Get Mystery Box with random crypto!

ወግ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @wegoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.51K
የሰርጥ መግለጫ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @leul_mekonnen1

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 27

2022-02-10 22:38:39 የፍቅር ቀን ወይም የአደይ ቀን

'እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ የፍቅር ጀግና ለማድረግ በአገራችን ቫለንታይንስ ደይ እየተባለ የሚከበረውን የፈረንጆች በዓል ተውሰን እንደ አገራችን ፀባይ ለማክበር እቅድ አውጥተን ነበር፡፡

የጦር ጀግኖች ብቻ ሳይሆን የፍቅር ጀግኖች ያስፈልጉናል፡፡

ቫለንታይን ጥሩ ሃሳብ ነው፡፡ ክፋት የለበትም፡፡ ተቃቅፈው የሚሄዱ ፍቅረኞች ማየት ደስ ይላል፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘው በመንገድ የሚሄዱ ወጣቶች ትዕይንት የሚናፍቅ ነው፡፡ እኔ ወጣት በነበርኩበት ዘመን እንዲህ ማድረግ ያሳፍረን ነበር፡፡ ልጆቻችን በፍቅር እንዲያፍሩ አልፈልግም፡፡

ፍቅርን ከብልግና አምታተናል፡፡

ይሄን ቫለንታይን ቀን በዓል ኢትዮጵያዊ ለማድረግ ሦስት ነገሮች ማሟላት አስበን ነበር፡፡

አንደኛ፤ ከየትኛውም የአገራችን ክፍል አስገራሚ የፍቅር ታሪኮችን መሰብሰብና ለብሔራዊ በዓል የሚያገለግለንን ነቅሰን ማውጣት፤

ሁለተኛ፤ ምሳሌ የሚሆኑንን የአበባ አይነትና የአበባ ቀለም መምረጥ፤

ሦስተኛ፤ በታዋቂ ገጣሚ፤ ሙዚቀኛና ኮርዮግራፈር በአሉን የሚዘክር በቀላሉ አድማጭ ሊያንጎራጉረው የሚችል ዜማ መስራት ነበሩ፡፡

ከነዚህ ውስጥ ኮሚቴው ለብቻው የሚወስናቸው የበዓሉን ቀን፣ የአበባው ዓይነትና የአበባ ቀለም ሲሆኑ፣ የተቀሩት ዐላማዎች ግን በጥናትና በህብረት ውሳኔ ይፀድቃሉ፡፡

አገራችንን ከአደይ የበለጠ ምን አይነት አበባ ሊወክላት ይችላል? ከመስከረም ወር የበለጠ ምን የሚያምር ወር አለ? ቢጫ ቀለምስ ውብ አይደለም?

የአገራችን ስም ከተሰራባቸው ቀለማት አንዱ ዮጵ ትርጓሜው ቢጫ ወርቅ ማለት ነው፡፡ ቢጫ የፀሐይ ብርሃን ነው፡፡ ፀሐይ ከሌለ ሕይወት የለም፡፡ እንደ ፍቅረኞች ፊት የምታበራው ፀሐይ አይደለችም? የተፋቀሩ ሁሉ እየተንቦገቦጉ አይደለ የሚውሉትና የሚያድሩት?

#የስንብት_ቀለማት
አዳም ረታ

@wegoch
@wegoch
@paappii
783 viewsDAVE / PAPI, 19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-06 08:23:29 ፅልመት -

ክፍል - አምስት
(የመጨረሻ ክፍል)

በቃል ሳይነጋገሩ ተመካክረው እንደተቃጠሩ ነገር በሽፍደት ገላቸው ላይ የጠለቁ ጨርቆችን የተወላለቁት አስጎምብሶ ፀጉሯን እየነጨ ፤ እየሳመ ፤ ቂጧን እየመታ ፤ እንደምታምር እየነገራት ፤ እየሰደባት ፤እያንሿካሿከ ፤ አንገቷን እያነቀ ፤ አስለምኗት ለረጅም ደቂቃ እየገለባበጠ ወሰባት ። እውነቱ ባሏ እንዲ አዋርዶ ሊወስባት አይችልም። በባሏ ላይ መሄዷ የጥፋተኝነት ስሜት ቢሰማትም አልጠላችውም ። ከዛ ግሩም ለሁለት ሳምንት ጠፋ ። አግኝታው ትክክል እንዳልነበሩ መንገር ብታስብም ግሩም ጠፋ። ከሁለት ሳምንት በኋላ ድሮ እንደሚልክላት የመጡ እቃዎችን በቴክስት ላከላት ። ሱቋ ሄዶ ምንም እንዳልተፈጠረ የስራ ወሬ አዋርቷት ተመለሰ። Slave Sex እያሰሰች መመልከት ጀመረች ።ያየችውን የሚያሳያት ፤ እንዳየችው
የሚያደርጋት ግሩም ብቻ ነው ! ሰሌን መቀመጫዬን እየመታኸኝ ፤ ፀጉሬን እየነጨህ ፤ እየሰደብክ እንዋሰብ እንዴት ትለዋለች ? ግሩምን እሷ ፈለገችው። ግሩም ምንም መወስወስ ሳያስፈልገው ፈለገችው። ተገናኙ እንደፈለገችው ፤ እንዳየችው ለሁለተኛ ጊዜ እሱ በመረጠው ስፍራ ተዋሰቡ ። ከሰለሞን ጋ የምትዋሰበው ለሰለሙን ስሜት ብቻ ብላ ሆነ። ሰሌን እንደምትሳሳለት ፤
እንደምታፈቅረው ፤ እንደምታከብረው የሚያቃት ሁሉ ያውቃል። እች አለም መቼም ግርንቢጥ ነች ምክንያቱ እና ውጤቱ መች ይገናኛል ? ምንአልባት ግርንቢጥ የሆነችው እንደ ቤተልሄም ያሉ ሰውች አቆሽሸዋት ይሆን?? እንደግሩም ያሉ ሰዎች በክለዋት ይሆን ? ወይስ እንደ ሰሌ ያሉ ምልክት የማይገባቸው አልያ ግትር ሰዎች አስተዋፅዖ እያበረከቱ ይሆን ? ለአምስተኛ ጊዜ በእሷ የበለጠ ፍላጎት ፤ በግሩም የቦታ ምርጫ የተገናኙ ቀን ነው ባሏ ሰለሙን ያያቸው።
ቤተልሄም ባሏን ታውቀዋለች ፤ ውስልትናዋን እንደደረሰበት ስድስተኛ የስሜት ህዋሷ
ነግሯታል። ሰሌ በመኳረፍ አያምንም ።የበዛ ኩርፊያ የሚፈታው ችግር የለም የሚያባብሰው እንጂ ይላል። ሰለሞን ቤተልሄምን እንደ ልጁ ኤዶም ነው የሚሳሳላት ፤ መሳሳቱን ተርኮላት አያውቅም ፍቅሩን በምግባር የሚገልጥ ሰው ነው ። ካለ'ኔ ማን አለሽ ሚስቴም ልጄም ነሽ ይላታል። ሰለሞን በሰው ወሬ ባልተረጋገጠ ነገር ፤
ከባድ ባልሆነ ነገር እንዲህ ሊጠየፋት እንደማይችል ታውቃለች። ፊቱን ካጠቆረባት በኋላ ፤ ሰሌ ከጠላት በኋላ ሰውነቷ ቀንሷል፤ ድብርት በልቷታል ። እሷ ራሷ ራሷን ጠልታዋለች። ከተበደለ የበለጠ ፤ መበደሉን የገባው በዳይ ኑሮው ሲኦል ነው። በክፉ ትዝታ ጥልቅ እንዳለች አልጋው ጫፍ ላይ ኩርምት ብላ ጤነኛ ጭኑ ላይ ላመል ያህል እንደተደፋች ዶክተሩ ገባ እንዴት ናችሁ ብሎ ሲገባ የቤተልሄምን ፊት ያጨመላለቀውን የእንባ አሻራ አይቶ በሰለሞን
አደጋ መሰለው። "ምን ሆንሽ ልጅ ቤተልሄም ፤ ተይ እንጂ አሁን ድኖ የለ እንዴ" እያለ በገመተው ጉዳይ ላይ ገሰፃት። በማናውቀው ጉዳይ ላይ ገምተን ማፅናናት ከትዝብት እና ከአስብልሃለሁ ውጪ የሚያመጣው ትርፍ የለም። ከሆስፒታል ከወጡ ከወር በኋላ ፤ከጥፋተኝነት ስሜት ስላልተላቀቀች ነፃ መሆን ሲታገላት ሰለሙን ቤቲሻዬ እናውራ አላት ያቺ የፈራችው እለት ደረሰች ፤ አስባበት አብሰልስላው ፤ አውጥታ እና አውርዳ ከልቧ ብትማከርም ፤ እናውራ ሲላት ሆዷ ባባ ። ፊቷ በሃዘኔታ እያየ ይቅርታ አድርጌልሻለሁ አላት ። ፍቅር የሚለካው ለምናፈቅረው ሰው ይቅር ለማለት እና ለመረዳት በምንሄድበት ርቀት እና ብዛት ነው። ወድቀሽ እምነቴን በላሽብኝ ። ትሆኛለሽ ያላልኩት ቦታ ተገኘሽ። ራስሽን ትበድያለሽ ፤ በዚህ መጠን ትጎሳቆያለሽ ባላልኩበት ደረጃ ፤ ማቅ ከመልበስ የማይተናነስ ፀፀት ውስጥ ራስሽን አድርገሽ ራስሽን ይቅር ማለት አቅቶሽ አየሁሽ ። ሳትነገሪኝ አሳየሺኝ ፤ ስለማውቅሽ ገባሽኝ። ይሄ በእኔ እና በአንቺ መሃል ያለ በእኔ እና በአንቺ መሃል የሚቀር ገመና ነው ። ከፈፀምሽብኝ በደል ያሳየሺኝ ፍቅር ይበልጥብኛል ። ባየሁት ውስጣዊ እና ውጫዊ መቆሳሰል ሳቢያ ብሰቃይም ፈጣሪ እችለው ፤ እማርበት ዘንድ መንገድ ከፍቶልኛል። ደሞም በሌላ ምክንያት ብንጣላ ፤ ብንቆስል ይሻላል እንጂ ፤ ለአንቺስ ዘሙታብኝ ተውኳት ብዬ ስሄድ ፤ አንቺስ ምን አይነት ስሜት ይሰማሻል? ያ ሁሉ ጊዜ ያፈቀርሽኝ ፤ የዋልሺልኝ ለመኖር አንድ ምክንያት እንዳልሆንሽኝ ሁሉ ፤ በአንድ ትልቅ ስህተት በዜሮ ለምን እደረምሰዋለሁ ። ኤዶም ነገ በምን ተጣላቹ ስትለኝ በምንስ እላታለሁ?? ብሎ አይን አይኖን አየ ቤቴልሄም ከብዙ ዝምታ በኋላ "ጌታዬዋ እኔ ካንተ ብለያይ በመለያየቴ ብቻ አይደለም የምጎዳው መተካት ባለመቻሌ ነው። አንተ የምትተካ ሰው አይደለህም ። የእንደዚህ አይነት ክስተት መጨረሻ ወህኒ ቤት ነበር። እወድቃለሁ ባላልኩት መንገድ ወደኩኝ ራሴን እስክጠላው ። መደበቂያ ፤ መኮብለያ እስካጣ ፤ ነፍሴ እስክትጨነቅ ነው መሽቶ በነጋ ቁጥር መፅናኛ ያጣሁት። ይቅርታ መቼ ጠየኩህ ስብራቴን አይተህ ማርከኝ እንጂ። አጥፍቻለሁ ፤ ይቅርታ ስላረክልኝ አመሰግንሃለሁ ። ራሴን በመፀየፍ እንዳልኖር ፤ ትከሻህን ሰጠኸኝ ብላ እግሩ ላይ ወደቀች። አነሳት እና አቀፋት አንገቱ ስር ውሽቅ አለች። አንድ አንድ ውድቀት ትሁት እንድንሆን ያድቦለቡለናል ፤ እንዳንፈርድ ያንፀናል ። አፈቅርሃለሁ ሳይሆን ሳፈቅርህ እኖራለሁ ፤ ነገር ግን ካንተ ጋር መኖር አልችልም። ነገ ሲውል ሲያድር ፤ የሚያስመሽ ጉዳይ ሲገጥመኝ ፤ ስልኬ ቢዘጋ ምን ትላለህ ፤ ምንስ ያስብ ይሆን እያልኩ መሳቀቁ ይገለኛል። ይቅርታ አረክልኝ ማለት እኔ ላይ እምነት ይኖርሃል ማለት አይደለም ፤ እምነት ሲደረመስ እንጂ ሲገነባ ዘመናት ይፈልግል። የቤታችን ምስሶ መተማመናችን ነበር ናድኩት ፤ አይኗ እንባ ግጥም አለ ፤ እንባዋን ለመቆጣጠር ታገለች ፤ አልሆነም አሸንፏት ወረደ ይሄውልህ ጌታዬዋ ፍጡር እንደፈጣሪ አይደለም ይቅር ብሎ አይረሳም ። ፍጡር እንደ ፈጣሪ አይደለም
ለበደልነው በደል ከንስሃ በኋላም ይጠይቀናል ፤ አምላክ ነው ከቀጣን በኋላ ቁስላችንን የማይነካብን ፤ የሚረሳልን ። ነገ ሳስከፋህ በደሌ ውስጥህ ያቃጭልብሃል ። ሰትበድለኝ ጮኬ ስናገር የበደልኩህ ይጮህብኛል ወይ አንተ ታስታውሰኛለህ። ነገ ድንገት ከማንም ጋ በመጋደም ብትጠረጥረኝ እንዴት ትጠረጥረኛለህ ማለት አልችልም፤ አንተም እንዴት በዚህ ተልካሻ ነገር ልጠረጥርሽ እችላለሁ ማለት አትችልም ፤
የትዳራችንን መዓዘን ደርምሼዋለሁ ። ጌታዬዋ ላፍቶ ሄጄ ተከራዮቹን ልቀቁ ብያቸዋለሁ ኤዶሜ ከኔ ጋ ብትሆን ደስ ይለኛል ግን አንተ ደስ እንዳለህ አለችው" እንርግት ፤ ዝም እንዳለ ፊቱ ላይ ምንም ሳይነበብ ቃል ሳያወጣ ቆይቷ አለም እንዲም ነች አለ ።ሌላ ምንም ሳይናገር አንገቱን በእሽታ ነቀነቀ።

-ህይወት ቢቀጥልም ይሄ ፅሁፍ አልቋል -
---- ---- ---- ---- ----

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Adhanom Mitiku
1.3K viewsDAVE / PAPI, 05:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-01 18:26:09 -ፅልመት-

ክፍል አራት

ቤተልሄም አልኳት ደንግጣ ትኩር ብላ አየችኝ ፤ከስንት ወር በኋላ ነው የጠራኋት ድሮ ድሮ ለቀልድ ነበር ሙሉ ስሟን የምጠራት ፤ ድሮ ድሮ ቤተልሄም ስላት ጌታዬዋ ነበር የምትለኝ። ዛሬ ቤተልሄም ብዬ ስጠራት ደንግጣ አፍጥጣ ብቻ አይታኝ አጎነበሰች ፤ ጌታዬዋ ማለት የፈለገች ይመስለኛል ግን ደግሞ ከንፈሯ አልላቀቅ ስላላት ነው ወዬ ማለትም ፈልጋለች ፤ ጆሮዋን ጠርቻት ይሆን አይሆን ማመን ስላልቻለች ነው። ቀስ ብላ በለሆሳስ እየተራመደች ጠጋ አለችኝ እረጋ ብዬ ለስለስ ባለ ቃላት ምነው አልኳት? ትኩር ብላ ከወገቤ ብቻ ቀና ያልኩበት የሆስፒታሉ አልጋ ላይ ቁልቁል በስስት ተመለከተችኝ። ቤት ለምን አትሄጂም ኤዶሜ አትናፍቅሽም አልኳት? አልጋ ላይ እርፍ ብለሽ ፤ ጠንከር ብለሽ ብትመጪ አይሻልም አልኳት ቀስ ብላ በእርጋታ አልጋው ጫፍ ላይ ቁጭ አለች። በስስት በመኪናው አደጋ ሳቢያ የተጎዳውን ሰውነቴን እያየች ። "ትንሽ ቀን ነው የቀረን አብረን እንሄዳለን አለችኝ "። አንች እኮ በጣም እየተጎዳሽ ነው አልኳት። አይኗ በፍጥነት ትኩስ እንባ አረገዘ ጭኔ ላይ ያረፈውን እጄን ሳመችው ። እጄን እንደያዘች ፤ "አንተን ለማን ጥዬ" ብላ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች። እጄ በእንባዋ ራሰ ዘማዊቷ መቅደላዊት የጌታዋን እግር በእንባ ስታጥበው የነበረው የንስሃ እንባ ከቤተልሄም እንባ ጋ ተመሳሰለብኝ ። እጄን ከእጇ በቀስታ ነጥቄ የተሰባበረ ፀጉሯ ላይ አደረኩት ። ፀጉሯን ሳሻሻት ፤ ሆዷ ባባ መሰለኝ ፤ የበለጠ አለቀሰች ፤ ሲቃ እየተናነቃት ተንሰቀሰቀች ። ከሲቃዋ ጋ እየታገለች ፤ ቃላቷ እየተደናቀፈባት "ለእኔ ባረገው !" አለቺኝ ። እንዲህ ያለቀሰችው አባቷ የሞቱባት እለት ብቻ ነው ። አለቃቀሷ ፤ ጉስቁልናዋ ፤ ኩርምት ማለቷ አንጀቴን በላው መሰለኝ አይኔ በእንባ ሞላ ። አቅም አነሰኝ እንጂ እንዲህ እየወደድሺኝ ለምን ካድሺኝ ማለት ፈልጌ ነበር። ነገር ግን ማለት የቻልኩት እንደዚህ ራስሽን የሚያስጥልሽን ፤ በዓይንሽ ሙሉ እንዳታይኝ የሚያደርግሽን ስህተት ውስጥ እንዴት ገባሽ አልኳት ?? ቤተልሄም የአይኗ ሽፋሽፍት በእንባ እንደተጨማለቀ በሃሳብ ሄደች ግሩም ጋ ግሩም እቃ የሚያስረክባት ደንበኛዋ ነው። በቴሌግራም ፤ በሜሴንጀር እቃ ያሳያታል ፤ ይጨዋወታሉ ፤ ይከባበራሉ ። ግሩም ነፃ አይነት ሰው ነው ፤ የፈለገውን የሚቀልድ አይነት ፤ በቤተልሄም ግዙፍ መቀመጫ ላይ ያሾፋል ፤ ብቻውን ይስቃል ፤ ወፍራም መቀመጫ ላለው ምን አይነት ወሲብ
ምቹ እንደሆነ ይቀላብዳል ። ትሰማው ትሰማው እና አንተ ጨምላቃ ትለዋለች። ሌላ የስራ ወሬ ይቀጥላል። ክችች አይልም ። እንደዚህ አይነት ቀልድ እና ጨዋታ ከእሷ ጋ ብቻ እንደሚጫወት ሹክ ይላታል ። ቁንጅናዋን ያስታውሳታል ፤ ያከብራታል ወይ እንደሚያከብራት ያስመስላል።
ከሌሎች አቅራቢዎች የተሻለ በጥሩ ዋጋ ስለሚያቀርብላት ፤የገዛቸውን እቃ ገንዘብ በቶሎ
አምጪ ስለማይላት ሙጥኝ ብላበታለች
ግሩም ምቹ ጊዜ ሲያገኝ ፤እንዴት አጣፍጦ እንደሚዋሰብ ይተርክላታል። ጡቷን እንደሚያምር ጠቆም ያደርግላታል ፤ ከወሲብ ወጣ ያለ ቁምነገርም ጨዋታም ያወራታል። ቁም ነገር ሲያወራት ፤ ሸፋዳነቱን ያስረሳታል ፤ ወሲብ ነክ ጉዳይ አይቀላቅልም በሌላ ቀን ይመጣ እና
ስለወሰባት ልጅ መቁነጥነጥ ፤ ማቃሰት ፤ መሻፈድ እርካታ እያዋዛ አፏን አስከፍቶ
ይተርክላታል። አወሳሰቤ ስቧት ድገመኝ ያላለችኝ የለም እያለ አለስልሶ ይጎርራል ከዛ ወሲባዊ ወሬውን አያስረዝመውም ፤ እሷ ከራሷ ጋ ታግላ ከማስቆሟ በፊት ራሱ ያቆማል ። እንድታወራለት በትንሹ መንገድ ስትከፍትለት ሆን ብሎ እንዳልገባው ይሆናል። እጥረት ደሞ ለፍላጎት መናር አስተዎፅዖ ያበረክትም የለ ከባሎ ሰለሙን ጋ የምትወስበው ወሲብ ባህላዊ ሆነባት ። ከሰለሙን ጋ አልፎ አልፎ ትዋሰባለች ፤ ሰለሙን ከእሷ በፊት ልምድ የለውም ፤ ቅደመ ወሲብ የለ ፤ መላላስ ፤ መማጠጥ ፤ መፋተግ ፤ መጋፈፍ ፤ ኖሮት አያውቅም ። እሱ ሲጨርስ የእሷን ስሜት
አይለካም ። ብዙ ቀን ምልክት ብትሰጠው አልገባው ብሏል። የግሩም ወሲባዊ ትረካ የሰለሙንን ድክመት አጎላባት ። በወሲባዊ ህይወቷ ደስተኛ እንዳልሆነች አስተያየችው።
ከራሷ ጋ ተሟግታ እንደዚህ አይነት ወሬ አታውራኝ ባለትዳር ነኝ እኮ እለዋለሁ ብላ ቃላት
አሰናድታ ሱቋ ሲመጣ ሲያገኛት በጠበቀችው እለት አያወራትም። ተገማች አለመሆን አላማን ለማሳካት ምቹ ነው ። አዕምሯችን የምንመግበው ውጤት ነው። እንዴት ሰው የሚያቀውን ከሰማው ጋ ያወዳድራል ። ለነገሩ ሴጣንስ ቢሆን ሄዋንን የረታት ያላየችውን በማስጎምጀት አይደለምን?
ግሩም እንደሚላት አይነት ወሲብ ከባሏ ጋ ለመዋሰብ አስባ ወደ ቤት ብዙ ቀን አቅዳ ቤቷ
ሄዳ ታውቃለች ። በዚህ መጠን ግልፅ መሆን የመጣችበት ቤተሰብ እና ማህበረሰብ አልፈቀደላትም። ከመሬት ተነስታ አወሳሰባችን እንቀይረው ማለት ከበዳት። አንድ ምሽት ልብስ ሲቀይር ሲራቆት ጠብቃ ፤ ጌታዬዋ አለችው ፤ ሲዞር ስሷን ፒጃማ በዳንስ መልኩ አሸቀንጥራ ፤ ጥላ ተጠመጠመችበት ሳመችው ፤ ፈገግ ብሎ ምን ሆነች ዛሬ አስተያየት ሲያያት ትዝብቱ አስፈራት ፤ በአቀደችው መንገድ አልሆነም ፤ የአዘቦታቸውን አወሳሰብ ተዋሰቡ ግሩም ባለትዳር ሆኖ ሌላ ጋ መሄድ የተለመደ ነው እያለ በጋራ የሚያውቋቸውን ሰዎች እንዴት በትዳራቸው ላይ እንደሚሄዱ በማስረጃ ነገራት። ስትገረም ተራ ነገር መሆኑን እያቀለለ ያሳያት ጀመር። ሴጣንስ ኢየሱስን ሊያስተው ጥቅስ እየጠቀሰ አልነበር ።ታማኝ ብላ የምታከብራቸውን ሰዎች እንደጥቅስ እየጠቀሰ ለብልግናቸው አመቻቻት። አንድ ቀን ሱቋ አመሻሽ ላይ የመውጫዋ ሰዓትን ጠብቆ ፤ ሱቅ እየዘጋጋች ሳለች መጣ ፤ ስለ ስራ ሌሎች ጉዳዮች እያወራት ፤ ወሬውን ጠምዝዞ ወሲብ ቀስቃሽ ወሬ ፤ የሚያሻፍድ ስዕላዊ ትረካ በተካተተበት ሁኔታ እየተረከ አፏን ከፍታ ስትመሰጥ በዝግታ የሱቋን በር ተነስቶ ዘጋው ። አንድ አንዴ የሰውነት ሁኔታ ከቃል በላይ ያግባባል ፤ በደመ-ነፍስ እንደሚታረድ በግ ምንም ሳትናገር ጠበቀችው

ይቀጥላል ......

@wegoch
@wegoch
@paappii

#adhanom mitiku
1.1K viewsDAVE / PAPI, 15:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-01 14:43:14 -ፅልመት-

ክፍል ሶስት

ከአራት ቀን ራስን መሳት በኋላ አንድ ትልቅ ሆስፒታል ውስጥ ራሴን አገኘሁት። ጭንቅላቴ የእኔ እንዳልሆነ እስኪሰማኝ ድረስ ህመሙ ከብዶኛል ፤ አንገቴን ላዞር ስሞክር ህመም ተሰማኝ ለካ የአንገት ድጋፍ አጥልቄያለሁ ፤ እግሬ በጀሶ ተጀቡኗል ፤ እንደ ቄስ ጥምጣም የዞረው ፋሻዬ ጭንቅላቴን አልብሶታል። ምን በድዬ ነው አካሌም መንፈሴም አንድ ላይ እስኪጨረምቱ የቆሳሰልኩት። እጅግ ተሰቃየሁ ። ምኔን ላስታም ። ቀና ስል ወንበር ላይ ኩርምት ብላ የተቀመጠች የድሮ ሚስቴን ብቻዋን አያታለሁ። ከስሬ አጠፋም ፤ እዛው ነው የምታድረው ፤ የግሏን ስራ ብትሰራም እኔን ለማስታመም የተወችው ይመስለኛል። አይኔን ስገልጥ አጥቻት አላውቅም ሊጠይቁኝ የሚመጡት ወዳጆቼ እንቀየርልሽ ቢሏት ፤ ዶክተሮቹ ቢመክሯት ፤ የድሮ ሚስቴ
አንገቴን በካራ አለች ፤ ከእዚህ ሆስፒታል እሱ ካልወጣ አልወጣም አለች። ፊት አልሰጣትም ፤ አላዋራትም ። እገላምጣታለሁ እቆጣለሁ ፤ ታለቅሳለች። እነጫነጫለሁ፤ አጉተመትማለሁ ፤ አሽሟጣታለሁ ። በጥቂት ወራት ውስጥ ከሰውነት ተራ ወጣች ማንም ሰው ጥሩ ገቢ ያላት ፤ ፋሽን የምታሳድ ፤ ዛሬ የለበሰችውን ነገ የማትደግም ነበረች ቢባል ግነት ይመስላል። ያለን ነገር ጠቅላላ በነበር ተከበበ ። እኔን ሊጠይቁኝ የሚመጡ ሁሉ ከሰውነት ተራ መውጣቷን እያዩ ዞር ብለው እሷን ገስፀው ፤ አፅናንተው ይሄዳሉ ተቆርቆሪነት በወለደው የወዳጅነት መንፈስ ።
አንድ ቀንም ምግብ ብይ ተጎሳቆልሽ ፤ቤት ሂጂና እደሪ ብያት አላውቅም ፤ በወጉ ስትበላም
ስተኛም አይቻት አላውቅም። የሆነ ጠዋት ከእንቅልፌ ስነሳ የድሮ ሚስቴን ሳያት ማድያት ጀማምሯታል ። ፀጉሯ ተሰባብሯል ፤ ሽበት ጀማምሯታል ፤ የለበሰችው ቱታ ራሱ ተነጫጭቶል ። ስቆጣት አይኗ እምባ ሲቋጥር ፤ ስታጎርሰኝ በክፉ አይኔ ሳያት ፤ የስሜቴን መቆጣት ስታይ እያለቀሰች ነበር
የምታጎርሰኝ ። ከቀናት መንጎድ በኋላ ኩርምት ካለችበት ቦታ ላይ ሸለብ አርጓት ሳያት ያለፉት የሆስፒታል ቆይታችን ትውስ አለኝ ፤ አሞኝ ሳቃስት እሷ ስትርበተበት ፤ በስሜቴ መኮማተር የወረደው
እንባዋ ፤ ለመንካት እንኳ በራቀ መልኩ ገላዬን በፎጣ ስታብሰው አንድ ባንድ መጣልኝ ። በእዚህ ሁሉ ፊት መነሳት ውስጥ ፤ በእዚህ ሁሉ መነጫነጭ ውስጥ ልጃችን ኤዶም ጋ
እንኳን ልሂድ ብላ ከሆስፒታል ጥላኝ ወጥታ አታውቅም ። የሁለታችንም ቤተሰቦች
ባይኖሩም የቅርብ ጓደኞቼ እንኳን እንደር ሂጂ ቢሏት እሱን ትቼ ነው የምትለው ኤጭ
ፍርጃ ነው ለዛች እምነቴን ለበላችብኝ ። ለዛች አይኔን ላስለቀሰችው፤ ለዛች ልቤን ለሰበረችው ፤ለዛች አንገቴን ላስደፋችው ፤ለዛች ሳቄን ለቀማችው ፤ለዛች ቀልቤን ለነጠቀችው፤ ለዛች ቤቴን ላቀዘቀዘችው የድሮ ሚስቴ። አሳዘነችኝ !! ከስንት ወር በኋላ ቤተልሄም አልኳት ደንግጣ አየችኝ

ይቀጥላል ....

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Adhanom mitiku
1.4K viewsDAVE / PAPI, 11:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-01 06:09:39
ለመጨረሻ ጊዜ ያቀፍኩት እዚህ በር ጋር ነበር:(
ያቺ ሴትዮ ስለማትወደኝ ወደ ቤታቸው ገብቼ አላውቅም።
ሰላሳ ሶስት ሳምንት ከሶስት ቀን ሙሉ አልደወለልኝም:(
ስለዚህ ንጋት እዚህ እየመጣው እጠብቀዋለው! እዚህ ስውል ያቀፈኝ ያቀፈኝ ይመስለኛል!
የሳቅነው ያስለቅሰኛል! የተደሰትንበት ያናድደኛል!

ቆይ ተስገብግበን ናፍቆት ብንለማመድስ ኖሮ?
ቆይ የማላውቅበትን ጠብቅሃለው ምን አስባለኝ?
ቆይ ምንአባቱ የማይመጣልኝ?
ቆይ ምን አባቱ የማያቅፈኝ?
ቆይ ምናአባቷ ይቺ ሴትዮ ስታየኝ የምታዝነው?
..........
Ribka Sisay
..........
@ribkiphoto
1.8K viewsRibka Sisay, 03:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-30 21:16:35
ካራማራ ጫፉን አያይዤ ልስፋው?
ካራማራ አናቱን ሻሽ ልደርብለት?
ካራማራ ልቡን በምን ላርስለት?
....
Ribka Sisay
....
@ribkiphoto
978 viewsRibka Sisay, 18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-28 07:22:27
የጁመዓን ሲሳይ አያውቁም። ዱዐ በማረግ ፈንታ በየጎዳናው ይቅበዘበዛሉ። ከዛ ቅዳሜ ሲሆን አላህ እኔን አይሰማኝም እያሉ ያማርራሉ።

ያ ረቢ ሳይጠይቁ የሚጠብቁህን ምንድነው ምታደርጋቸው? ከእኛ እኩል ነው የምታያቸው?

......
ጁመዓ ሙባረክ
...
Ribka Sisay
....
@ribkiphoto
@wegoch
1.3K viewsRibka Sisay, edited  04:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-27 22:37:02 -ፅልመት-

ክፍል ሁለት

ከቤተልሄም ጋ በጋራ ወደ ቀለስኩት ጎጆ ሄድኩ ።
ሳሉ አምላክ እንዳየቺኝ ሰላም ሰሌ? አለቺኝ ፤ በስሱ ሰላም ሳሉ ብዬ አጉተመተምኩ። ሳሉ እቤት የምታግዘን አጋዣችን ናት። ቤቴ ያ ቅድም የወጣሁበት ቤት አልመስልህ አለኝ ። አስጠላኝ። ሳሉ "ምነው አመመህ እንዴ" አለቺኝ ምነው? ስላት ፊትህ ጥሩ አይደለም አለቺኝ "አዎ አሞኛል" አልኳት ቀና ስል የሰርጋችን ፎቶ ግድግዳ ላይ ተለጥፎ አየሁት ። ትክ ብዬ ስመለከተው ከግድግዳው ላይ አውረደህ ሰባብረው አለኝ 'ማደጋችን የሚለካው የምንፈልገውን ሁሉ ባለማድረግ ነው' ቀጥታ መኝታ ክፍል ሄጄ ተኛው ። እኔ ገብቼ ጋደም ካልኩ አንድ ሰዓት ቆይታ
የድሮ ሚስቴ ገባች መቼም የድሮ ሚስቴ ነች ። የተፋታነው ቅድም ሆቴል ውስጥ ያን ክንውን ካየሁ በኋላ ነው። አልመጣም እንዴ ሰሌ ስትል ሰማኋት ፤ ድምጿ ለካ ያስጠላል ። ነገሩ ከሃዲ ደሞ ምኑ ያምራል ? ትንሽ አሞታል አለቻት ። ምነው ጠዋት ደና አልነበር እያለች ወደ መኝታ ክፍላችን ስትመጣ ኮቴዋ ይሰማል ። እንደ ተኛው መሰልኩ። ህመማችን የሚባባሰው የበሽታዎቻችን ምክንያት እናክምህ ሲሉ ነው።
ወዳጃችን ሲያቆስለን ህመማችን የሚበረታው እንደሚያስብልን ማስመሰሉ ስለማይቀር
ነው። ብርድ ልብስ ውስጥ ተጠቅልዬ ማሰብ ማቆም ያልቻልኩት ነገር ቢኖር ክህደቷን ነው ።
ሰው ከካደው ጋ እንዴት ኑሮን ይገፋዋል ። አለማወቅን የመሰለ ነፃነት የት አለ ?! ዛሬ እዛ
ሰዋራ ሆቴል ባልገኝ መቼ ህይወት ይገለበጥብኝ ነበር??? እስከዛሬ አልፎ አልፎ በኔ ጉትጎታ ብቻ የምንዋሰበው ለካ ውጪ ከማንም ጋ ስለምትጋደም ነው። ለካ እስከዛሬ ለቅሶ ገለመሌ እያለች አምሽታ የምትመጣው የትም ስትሸረሙጥ ነው ! ጭንቅላት አንዴ አይመረዝ አዕምሮ ውስጥ የሚመጣ አንድ መልካም ጥንጥዬ ነገር እንኳን
አይኖርም ። በጣም ሲመሽ ሰሌ ሰሌ እያለች ቀሰቀሰቺኝ ፤ ቀና አልኩ ፊቴን ስታየው ደነገጠች ፤ ድምጿን ጮክ አድርጋ እንዴ ምነው በጣም አመመክ እንዴ ምን ነው?? ዝም ብዬ ትክ ብዬ አየኋት ። ፊትህ ጠቁሯል ፤ አይንህ ብር ብሏል፤ በጣም አልቦሃል ፤ ምን ሆንክ? ሃኪም ቤት እንሂድ
እያለች ብዙ ቀላበደች ። ፊቴ እንደተጨማተረ ፤ በአስለቀሰችው አይኔ ትኩር ብዬ እያየኋት ደህና ነኝ! አልኳት ሁኔታዬን አይታ ይመስለኛል ቃል አልተነፈሰችም !! ፒጃማ ቀይሬ ተመልሼ ተኛው ፤ እንቅልፍ በአይኔ ሳይዞር ፤ በጣም በጠዋት ወደ ስራ ሄድኩኝ ። በዛ ሰሞን አመመህ? ምን ሆነሃል ? ከሳህ የማይለኝ አንድም ወዳጅ ጠፋ ።
የውስጥ ሰላም ሲናጋ ፤ የማይናጋ የሰውነት ክፍል መቼ ይኖራል ። ዘውትር ማታ እቤቴ ስመጣ የማንጠለጥለው አትክልት ፣ ኬክ ፣ ዳቦ እርግፍ አድርጌ ተውኩት ። እንደበፊቱ ልጄን ማጫወት እያንዳንዷን እንቅስቄሴ መጠየቅ አቆምኩ ።
ለካ ሰነፍ ሴት የሞቀ ቤት ታቀዘቅዛለች። ቤተልሄምን አላኮረፍኳትም ፤ ሰው የሚኳረፈው ጭላንጭል ፍቅር ሲኖር ነው። ስታወራኝ
እመልስላታለሁ። ቤተልሄም ምክንያታዊ እንደሆንኩ ስለምታውቅ ዝምታዬን አትንቀውም ።ኮስተር ብዬ ያኮረፍኩበትን ጉዳይ ስናገር ፤ የምዘረዝረው አሳማኝ ምክንያት እንደሚኖር ትላንታችን ምስክር ነው። ምክንያታዊነትህን እወድልሃልሁ ትለኝ ነበር ። እንደምትወደኝ ተጠራጥሬ አላውቅም ነበር አንድ ቀንም !ነፍሴ ተጠይፏታል ። ጎጆ እንደ እምነት አይደለም በአንድ ለሊት አይደረመስም ። ቤቴ ላይ
የማፈሰውን ትኩረት እርግፍ አድርጌ ተውኩት ። ስለወጪ ከሳሉ ጋ ብቻ አወራለሁ። ቤቴ በቶሎ ላለመግባት የድሮ ጓደኞቼን ማሰባሰብ እና መጠጣት ጀመርኩ። አንድ ቀን የያሁት ነገር ኑሮዬን ቀለበሰው ። የነበረኝን ፍቅር ደረመሰው ። ፍቅር እንደዚህ ማያያዣው ስስ ነው??
ስለ አለም የነበረኝ ምልከታ ተዛባ ።
እንዲ እየኖርኩ ሳለ አንድ ቀን ወደ ስራ እየሄድኩ የተሳፈርኩበት ታክሲ አቅጣጫ ስቶ ሲበር ይመጣ ከነበረ ዘመናዊ የቤት መኪና ጋ ተላተመ። ከውስጣዊ ስብራት ሳልጠገን ሌላ ውጫዊ አደጋ
ይቀጥላል...

@getem
@getem
@paappii

#Adhanom Mitiku
512 viewsDAVE / PAPI, 19:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-26 22:22:19 "ድምቀት ወ ፅልመት"



አርብ 'ለት ነበር ፣ 12:00 ሰአት አካባቢ፣ ቀኑ ቀን አልመስል እያለኝ ወደቤቴ ለመሄድ መንገድ ላይ ሳለው አብዶ ይሁን ፣ እያበደ ይሁን ግራ የሚያጋባ ሰው ድንገት በመንገድ ላይ ያገኘኝና ልክ የዘመናት ጓደኛው እንደሆንኩ ያክል ያወራኝ ጀመር።

" አየሀት ያቺን ጀንበር? ....... ፣ ገና እያጎጠጎጠች ያለች ቆንጆ ሴት ትመስላለች ፣ ልክ እንደ አንዲት ሴተኛ አዳሪ ፣ ልክ እንደ አዲስ ፍቅረኛሞች....፣ ግን ፈጣሪ ለምንድነው ይሄን ያክል የምታሳሳ ልጅ ያስመሰላት?............. ግን አንተ ምን ይታይሀል?....... " አለኝ ። እየተከተለኝ ይሁን መንገዳችን ተገጣጥሞ በምታጠፍበት እየታጠፈ ፣ ጀንበሯን አዘቅዝቆ እያየ ይጠይቀኛል።

" እኔ እንኳን ስራ ፈትቼ እሷን የማይበት ጊዜ የለኝም " አልኩት ። እንዲተወኝ ፈልጌ እንጂ ሳላያት ቀርቼ አልነበረም።

" ተፈጥሮ ለማን የተፈጠረ ይመስልሀል ?"

" ያው ለራሱ መሰለኝ " አልኩት ጥያቄው ስላልገባኝ ።
" ተፈጥሮ ሁሉ ለሌላ ጠፈጥሮ ነው የተፈጠረው ፤ ሰው እንኳን ለሌላ ሰው ነው የተፈጠረው " አለኝ አይኑን ከጀንበሯ ሳይነቅል።

"እና ምን ነበር ይታየኛል ያልከኝ" አለኝ ምንም እንዳላልኩት እያወቀ።

" እኔ እንኳን ቆንጆና ደማቅ ጀንበር ናት ምትታየኝ" አልኩት ፣አስተውዬ ለማየትም አልሞከርኩም ምክንያቱም ሰውየው እብድ ይሁን ጤነኛ እርግጠኛ አልነበርኩም።

"አንድጊዜ ቆንጅዬ ልጅ መንገድ ላይ አየሁና መከተል ጀመርኩ" አለኝ ያቺ ቆንጆዋ ልጅ ጀንበሯ አንደሆነች ያክል ወደ ጀንበሯ እያፈጠጠ።

"እሺ......." አልኩት

"ተከተልኳት ተከተልኳት ተከተልኳት....."

"እሺ ከዛስ.." ደገምኩት

"ተከተልኳት ተከተልኳት ተከተልኳት...."
ሳቄ እንደ ትንታ አመለጠኝና ወዲያው ዝም አልኩኝ።

"ተከተልኳት ፣ እንደዚ ቆንጆ ሆና ግን ማንነቷን የሽማግሌ ኪስ ወስጥ አገኘዋለው ብዬ አላሰብኩም ነበር" አለኝ እንደማዘን ብሎ።

"ሌባ ነበረች?"

" ሌባ ህሊናውን ይሸጥ ይሆናል እንጂ አካሉን አይሸጥም ፣ ይቺ ቆንጆ ሰው....ነቷን ሁሉ ነው የሸጠችው ፣ እኔ እሷን መከተሌ ድካም ነው ያተረፈልኝ ፣ አንተም የጀንበሯን ውበት ብቻ ማየትህ የት እንደሚያደርስህ አላውቅም " አለኝና ለትንሽ ጊዜ ዝም አልን። ግን ምን ማለት እንደፈለገ ማወቅ እንዳለብኝ ተሰማኝ።

"አንተ ምንድን ነው ሚታይህ?" አልኩት።

" ታሳዝነኛለች" አለና እንባው እንደቀልድ መውረድ ጀመረ "በጣም ታሳዝነኛለች ፣ ስልጣኑ ቢኖረኝ እንደዚ እንዳማረባት ዘላለም ባቆያት ደስ ይለኛል ፣ ልብ ብለህ እያት ፣ መንገዷን ተመልከት ፣ ቅድም ስንገናኝ የነበረው ውበቷ አሁን የለም ፣ አሁን ያለው ውበቷ ከደቂቃዎች ቡኋላ አታገኘውም ፣ መንገዷም መጨረሻዋም የከፋ ነው " አለና ጣቱን ወደጀንበሯ እየጠቆመ ፣
" አንቺ ጀንበር ተጠንቀቂ ፣ ቀን ወደነበርሽበት ተመለሺ !!" አለና ሳይሰናበተኝ በመጣንበት መንገድ ተመለሰ።

ምን ሊነግረኝ ፈልጎ ነው? ፣ ማንስ ነው የላከው ?፣ ጀንበሯ ማነች? ፣ ቀንስ ምን ነበረች ?፣ አሁንስ ምን ልትሆን ነው? እያልኩኝ እራሴን ስጠይቅ ያቺ ገና እያጎጠጎጠች ያለች ቆንጆ ሴት የምትመስለዋ ፣ ልክ እንደ አንዲት ሴተኛ አዳሪ የምትመስለዋ ፣ ልክ እንደ አዲስ ፍቅረኛሞች የምታስቀና የነበረች ጀንበር አሁን የለችም ፣ ምድሪቱን ጨለማ ወርሶታል ፣ እኔም ከነጥያቄዎቼ ወደ ቤቴ ገባሁ ።

(ቤካ)

@wegoch
@wegoch
@paappii
592 viewsDAVE / PAPI, 19:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-26 15:24:58
የመጽሐፍ ውይይት
በ ብሄራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ኤጀንሲ

መንደሪን መንደሪን
ደራሲ: ምግባር ሲራጅ

@getem
1.3K views ገብርዬ, 12:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ