለው ዘመኑ የዓለም-ማያ (ሀረማያ) እርሻ ኮሌጅ ተማሪ ነበር፡፡ ዘርዑ ክሕሸን የሚባለው ተማሪም ከርሱ ጋር ይማር ነበር፡፡ ሁለቱ ተማሪዎች በ1954 ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተዛወሩ፡፡ ከዓመት በኋላም በገብሩ ጠንሳሽነትና በዘርዑ ተባባሪነት ማርክሳዊ ርዕዮት የሚያጠኑበትን ቡድን መሰረቱ፡፡ ከነርሱ ጋር ተቀራራቢ ሀሳብ የነበራቸውን ሌሎች ተማሪዎችንም መሳብ ጀመሩ፡፡ በዚህ መሰረት የቡድኑ ቀዳሚ አባላት የሆኑት

1. ኃይሉ ገብረ ዮሐንስ (ገሞራው)
2. ስዩም ወልደዮሐንስ
3. አበራ ዋቅጅራ
4. ዮሐንስ ስብሐቱ ናቸው፡፡

በማስከተልም የነርሱን ዓላማ የሚደግፉ በርከት ያሉ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲገቡ የአዞዎቹ ቡድን መሰረቱን ማስፋት ጀመረ፡፡ በ1956 የተማሪ ማህበር አመራር አባላት የነበሩት ብርሃነ መስቀል ረዳ እና እሸቱ ጮሌ ከቡድኑ ጋር ተቀላቀሉ፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላም ሚካኤል አበበ፣ ታዬ ጉርሙ እና ሐብቴ ወልደ ጊዮርጊስ የአዞዎቹ ቡድን አባል ሆኑ፡፡
*
የአዞዎቹ ቡድን ጅምሩ ላይ የጥቂቶች ስብስብ ነበር፡፡ እያደር ግን ስር-ነቀል ለውጥ ደጋፊ የሆነ ተማሪ ሁሉ የሚሰባሰብት የጋራ ማህበር ሆኗል፡፡ ምንም እንኳ ቡድኑ ከ1960ዎቹ መግቢያ ጀምሮ “አዞዎቹ” በሚለው ስም መጠቀሙን ቢያስቀረውም በአዞዎቹ የተዘረጋው የስር-ነቀል ለውጥ ደጋፊ አብዮተኛ ተማሪዎች መስመር እስከ 1966ቱ አብዮት ድረስ ቆይቷል፡፡ በዚህ መሰረት ከ1950ቹ መጨረሻ ጀምሮ የአዞዎቹ መስመር ተከታይ በመሆን በንቅናቄው ውስጥ ከፍተኛ ሚና ከነበራቸው አብዮተኛ ተማሪዎች መካከል የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡

1. ዋለልኝ መኮንን
2. ጥላሁን ግዛው
3. ጸጋዬ ገብረ-መድህን (ደብተራው)
4. ገዛኽኝ መኮንን
5. ተካልኝ ወልደ አማኑኤል
6. ጌታቸው ሀብቴ
7. ታምራት ከበደ
8. ሄኖክ ክፍሌ
9. ዳዊት ስዩም
10. ጸሎተ ህዝቅያስ
11. ሙሐመድ ማሕፉዝ
12. በድሩ ሱልጣን
13. ዳዊት ህሩይ
14. ተስፉ ኪዳኔ
15. ዮሐንስ በፍቃዱ
16. አማኑኤል ዮሐንስ
17. ሙሉጌታ ስልጣን
18. መስፍን ሐብቱ
19. አያሌው አክሎግ
20. ጌታቸው ሻረው
21. ፋንታሁን ጥሩነህ
22. ይርጋ ተሰማ
23. አባይ አብርሃ
24. መስፍን ካሱ
25. ዮሐንስ ብርሃኔ
26. ብርሀነ ኢያሱ
27. ወርቁ ገበየሁ
28. እሸቱ አራርሶ
29. ኢያሱ ዓለማየሁ
30. ብንያም አዳነ
31. ገዛኽኝ እንዳለ
32. ዮሴፍ አዳነ
33. አብዱል መጂድ ሁሴን
34. አብዲሳ አያና
35. ሀይለእየሱስ ወልደሰንበት
36. ማርታ መብራህቱ
37. ታደለች ኪዳነ ማሪያም
38. ተስፋዬ ቢረጋ
39. ገብሩ መርሻ
40. ታሪኩ ደብረ ጽዮን
41. ግርማቸው ለማ
42. ጌታቸው ማሩ
43. መለስ ተክሌ
44. ግደይ ገብረዋህድ
45. ረዘነ ታደሰ
46. አሰፋ እንደሻው
47. ሳሙኤል አለማየሁ
48. መላኩ ማርቆስ
49. ወርቁ ገበየሁ
50. ብርሃኑ እጅጉ
------
ከላይ በቀረበው ዝርዝር ውስጥ የተጠቀሱት በሙሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ነበሩ፡፡ እነዚህ ተማሪዎች በህቡዕ የሚንቀሳቀሰውና በ1960ዎቹ መጀመሪያ መሠረቱን እያሰፋ የመጣው የአዞዎቹ ቡድን ቀጥተኛ አባላት ናቸው። የአዞዎቹ ቡድን አባል የሆነ ሰው ማንነቱን በግልጽ ሳያስታውቅ ሌሎች ተማሪዎችና ምሁራን የትግሉ ደጋፊ እንዲሆኑ ይቀሰቅሳቸዋል። ሰልፍና አድማ በሚኖርበት ወቅት ግንባር ቀደም ሆኖ ያስተባብራል። የንቅናቄው አባል የሆነ ተማሪ ከትምህርት ጉዳይ በስተቀር በሌሎች ጉዳዮች ላይ አድሃሪ አቋም ካላቸው ተማሪዎች ጋር ጉድኝት አይፈጥርም።

ከ1962 በፊት በነበረው ጊዜ የተማሪዎቹ ዋነኛ የትግል ስልት በተቃውሞ ሰልፍና በህትመት መድረኮች ንጉሣዊውን ስርዓቱን ማስጨነቅ ነበር፡፡ ከዚህም ጎን ህዝቡንና አብዮታዊ ምሁራንንም በተቃውሞው ጎራ ለማሰለፍ ጥረት ያደርጉ ነበር፡፡ ከ1962 በኋላ ግን የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ይህንን ስልት እርግፍ አድርገው በመተው ልዩ ልዩ የውይይት ክበቦችን እየመሰረቱ በሶሻሊስት ርዕዮተ-ዓለም እና በድርጅት ምስረታ ላይ ጥልቅ ውይይት ማድረግ ጀመሩ። አንዳንድ ተማሪዎች ደግሞ ከስርዓቱ ክትትል ለማምለጥ ከሀገር ተሰደዱ፡፡ በሀገር ውስጥ የቀሩት ተማሪዎች በውጪ ሀገር ካሉት የተማሪ ማህበር አባላትና ስደተኛ ተማሪዎች ጋር በመቀናጀት የስርዓት ለውጥ የሚመጣበትን መንገድ ለመሻት ተንቀሳቀሱ፡፡ በስተመጨረሻም በልዩ ልዩ የፖለቲካ ድርጅቶች (ኢህአፓ፣ መኢሶን፣ ኦነግ፣ ህወሓት፣ ጀብሃ፣ ሻዕቢያ፣ ወዝሊግ ወዘተ....) ስር በመሰለፍ ታገሉ፡፡ ይሁንና በጣም የሚበዙት ያሰቡትን ከግብ ሳያደርሱ ከዚህች ዓለም ተሰናበቱ፡፡
------
እዚህ ዘንድ ሁለት ነገሮችን መጨመር ተገቢ ይመስለኛል። የአዞዎቹ ቡድን ጀማሪ አባላትም ሆኑ ሌሎቹ የዚያ ዘመን የተማሪ ንቅናቄ ተሳታፊዎች በቆራጥነታቸው የተነገረላቸው ናቸው። ለምሳሌ አንድ ተማሪ ከመኳንንትና መሳፍንት ቤተሰብ የተወለደ ሆኖ የመደብ ጀርባው ሳያግደው ለገበሬው ሲል "መሬት ላራሹ" እያለ ይጮኽ ነበር። አባቱ ጄኔራል ሆኖ በቅንጦት መኖር እየቻለ ለትግል ሲል አባቱንም ከንጉሣዊው ስርዓት ጋር የህዝብ ጠላት አድርጎ ይፈርጅ ነበር። ከወንድሙ ጋር በዓላማ የማይጣጣም ከሆነም ከወንድሙ ይልቅ ትግሉን ያስቀድም ነበር። አንዳንድ ተማሪዎች ደግሞ በትግሉ ሳቢያ እየታሰሩ ሲፈቱ ከመቆየታቸው የተነሳ ትምህርታቸውን እርግፍ አድርገው በመተው የሙሉ ጊዜ አብዮተኛ ታጋይ ሆነዋል።

@wegoch
@wegoch
@paappii
671 viewsDAVE / PAPI, 18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-13 10:12:27 ትልቅ ሰው ሁሌም ትልቅ ነው!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
ያደኩባት ከተማ ውስጥ እጅግ ትታወቅ የነበረች ጠጅ ቤት ነበረች።
አቤት ያቺ ጠጅ ቤት ስራ የጀመረች ጊዜ መቼም ዓለም ነበር !...ከሩቅ ሰፈር ድረስ የመጡ እንግዶች ጠባቧን ቤት ይሞሏታል።
ከቤቷ የተትረፈረፉ አርፋጆችም ግቢ ውስጥ የሚገኝ ጥላ ይመርጡና ቁጭ ብለው ይሸርባሉ :)
በረከታሙ ግቢ የውጭውን በር አለፍ ብለው ወደ ውስጥ ሲዘልቁ ጀምሮ መዓዛው ያውዳል። እኔ ልጅ ሆኜ ብዙ ጊዜ እዛ ቤት ስላክ ደስ ይለኝ ነበር። አባዬ ከጓደኞቹ ጋር ቁጭ ብሎ አንድ ሁለት ብርሌውን ሲልፍ ጊዜ ተካፋች የሞባይል ስልኩን ያነሳና ይደውላል።
ሄሎ.. . (እናቴ ስልኩን ታነሳዋለች)
እናቴ.. . (አባዬ እናቴን የሚጠራት እንደዚህ ብሎ ነው )
እሺ.. . ቤት አይመጣም?
(ጋሼ ምን እንደሚላት እንጃ ፈገግ ትላለች)
እሺ.. .
አዎ ...አለች ያቺኛዋ ጄሪካን...
እህ?
እሺ.. .እሺ.. .
እሺ በቃ ይመጣል ።...አንተም ደግሞ ፊት አገኘሁ ብለህ አታምሽ
.
ሚኪ ... (እማዬ ትጣራለች)
በርሬ ስሯ እደርሳለሁ ። ... ወደ ጓዳ ገብታ አምስት ሊትር ጄሪካን ይዛ ትመጣና ክዳኑን ከበላይ ጥላ የምትዘጋበት ስስ ፌስታል እየፈለገች.. ..
'ሂድ አባትህ ... እከሊት ጠጅ ቤት ና ብሎሀል ። ' ትለኛለች።
መቋጠሪያ ላስቲኩንና ቢጫውን ጄሪካን ተቀብያት እከንፋለሁ።
የጠጅ ቤቷ በር ጋ ስደርስ የሰው አይን ስለሚያስፈራኝ አንገቴን ሰብሬ እገባለሁ።
ጫጫታው.. .ጨዋታው ግን አንዳች መስህብ አለው። አጎንብሼም ግን ቆሎ ከሚያዞረው ልጅ ቁና ላይ መስረቄን አልተውም።
"አባት መጣህ ? ...ግባ ወደ ጓዳ " ይላል አባዬ።
"ማነሽ ...የሺ ! ዘሪሁን መቷል ...ብርዝ ስጭውና ይዞ ይሂድ "
የጠጅ ቤቷ ባለቤት መልከ መልካሟ የሺ ትመጣለች። ሳያት ደስ ትለኛለች...እንደ እቴጌ መነን ጀነን ያለ ኩራት አለባት። በዛ ላይ እኔን ትወደኛለች...ስትንከባከበኝ ደስ ይለኛል።
"መቼም አባትህ ካንተ ውጭ ወሬ የለውም !"
ትለኛለች። ...
"ትምህርት ደግሞ ሁለተኛ ወጣክ አይደል?"
"አዎ እትዬ! "
" ታድያ ትምህርት ሁለተኛ ወጣህ ብሎ ለምን ይቆጣካል?"
"አንደኛ የወጣው ልጅም እንዳንተ እንጀራ ነው የሚበላው.. . አንተ ከሱ ለምን አነስክ ብሎ ነዋ "
"ቂ....ቂ....ቂ....ክፍል ውስጥ ስንት ተማሪ አለ ?"
"80 ነን እትዬ"
"እና ሎሎች ሰባ ስምንቱ የጠላ ቂጣ ነው የሚበሉት? ሁሌም ተማሪ ታለ ውድድር አለ ...ውድድር ካለ ደግሞ አሸናፊም ተሸናፊም አለ። ደግሞ ከአንድ እስከ ሶስት መውጣት ሁሌም ጉብዝና ነው። ምነው የአባትህ ጓደኛ የአያ ቸሬ ልጅም አለ አይደል እንዴ? እያንዳንዱን ክፍል እንደ ውዳሴ ማርያም ሳይደጋግም አያልፍም እኮ! ቂ...ቂ...ቂ "
እትዬ የሺ ትስቃለች። ስትስቅ የድዷ ውቅራት ደስ ይላል። በጥቁር ድዷ ላይ ደግሞ ነጭ ሳይሆን የሆነ ነጣ ያለ ማኪያቶ የሚመስሉ ስድር ጥርሶች አሏት ።
ከደቂቃዎች በኋላ በትንሿ ብርጭቆ ብርዝ ትሰጠኛለች። ገዝቻች አይደለም...ግዴታዋም አይደለም...ስለ ፍቅሯ ብቻ!
ብርዙን ፉት ስለው ገና ከገነት ፍሬዎች አንዱን ቀጥፌ የመጠጥኩት ይመስለኛል።
ጥፍጥ.. ..
....
ህይወት በዛ ቤት እንደዚህ ውብ ሆና ለመቀጠል ግን ጥቂት ዓመታት ብቻ ነበሩ ደግ ሆነው የቆዩት ።
ከሆነ ጊዜ በኋላ እትዬ የሺ ስኳር መጠቀም ጀመረች አሉ። ከዛ ብዙ ብዙ እኔ የማይገቡኝ የትልቅ ሰው መከራዎች ደርሰውባት ከአካባቢው ዞር አለች። የጠጅ ቤቷ ዝና ወረደ ...እኛም ያደግንባትን ከተማ ለቀን ለዩንቨርስቲ ትምህርት ተሰደድን ።
የሆነ ጊዜ ደግሞ እንደዚህ ሆነ...
5 ዓመታትን በተለያየ ከተማ ተበታትነን የነበርን ጓደኞች ተገናኝተን የድሮዋን ታዋቂ ጠጅ ቤት ለመጎብኘት ሄድን። አዲሷ ቤት ደመ ቀዝቃዛ ናት። ድሮ እታለም ጠጅ ቤት ስሄድ የነበረው ሁካታና ግርግር የለም። ቅር አለኝ። እትዬም ስራውን ለሰው ለቃ ስለነበር ብዙ ጊዜ ሳሎኑን አትጎበኘውም።
ከልጆች ጋር ተሰብስበን አንድ ሁለት ካልን በኋላ እትዬ መጣች።
ፍቅሯ እንደ ድሮው አልነበረም። ጭራሽ ረስታኛለች.. .ደግሞ ጉስቁል ብላለች ።
ስታወራ ድምፅዋ ቅልስልስ አለ ...
እኔ ከጓደኞቼ ጋር ስጫወት ቆየሁ። በመሀል የሺ ትክ ብላ አየችንና ከመሀል አንዱን ጓደኛችንን አንተ የጋሽ ክፍሌ ልጅ ነህ አይደል? አለችው።
"አዎ እትዬ" አላት...ሀዘንና ቁጣዋ እስከ አሁኗ ደቂቃ ድረስ ፊቴ ላይ አለ።
"እናንተ ባለጌዎች አሁን እናንተም አድጋችሁ ጠጅ ለመጠጣት በቃችሁ ?" እትዬ.. .ጮኸች!
እትዬ አልገባትም እንጅ አድገን ስራ ሁሉ ይዘናል እኮ ። እንደውም አንዱ ጓደኛችን ሚስት ሊያገባ ስላሰበ ለሚዜነት ሊጀነጅነን ነበር እዛች ቤት የገባነው። የሺ ግን ልጅ ሆነን ስለምታውቀን አንጀቷ እንቢ አለ ።
ለሶስተኛ ጊዜ መጥታ ጠጅ ልትቀዳልን ያለችው ዓለም ላይ እትዬ ጮኸችባት።
"ውጡ " ...
"እንዴ እትዬ ሂሳብ አልከፈሉም እኮ" አለች ዓለም።
"የራስሽ ጉዳይ ...እነዚህ እኮ ልጆች ናቸው። አባቶቻቸው ነበሩኮ እኔ ጋር የሚመጡት.. .የዛሬን አትይ ..." እትዬ እንባዎቿ ወረዱ !
እኔ ግን እንዴት እንደሆነ ባላውቅም እትዬ የሺ አሁንም ድረስ እንደ ንጉስ ሀይለ ስላሴ ሚስት በኩራት ታየችኝ።
በዚህ ገንዘቤን እንጅ ስለ ትውልዱ ምናገባኝ የሚል ስግብግብ ነጋዴ በበዛበት ዓለም...18 ዓመት ላልሞላው ልጅ ጫት እና መጠጥ በሚሸጥበት ዓለም... እኔ ያገባኛል የሚል ነጋዴ...ለዛውም ከስሮ ችግር ላይ ያለ ነጋዴ ሲታይ እንዴት አይገርምም?
ሁላችንም ተግተልትለን መውጣት ጀመርን። እትዬ ብትናፍቀኝም...እንደ ረሳችኝ አውቄ ባፍርም የአባዬ ልጅ ነኝ ብዬ ብነግራት እጅግ የምትናደድ ስለመሰለኝ ዝም አልኳት።
የናፍቆት የናፍቆቴን በር ጋር ደርሼ ዞር ብዬ አየኋት። ነፍሷ ዛሬም ውብ ናት !
ትልቅ ሰው መቼም ትልቅ ሰው ነው

@wegoch
@wegoch
@paappii
1.5K viewsDAVE / PAPI, 07:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ