2022-04-16 21:52:36
እንደሚሞት እያወቅሁ አክመዋለሁ(ክፍል 9)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
"ቆይ ራስሽ አልነበርሽ እንዴ የነገርሽኝ?"ስትለኝ እያወራን ያለነው በአንድ ዓይነት ቋንቋ አለመሆኑ ተገለጠልኝ ።
"ምኑን ነው ደግሞ እኔ የነገርኩሽ እምዬ?"
"ለዳንኤል የፍቅር ስሜት ምላሽ ሳይሰጡ መቀመጡ የህክምናው አንድ አካል ነው አላልሽኝም ራስሽ?"
"እእእእ....እ...እሱን ነው እንዴ 'ምትይው?አዎ ነግሬሻለሁ ልክ ነሽ ኧረ እኔ ነኝ ደነዟ"አልኩ ምንተ ሀፍረቴን እየተቅለሰለስኩ።ለዳንኤል ስሜት እንዳለኝ እንዴት አወቀችብኝ ብዬ ስጨነቅ እሷ ለካ ያሰበችው ሌላ ነበር! 'አይ እምዬ! ቀልቤን ገፈፍሽው የስራሽን ይስጥሽ' ስል በልቤ
"ለሱ ስሜት እንዳለሽምአውቃለሁ!"ብላ እጥፉን ቀልቤን ገፈፈችው።ብርግግ ብዬ ተነሳሁና
"ምን አልሽ?ም...ምንድነው ያልሽው?"አልኳት ወገቤን ይዤ።ተውረገረግሁባት ቢባል ይቀላል።አላፍርምኮ ልክድ ነው?
"ምነው ዋሸሁ?" ስትናገር ከልክ በላይ ዘና ብላ ነው። ወዲያው ቀጠል አረገችና
"እናትሽ'ኮ ነኝ!እ?ይህን ዕውነት የመካድ ሀሳቡ አለሽ?" ስትለኝ
"ሁሁሁሁሁፍፍፍፍፍፍፍፍ!የለኝም" በረጅሙ ተንፍሼ አልጋው ላይ ከቁሜ ወደቅሁበት።አፍታም ሳልቆይ ፈትለክ ብዬ ተነሳሁና
"እና እያወቅሽ ነው ይህን ሁሉ 'ምታደርጊው?" በድጋሚ ጮህኩ።
"አዎ" አሁንም ዘና ብላለች።እኔ ግን ባሰብኝ
"እውነት ነበር ለካ!"አልኩኝ።
"ምኑ?"
"አባዬ እናትሽ አንዳንዴ ክፉ ናት ያለኝ...እንዴት ለማላፈቅረው ሰው ልዳር መሆኑ ሰላም ሰጠሽ?"ስል ፊቷ ተለዋወጠ።አትኩራ ለሴኮንዶች አየችኝና ለዘብ ባለ አንደበት እንዲህ አለችኝ...
"እየውልሽ ሚጥሻዬ...አባትሽ ክፋትና ለራስ ማወቅ የሚባሉት ሁለት ሀሳቦች ይምታቱበት ነበር።ለሞት ያበቃው ከልክ ያለፈ ርህራሄውና ሰው አማኝነቱ እንደሆነ ታውቂያለሽ።ስለራስህ አስብ...ላንተ ሳትሆን ለሰዎች መሆን አትችልም ማለቴ ክፉ ያስብለኝ ነበር።የዋህነቱን ስለሚያውቁ ሞልቶ የተረፋቸው ሳይቀሩ ችግረኛ መስለው አበድረን ይሉታል።አበድሮ አይረካም ነበር...የሁዋላ የሁዋላ እሱ ራሱ ነፍሱን አስይዞ በማይሆን ብድር ውሀ ሆኖ ቀረ እንጂ..."እንባዋን ታግላ ማስቀረት ተሳናት።
"...ሰማሽ ሚጡ ለራስሽ እወቂበት!ያንቺን አጥር በጅምር ትተሽ የጎረቤት አጥር ስታጥሪ ጎረቤትሽ ጀሌውን ልኮ በጀርባ ያዘርፍሻል።በሁዋላ አብሮሽ የጠፋሽን ንብረት ሊያፋልግሽ ይመጣል።ከዘረፈሽ ገንዘብ የሩቡን ሩብ 'ለአንዳንድ ነገር ትሁንሽ' ብሎ ሸጎጥ ያደርግልሻል።ብታምኚም ባታምኚም የምትኖሪበት ዐለም Reality ይህ ነው"
አሁን ደግሞ እንባዋ ቆሞ ወደሆነ ወደማላውቃት አይነት አስፈሪ ሴት ተቀየረችብኝ።የምትነግረኝ ነገር ከኔ ህይወት ጋር ምን እንደሚያገናኘው ባላውቅም ልክ መሆኗን አልክድም።ለህይወትሽ የሚበጅሽ ስዩምን ማግባቱ ነው ለማለት ነው ይሄ ሁሉ? ራሷን አረጋግታ ስትቀመጥ ጨከን ባለ አንደበት እንዲህ አለችኝ።
"ዕውነታውን ተጋፈጭው ጊዜ!"
"የምኑን ዕውነታ?"
"የዳንኤልን ሞት መቀበል ከብዶሻል አውቃለሁ።"
"ማን ያውቃል እኔ ቀድሜው እንደማልሞት?እ?"
"እየውልሽ ሚጥሻዬ..."ልትቀጥል ስትል የክፍሉ በር ተንኳኳ።
"ይግቡ"አልኩ በደመነፍስ።ዳንኤል ነበር።እናቴ ሲያለቅሱ የቆዩ ዐይኖቿን እየጠራረገች
"ልጅ ዳንኤል!ና ግባ እስኪ"አለችው።ገብቶ ከጎናችን ተቀመጠ።ዝምታ በመሀከላችን ነገሰ።እናቴ
"እ...እናንተ መነጋገር ሳይኖርባችሁ አይቀርም እኔ ልሂድ!"ብላ ስትነሳ እጇን ይዤ በተማፅኖ አስተያየት
"እማ አትሂጂ አብረሽኝ ሁኚ!"አልኳት።ከዳንኤል ጋር ለብቻችን አንድ ክፍል ውስጥ የመቀመጡን ሀሳብ አልወደድኩትም።እምዬ እንዴት እንዳሰበችው አላውቅም።
"ስጋትሽ ገብቶኛል ግን ሁለታችሁም ላይ ዕምነት አለኝ።በነፃነት አውሩ"ብላ ጥላን ወጣች።እኔኮ ግን እሷ የምታምነኝን ያህል ራሴን አላምነውም።ከመውጣቷ
"አታስቢ ዶክተር! ከበሽታዬም በላይ ስብዕናሽ ወሰኔን እንዳላልፍ ያስገድደኛል"አለኝ።ምን ዐይነት ጦር የሆነ ንግግር ነው?
"እ...እኔ እንደዛ አላልኩም...ለማለት የፈለኩት..."ጠቋሚ ጣቱን ከንፈሬ ላይ አድርጎ በምልክት ዝም እንድል ነገረኝ።ዝም አልኩ።ትኩርርርርርር አርጎ ሊያየኝ ነው ብዬ ስፈራ ጣቱን አነሳና በዝግታ ሳቀብኝ።
"አሃሃሃ...ሃሃሃሃሃ...ሃሃሃ"
"ምን ያስቅሀል?"
"ትፈሪኛለሽ አ?ምኔ ነው ሚያስፈራሽ ቆይ?"
"ኧ...ኧረ እኔ አልፈራህም!ለምን እፈራሀለሁ?"ነጭ ውሸት ዋሸሁ።ሲጠጋኝ እፈራለሁ...የሆነ የማላውቀው ንዝረት መላ ሰውነቴን ይሰማኛል...በአካል ስንራራቅ ደግሞ ንዝረቱ ወደጭንቅላቴ ይወጣል...የምናብ ንዝረት...ከሀሳብ ተነስቶ ሰውነትን የሚያናውጥ ንዝረት።ይሄንን ይመስለኛል "ኤክስፐርቶቹ" የስሜት ፍቅር የሚሉት።የስሜት ፍቅር ሲራራቁ የሚደበዝዝ አካላዊ ቅርርብ ላይ ብቻ የተመሰረተ "ፍቅር-ቅብ" እንጂ ፍቅር አይደለም ሲባል ሰምቻለሁ። ምናውቄ?ኧረ በሆነልኝና ዳንኤል በጊዜ ሂደት የምረሳው የሆነ ጊዜ ላይ በህይወቴ የተከሰተ ጥሩ ነገር ሆኖ ባለፈልኝ!
"እህህህህም!ካልሽ እሺ...ግን ከአንደኛ ሚዜ'ኮ ምንም አይደበቅም...ንገሪኝ?"
"ያምሀል ግን?ንክ ነገር ነህ አይደል? "አልኩ ሌባ ጣቴን ጭንቅላቴ አካባቢ ከጆሮዬ ከፍ አድርጌ ቡለን እንደማላላት እያጠማዘዝኩ።
"እንግዲህ ሐኪሟም አንቺ ነሽ እኔ ምናውቄ!"
"ቀልዱ እዚህ ጋ ቢያበቃና ወደቁምነገሩ ብንገባስ?"አልኩ በመሰላቸት።
"በዛች ቀን ከጎንሽ መሆን እፈልጋለሁ!በሰርግሽ ቀን!ደስታሽን ባልካፈል ይፀፅተኛል" ከምሩ ነው?
"ኧረ ተው የኛ ክርስቶስ!ፍቅርህስ የት ገባ?የመኖሬ ምክንያት ነሽ የተባልኩትስ?ወይስ ስሜቱ ሰርጌ ላይ አንደኛ ሚዜ እስከመሆን አጀግኖሀል??ፍቅርህ የት ሄደ?"እየጮህኩ አፈጠጥኩበት።የሚደነግጥ ዐይነት አይደለም።
"እሱንማ ሸጥኩት"
"ዳንኤል ክፉ ነገር እንዳደርግ አታስገድደኝ እባክህን!"የደም ስሬ ሲግተረተር ይሰማኛል።
"ምን?ልትገይኝ ነው?ትንሽ ነውኮ የቀረኝ ታገሺ ሰበብ እንዳልሆንብሽ"
"እስኪ እየኝ"አልኩ ዐይኑ ላይ አፍጥጬ።ጉንጭና ጉንጩን በሁለት እጆቼ ይዤ አፈጠጥኩበት።
"ንገረኝ"
"ምን ልንገርሽ?"
"ውሸት ነው በለኝ"
"ምኑ?"
"አ...አሁን የሚሰ...ሰማኝ"...እንባዬን ማን መቶ ተው ይበልልኝ!
"ምንድነው የሚሰማሽ?" ትኩርርርርር ብሎ አየኝ።
"ታውቀዋለህ...ሳ...ሳ..ልነግርህ ታውቀዋለህ" እንባዬን በአይበሉባው ጠረገና
"እባክሽን ተይ ጊዜ!"አለኝ እጆቼን ከጉንጮቹ እያስለቀቀ
"ምኑን ልተወው?"
"የሚሰማሽን"
"አንተ ትተኸዋል?"በድጋሚ እንባዬ ወረደ።
"በፍፁም ልተወው አልችልም"
"እንጥፋ"አልኩ ሳላስበው።
"ከዛስ?"ፈገግ አለ።
"ከዛማ በቃ አብረን እንኖራለን!"
"አንቺ ሴት ጅል ስትሆኚም ያምርብሻል ልበል!?"
"መብትህ ነው በል!በነካ አፍህ እንጥፋ ላልኩህም እሺ በል"
ይቀጥላል
ደራሲት:- ማዕዶት ያየህ
@wegoch
@wegoch
@paappii
4.4K viewsDAVE / PAPI, 18:52