Get Mystery Box with random crypto!

ወግ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @wegoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 21.12K
የሰርጥ መግለጫ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @lula_al_greeko

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-06-15 10:50:14 አነቃቂው መድረኩ ላይ እየተንጎራደደ "በህይወቴ ምርጡ ጊዜ ሚስቴ ያልሆነች ሴት እቅፍ ውስጥ ያሳለፍኩት ጊዜ ነው!" ሲል ተነገረ።

ለመነቃቃት አዳራሹ ውስጥ የተሰበሰበው ሰው በድንጋጤ ክውታ ተዋጠ።

አነቃቂው ንግግሩን በመቀጠል "እናም ያቺ ምርጥ ሴት፣ ዘጠኝ ወር በሆዷ፣ ከእዛም በጀርባዋ፣ ከእዛም በእቅፏ ያሞላቀቀችኝ ምርጥ ሴት፣ ያቺ ስጦታ ሳልሰጣት ያቀፈችኝ ምርጥ ሴት እናቴ ናት?!" ሲል ተናገረ።

አዳራሹ በሳቅ እና በጭብጨባ ተሞላ።

**
ከሳምንት በኋላ በእዚህ የአነቃቂ ንግግር ላይ የተገኘ ሥራ አስኪያጅ ድግስ ብጤ አዘጋጅቶ ዘመድ አዝማድ፣ ጓደኛ ቤቱ ጠራ። ዝግጅቱ ላይ ወዲህ ወዲያ እያለ ሰው ሲያስተናግድ፣ ሲጎርስ ከመጠጡ ሲጎነጭ ሞቅ ከማለት አልፎ ሰከረ።

ይሄኔ ነው እንግዳው ምግብ በልቶ፣ ጠጥቶ ሳይዝናና መሄድ የለበትም ሲል በአነቃቂ ንግግር ስልጠና ላይ ተገኝቶ የሰማውን ቀልድ ለታዳሚው ለመጋበዝ በመወሰን ድምጹን ጠራርጎ ንግግር የጀመረው።

"በህይወቴ ምርጡ ጊዜ፣ ሚስቴ ያልሆነች ሴት እቅፍ ውስጥ ያሳለፍኩት ጊዜ ነው!" ሲል ተነገረ።

ይሄኔ የሚስቱ ፊት፣ እንደመቅላት፣ አመድ እንደ መንዛት፣ አሸቦ እንደመምሰል ከእዛም ወደ ጥቀርሻነት ተለወጠ። ንግግሩን የሰማው የድግሱ ታዳሚ በድንጋጤ የጨው አምድ መሰለ።

ይሄኔ ባልየው በአነቃቂ ንግግሩ ወቅት የተነገረው የቀልዱ ሁለተኛ ክፍል ምን እንደሆነ ስለዘነጋ ለማስታወስ ለሀያ ሰከንዶች ያህል በዝምታ ከቆየ በኋላ ትዝ ሊለው ስላልቻለ ጎሮሮውን ጠራርጎ...

"...እናም ያቺ ሴት ማን እንደሆነች አላስታውስም!" ሲል ንግግሩን ደመደመ።
**
ማስታወሻ፣

ሰውየው ንግግሩን እንደጨረሰ ከሚስቱ በተሰነዘረበት የውስኪ ጠርሙስ ፍንከታ ምክንያት ኮማ ውስጥ ስለገባ አሁን ላይ ሆስፒታል ተኝቶ እስኪነቃ እየታከመ ይገኛል።

@wegoch
@wegoch
@paappii

By #Tilahun ango Girma
6.2K viewsPapi, 07:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 08:26:31 ፀሀፊና አንባቢ : ማዕዶት ያየህ (ዘማርቆስ)
@gize_yayeh

@wegoch
@wegoch
@wegoch
5.1K viewsPapi, 05:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 17:25:51
ቆንጅዬ ካምፒንግ ወደ ቆንጅዬዋ ወንጪ ከስንሴት ሀይኪንግ   Camping Trip to the Beautiful #Lake_Wenchi

Hiking Date :- Jun 24 & 25 (ሰኔ 17 እና 18)

       Activities
Hiking , Socializing, Playing, Music Performance (if any), Swimming, Mud Bath, Horse riding (#self_sponsored ) , Boating and so on

         Package_Includes
4 Meals
Photography  
Transportation
Bottled water
Boating
  Guide & Entrance fee

Hiking #Cost 3400 birr

Departure: Piasa (Taitu Hotel)

Departure Time - 12:00 LT

for more join
@sunsethiking
@sunsetphotography
         https://t.me/sunsethikers

tickets available at
@Gebriel_19 (0984740577)
@ribki (0926743929)

Okay for Beginners, mid and Advance
815 viewsRibka Sisay, 14:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 11:48:11
ቆንጅዬ ካምፒንግ ወደ ቆንጅዬዋ ወንጪ ከስንሴት ሀይኪንግ   Camping Trip to the Beautifup #Lake_Wenchi

Hiking Date :- Jun 24 & 25 (ሰኔ 17 እና 18)

       Activities
Hiking , Socializing, Playing, Music Performance (if any), Swimming, Mud Bath, Horse riding (#self_sponsored ) , Boating and so on

         Package_Includes
4 Meals
Photography  
Transportation
Bottled water
Boating
  Guide & Entrance fee

Hiking #Cost 3400 birr

Departure: Piasa (Taitu Hotel)

Departure Time - 12:00 LT

for more join
@sunsethiking
@sunsetphotography
         https://t.me/sunsethikers

tickets available at
@Gebriel_19 (0984740577)
@ribki (0926743929)

Okay for Beginners, mid and Advance
1.3K viewsLeul Mekonnen, 08:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 13:51:01 ድሮ ድሮ ብሶት በወለደው በዘመነ ኢህአዴግ

¤¤¤¤

ድሮ ድሮ ከአድማስ ዩኒቨርሲቲ በዲፕሎማ ለተመረቀ ልጃቸው በሬ አርደው የሚደግሱ ቤተሰቦች ነበሩ

¤

ድሮ ድሮ ኑሮ ጥሩ ስለነበረ ህዝቡ ደረጄና ሀብቴ "ሙያሽ ይዘርዘርልሽ" እያሉ ሲዘፍኑ ሆዱን ይዞ ይስቅ ነበር

¤

ድሮ ድሮ ወደደብረ ማርቆስ የሚጓዝ አውቶቡስ ውስጥ የታደለ ገመቹን የነቀምት አውቶቡስ ውስጥ የሰማኸኝ በለውን ዘፈን መስማት ኖርማል ነበር

¤

ድሮ ድሮ ታመን ጤና ጣቢያ ስንሄድ ከመድኃኒቱ በፊት ወተትና ስጋ መመገብ እንዳትረሱ የሚል ማስጠንቀቂያ ይሰጠን ነበር

¤

ድሮ ድሮ አንድ ሱፍ ለመስፋት 30 ሜትር ጨርቅ እንጠቀም ነበር

¤

ድሮ ድሮ አዜብ መስፍን የተባሉ የቤት እመቤት ባለቤታቸው በሚከፈላቸው 7500 ብር ወርሃዊ ደመወዝ ድልቅቅ ብለው እንደሚኖሩ ከታይላንድ ጉብኛታቸው በዃላ ነግረውናል

¤

ድሮ ድሮ የመንግስት ሰራተኛው በወርሃዊ ቁጠባ ኮንዶሚኒየም ይደርሰው ነበር

¤

ድሮ ድሮ አርከበ እቁባይ የተባለ የብዙ የአዲስ አበባ ወጣቶችን ህይወት የቀየረ ከንቲባ ነበረ

¤

ድሮ ድሮ አበበ ተካ የሚባል ዘፋኝ የሆነች ቀሽት ዲያስፖራ አፍቀሮ "አለቅሳለሁ" የሚል ዘፈን አውጥቶ ሲያለቃቅስ ህዝቡ በጣም ስለተሰማው ገንዘብ ተሰብስቦ በአላሙዲን ድጋፍ አሜሪካ ሄዶ ልጅቷን እንዲያገኛት ተደርጓል

¤

ድሮ ድሮ ኃይሌ ገብረስላሴ 5 ኪሜ ውድድር ሲያሸንፍ ህዝቡ ከኮተቤ ፒያሳ ድረስ 10 ኪሜ እየሮጠ ደስታውን ይገልፅ ነበር

¤

ድሮ ድሮ ሰው ቤት ገብቶ መዘፍዘፊያ የሰረቀ ሌባ ፖሊስና ህብረተሰብ ቴሌቪዥን ላይ ቀርቦ ይወገዝ ነበር

¤

ድሮ ድሮ ከሰል ለማያያዝ አንድ ሌትር ጋዝ የሚጠቀሙ እናቶች ነበሩ

¤

ድሮ ድሮ ሀገሪቱ ውስጥ ከነበረው ህዝብ መካከል ስጋ በደንብ አያገኝም ተብሎ በፍለጋ የተገኘ አንድ አዛውንት አለቤ ሾው ላይ ቀርቦ ለ3 ዓመት ስጋ በነፃ እንዲወስድ ስሙን የረሳሁት ስጋ ቤት ቃል ገብቶላቸው ነበረ

¤

ድሮ ድሮ ተኽላይ ደምቢዶሎ ውስጥ አራርሳ ባህርዳር ላይ ሆቴል ነበራቸው

¤

ድሮ ድሮ ባለስልጣናትና አርቲስቶች የእግር ኳስ ግጥሚያ በህዝብ ፊት ያካሂዱ ነበር

¤

ድሮ ድሮ "ምግብማ ሞልቷል አምላክ መች ነሳኝ" የሚል ዘፈን ነበር

¤

ድሮ ድሮ ምግብ በተትረፈረፈበት ዘመን ከመመገባችን በፊት እጃችንን መታጠብ አንርሳ የሚል ተደጋጋሚ ማስታወቂያ ነበረ

¤

ድሮ ድሮ የ4ኛ ክፍል መምህር ካዛንቺስ ተከራይቶ ይኖር ነበር

¤

ድሮ ድሮ ማር ሲበዛ ይመራል የሚሉ ማር ያላቸው ወላጆች ነበሩን

¤

ድሮ ድሮ የቀበሌያችን ሊቀመንበር ልጆች አብረውን ደጃዝማች ወንድይራድ ት/ቤት ይማሩ ነበር

¤

ድሮ ድሮ መክሰስ የሚባል 10 ሰዓት ላይ የሚበላ ምግብ ነበረ

@wegoch
@wegoch
@paappii

By yihune ephrem
1.8K viewsPapi, 10:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-09 07:57:06 "የሙሉቀን መለሰ ትዝታዎች"
(በዕውቀቱ ሥዩም)

ከብላቴናነቴ ጀምሮ ሙሉቀን መለሰን ስወደው ኑርያለሁ። አስቴር አወቀ፣ ኤፍሬም፣ ሙሉቀን እና አበበ ተካ በዜማ ባያጣፍጡት ኖሮ የጉብዝና ወራቴ ምንኛ እጅ እጅ ይል ነበር...!
"ስለምትመኘው ነገር ተጠንቀቅ አንድ ቀን ልታገኘው ትችላለህና" ይላል ጠቢብ...!
ታድያ አንድ ቀን ራሴን ሙሉቀን መለሰ ቤት አገኘሁት። በርግጥ ያገኘሁት በልጅነቴ የማልመውን ሙሉቀንን አልነበረም፤ ሙሉቀን የወጣትነት ሥራውን ሲኮንን ነበር የደረስኩበት። "የዘፈን ምንጭ ሰይጣን ነው" ይላል፡፡(ነገሩ እንዲህ ከሆነ፤ የኢትዮጵያ ባህል ሚኒስትር ሰይጣን ላገራችን ኪነጥበብ ያደረገውን አስተዋጽኦ አስታውሶ ቢሸልመው ደስ ይለኛል...ሰይጣን አይሸለምም ያለው ማነው?)
ሙሌ የተራኪነት ተሰጥኦ አለው፡፡ ስለአማርኛ ዘፈን ታሪክ ሲነሣ ጠንከር ያለ ትንታኔ ያቀርባል፣ ለጊዜውም ቢሆን ዘፈን የሰይጣን መሆኑን ይረሳና በግሉ ስላበረከተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይተርካል።
በርግጥ የታዋቂ ዘፋኞችን ችሎታ ያጣጥላል። አንዱን ስሙን የማልጠቀሰውን ዘፋኝ ሣነሳበት...
“እሱ እንዲያውም መዝፈን አይደለም ዘፈን እንዲያዳምጥ እንኳ ሊፈቀድለት አይገባም” አለኝ በተለይ ጥላሁን ገሠሠን ተችቶ አያባራም...
”እሱ እኮ የጉልበት ዘፋኝ ነው” ይለዋል።
ነገሩን ማስ ማስ ሳደርገው ከጥላሁን ገሠሠ ጋር ያለው
ግኑኝነት የፉክክር ብጤ ይመስላል። አልፈርድበት
“ሁለት አንበሶች ባንድ ዋሻ ውስጥ አይኖሩም ” ይላል ጎርኪ። በቅርቡ ሙሌ፤ “ናፍቆት ኢትዮጵያ” ከተባለ መጽሄት ጋር ዘለግ ያለ ቃለ-መጠይቅ አድርጓል።
ከምልልሱ ውስጥ ይቺን በፈገግታ ቀንጭቤ ልሰናበት...
ናፍቆት:- ለመሆኑ እስከ ስንተኛ ክፍል ተምረሃል?
ሙሉቀን፡- ረሳሁት እስከ ሦስተኛ ክፍል የተማርኩ ይመስለኛል።
ናፍቆት፡- ድምፃዊው ጥላሁን ገሠሠ በሁለት ክፍል ይበልጥሃላ!
ሙሉቀን፡- እሱ እዚያ ደርሷል እንዴ?
ናፍቆት:– አዎ፣ የምናውቀው እስከ አምስተኛ ክፍል ድረስ መማሩን ነው ….
ሙሉቀን፡- እንዲያውም አሁን ትዝ አለኝ አምስተኛ ክፍል ድረስ ነው የተማርኩት...

(ቀንጭቤው ነው እንጂ ረጅም ነበር)

@wegoch
@wegoch
@paappii
2.2K viewsPapi, 04:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-08 20:36:17 "ምነው ማዘር ችግር አለ?"
"ኧረ የለም ዓለሜነህ!...አምና ቁርጥማት ያመኝ የነበር ግዜ ይኸን መሳይ ክኒና ነበር እምውጥ እንደው ሲያገረሽብኝ ግዜ ድጋምኛ ልዋጠው ይሆን ብየ ነው ...ሌላም አይደል"

"ኧረ...ተመሳስሎብዎት ነው 'ሚሆን ማዘር ይሄኮ post pill ነው"
"ምን pill?"
"postpill....postpill ማለት..."ብሎ ማብራሪያ ሲጀምርላቸው አንቺ እቃሽን እንዲያሻክፉሽ ወደ ጓደኞችሽ እየደወልሽ ነው።

ማዕዶት ያየህ(ዘማርቆስ)
(@gize_yayeh)
25/09/2015 ዓ.ም.

@wegoch
@wegoch
@paappii
2.2K viewsPapi, 17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-08 20:36:17 °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
   ዘርሽ ቢቆጠር ጉድፍ የለበትም።የጀግና ዘር ነሽ!በአባትሽ በኩል ቢኬድ ቅድመ አያትሽ የሚኒሊክ ዘብ ጠባቂ የቅርብ ወዳጅ ነበሩ።በእናትሽም በኩል ቢኬድ ምንጅላትሽ የሽምብራ ቆሬ ጦርነት ላይ የግራኝ አህመድን አሽከር በቀይ ጥይት ግራ ቂጡን ነድለውት ሲቅመደመድ ኖሮ መሞቱን አዲስ ዘመን ጋዜጣ የሆነ ጊዜ ላይ አስነብቧል።

  በማን እንደወጣሽ ባይታወቅም፣ዕድልሽ ይሁን ተፈጥሮሽ ግልጽ ባይሆንም፣ከአንድ ወንድ አትረጊም።ተረግመሽ ነው መሰል ከሚያጋጥሙሽ ወንዶች 25 % የሚሆኑት የጥሪ ማሳመሪያ ተጠቃሚዎች ናቸው። ልክ ስትደውይ
  "ወይ ሞልቶ ላይሞላ
   ለዚች ዓለም ኑሮ
   እኔ አልጨነቅም
   ከዛሬ ጀምሮ" የሚል መፈክር ይሁን ዘፈን ያልለየለት ብሶት ትሰሚያለሽ።(ሳትረገሚማ አትቀሪም!) ሌሎቹ 25 % የሚሆኑት ደግሞ የትንሽ ጣታቸውን ጥፍር የሚያሳድጉ ናቸው።ደህና መትረየስ እንዳነገበ ጀግና በጥፍራቸው አይን አ*ቸውን እየመነገሉ፣የከናፍራቸው ጫፍ ላይ የወጣችን ቡግር እየፈነቀሉ ቀንሽን ለሰማይ ለምድር የከበደ 'ትራጀዲ'ያደርጉብሻል።(በእርግጠኝነት ምንጅላትሽ የመቱት አሽከር ነው የረገመሽ!)

'እፎፎፎይ'ብለሽ ወደ ሌላኛው 25% ስትሮጪ መፈናፈኛ እስኪያጣ ሱሪውን የሚያስጠብብ፣ቀሪው 25% ደግሞ የሞተ ፍየል በብብቱ የያዘ እስኪመስል ድረስ አስጨናቂ ጠረን ያለው፣ላቡ ከብብቱ ስር እንደቀበና የሚወርድ ክልል-ዘለል የሆነ ፌደራላዊ ግማት ላይ ትወድቂያለሽ ።

"እና እንዴት ነው ኑሮው?"ይልሻል አፉ እንደተቀየደ ፈረስ ድዱን እያሰጣ።

  "ደህና ነው መቸም" ትያለሽ ሰው ያገኘሽ መስሎሽ።

"እናስ ተማሪ ነሽ ሰራተኛ?"ይልሻል  እንዳገጠጠ አንዴ ከላይ ወደታች፣አንዴ ደግሞ ከታች ወደ ላይ scan እያደረገሽ።

  አንድ ቀን አልፎልሽ በፀሃፊነት ወደምትሰሪበት ድርጅት ለጉዳይ የመጣ ነጋዴ ነኝ ባይ ትተዋወቂያለሽ...ቀጠሮ ትይዣለሽ።ደሞዝሽ በፈቀደው መጠን ለመዘነጥ ትሞክሪያለሽ።ከታች እናትሽ መሰረተ-ትምህርት ሲማሩ ለብሰውት ይሄዱ የነበረውን ቀሚስ ከወገቡ አስቆርጠሽ በሰውነትሽ ልክ አሰፍተሽ ለብሰሻል።ከላይ ከሰልቫጅ ተራ በ80 ብር የገዛሻትን ቲሸርት ጣል አድርገሻል።ባለፈው ወር እቁብ ሲደርስሽ የገዛሻትን የ 200 ብር ሽቶ "ምናባቱ!ሺህ ዓመት አይኖር!"ብለሽ የግራ ብብትሽ ስር አንዴ ረጭተሻታል። የቀኙንም'ኮ ልትረጭው ነበር ግን አሰብ አረግሽና "መቸስ ከጎኑ ስሄድ አንድ ጎኔ ነው በሱ በኩል የሚሆን"ብለሽ ተውሽው።ኤታባቱ!ሺህ ዓመት አይኖር!

  ፀጉርሽን በ 50 ብር ካስክ አፍሪካዊ ለዛውን ታሳጭዋለሽ።ተመስገን ነው!ሰሞኑን ማበጠሪያ አይሰበርብሽም!በፈቃደኝነት የሚያፈናቅል ሽታ ያለውን ሎሽንሽን መላ ሰውነትሽን ተቀብተሻል...ለእግርሽ ግጣም ከቆራሌው የተረፈች አንዲት ክፍት ጫማሽን ግጥም ታደርጊና ትሄጃለሽ !ወደ 'ዴትሽ'

ሰውዬሽም ከሞላ ጎደል ዘንጧል።

  "ምን ይምጣ የሚበላ?"
  "አንተ የተመቸህ ይሁን"
ጥብስ ይታዘዝና ጠበሳው ይቀጥላል ። ጥብሱ እስኪደርስ...

"እና...ደሞዜ 3000 ብር ነው አልሺኝ?"
"3200"
"ያው ነው...አሁን እኔ ወደዚህ ስመጣ የኮንትራት ታክሲ 200 ብር ነው የከፈልኩት" ብሎ ኩም ያረግሻል።ጥብሱ ደርሶ ከተበላ በሁዋላ
  "እና የቤት ኪራይ 600 ብር ነው የምከፍለው አልሽኝ?"
  "550"
  "ያው ነው 50 ብር ማለትኮ ለአስተናጋጅ የሚሰጥ 'ቲፕ' ነው"
  "እሱሰ ልክ ነህ"ከጥቂት ዝምታ በሁዋላ
"ተጫወች እንጂ ምነው?እኔ ዝም የሚል ሰው አልወድም...የምሬን ነው!የሚያስጨንቅሽ ነገር ካለ ንገሪኝ"
"ኧረ የለም!አመሰግናለሁ"
  "ምስጋና ስንቅ አይሆንም ...ባይሆን..."
  "ባይሆን ምን?"
  "ባይሆን ሌላ ጊዜ በደንብ ታጫውችኛለሽ እ?ሃሃሃሃሃ"
በኮንትሮባንድ የገባ ሳቅ ይለቅብሻል።
"እንሂድ እየመሸ ነው"ትያለሽ ሰዓትሽን አየት ታደርጊና።
"ኧረ ገና ምኑን ያዝነውና!አይዞሽ እኔ ራሴ ነኝ በኮንትራት ታክሲ ቤትሽ የማደርስሽ"ብሎ ሳይሰማሽ መጠጥ ያዛል ።'አልኮል አልጠጣም' ብለሽ ለመገገም ትሞክሪያለሽ።
"ምናይነቷ ናት ባካችሁ?ልንዝናና አይደል ወይ የመጣነው?እንደ ህፃን ፋንታ ልትጠጪ ነው?"ብሎ እንደምንም ቀበጣጥሮ አንድ ቢራ ያስከፍትልሻል።እየተሽኮረመምሽ መቀማመስ ትጀምሪያለሽ።ሞቅ ሲልሽ ፍርሀት ቢጤ ይሰማሽና

"እየመሸ ነው ብሄድ ሳይሻል አይቀርም"ስትይ ሰዓቱን አየት ያደርግና 
"ሆሆሆሆ እንዴት ያለችው ላይ ጣለኝ ባካችሁ?ገናኮ 3 ሰዓት ነው...ምን የሚያስቸኩል ነገር አለ?ገብተሽ አታበስይ ምናለሽ?"

"እሱስ አላበስልም...አከራዬ ደስ አይላቸውም እንጂ..."
"አአአአይ ...ለዛሬ የኪራይ ቤትሽን እርሻት...እዚሁ ቆንጆ room እይዝልሻለሁ" ሲልሽ መፍራት ትጀምሪያለሽ።

"ኧረረረረ አያስፈልግም ቤት እገባለሁ"ስትይ
"ለማንኛውም እየጠጣሽ "ይልሽና በተቀመጥሽበት ትቶሽ ወደ እንግዳ ተቀባዪአ ይሄዳል።ከቆይታ በሁዋላ አንድ ቁልፍ ይዞ ይመጣል።

"ምን...ባክሽ...' 'ሩሞቹ' ተይዘው አልቀዋል' አለችኝኮ...አይዞሽ double bed ነው የያዝኩት...መቼም የመሸበት አላሳድርም አትይም ሃሃሃሃሃ"
አሁን የምር...የምር...የምር ትፈሪያለሽ።ያቺ ተቆንጥጣ ያደገችዋ...ያቺ በዘመን ግሳንግስ ቀለሟን ያደበዘዝሽው አንቺነትሽ እየተፍገመገመች
"አምልጪ!...ተበላሽ! ትልሻለች።
"አአአአይ....ኧረ አትቸገር እዚሁ አካባቢ አንድ ጓደኛ አለችኝ እሷ ጋር እደውላለሁ..."
"ቆይ አላመንሽኝም ማለት ነው?ስታስቢው በጥብስና በቢራ የሴትን ገላ የምገዛ ርካሽ እመስላለሁ?I really feel sorry እንደዛ ካሰብሽኝ"
"ኧረ...እንደዛ ማለቴኮ አይደለም...አስቸገርኩህ ብዬ ነው እንጂ!እሺ በቃ" ትይውና

"እሳትና ጭድ አንድ ክፍል ውስጥ ያድሩ ዘንድ ደግ አይደለም...አንዳቸው የሌላቸው መጥፊያ ይሆናሉና " የሚለውን ቃል ጥሳችሁ አንድ ጣራ ስር ታድራላችሁ።

ጧት ለሰዓታት የተቃጠልሽበት ፀጉርሽ ፈርሶ...ጋኔል ያደረባት ጃርት መስለሽ ወደሰፈርሽ ትመለሻለሽ።ወደ መዳረሻሽ ገደማ ፋርማሲ ታይና ጎራ ትያለሽ።ሰው የተባለ ፍጡር ገና ከእናታቸው ማህፀን ሳሉ ጀምሮ የማያምኑት አከራይሽን ፋርማሲ ውስጥ ስታያቸው ልብሽ በአፍሽ ልትወጣ ትደርሳለች።በተጠራጣሪ አይኖቻቸው ከእግር እስከራስሽ አብጠርጥረው ያዩሽና
"አንች የኔ ዓለም የት ጠፍተሽ ነው ስታሸብሪን ያመሸሽ?"ይሉሻል።

"እንዴት አደሩ እትዬ?ማታ...ኮ አምሽቼ የምጨርሰው ስራ ኖሮኝ ሰዓት ስለሄደብኝ እንዳልረብሻችሁ ብዬ እዛው አድሬ ነው"

"ኧሯሯሯሯሯ!እና ስልኩ ቢከፈት ምን ይላል አደራሽ?...በዚህ በከፋ ዘመን እንደው ሰውስ ያስባል አይባልም?ጅብ በመውጫው አንችን ፍለጋ እንጉለሌ ልህድ?"

"ይቅርታ በጣም"

"የሆነው ሁኖ...ምን ልትገዥ ነው?"
ብለው እጅ ከፉ እንደተያዘ ሌባ ያፋጥጡሻል።

"እ...እንቅልፉ ነው መሰል ትንሽ ራሴን አሞኛል ማስታገሻ ልግዛ ብዬ"

"እህህህህም ነው?በይ...ደህና ዋይ"ብለውሽ ከፋርማሲው ሲወጡ የዘመናት ሀጥያትሽ የተፋቀልሽ ያህል ይቀልሽና "እፎፎፎፎፎፎይ!"ትያለሽ በሆድሽ።የምትገዥውን ገዝተሽ ስትወጪ አከራይሽ ፋርማሲው በር ላይ ቆመዋል።ስታያቸው ስቅቅ ብለሽ ታልፊያቸዋለሽ።ከማለፍሽ ወደ ፋርማሲው ድጋሚ ሲገቡ ታይና ጠጋ ብለሽ ለማየት ትሞክሪያለሽ።

"የኔ ዓለም...እንደው አሁን የወጣችቱ ልጅ የገዛችው ክኒና የምንድነው?" ይሉታል መድሀኒት ሻጩን።
2.2K viewsPapi, 17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 22:19:30
ሥዕል ለማሳል በ+251984740577
ወይም @gebriel_19 ላይ  ፎቶ  በመላክ በ ተመጣጣኝ ዋጋ  ማዘዝ ይችላሉ!


@seiloch
@seiloch
2.3K viewsLeul M., 19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-31 07:54:49 ከቤት ስወጣ የሚያጋጥመኝ ሶስት አይነት ሰው ነው። ሙሉ በሙሉ የነቃ (ሞቲቬሽናል ስፒች ሚሰማ መሰለኝ) ሙሉ በሙሉ ያልነቃ (ከምኔው ታክሲ ውስጠሰ ገብቼ ያቋረጥኩትን እንቅልፍ በቀጠልኩ የሚል) እና በከፊል የነቃ ሰው ይገኙበታል። በከፊል የነቃውን ኢዜማ ልትሉት ትችላላችሁ

ቅም አያቴ እስልምናን ከመቀበሉ በፊት መዳፍ ያነብ ነበር የሚል ታሪክ ሰምቻለሁ። እኔም የርሱ የልጅ ልጅ ልጅ ልጅ የሰው ፊት ማንበብ ቀኔን እጀምራለሁ።

ለታክሲ ከተሰለፉት ቁርሱን ቂንጬ የበላ ፣ ያደረ ሽሮ የበላና አሳር የበላን አብጠርጥሬ የመለየት ልዩ ተስጥኦ አለኝ። ከቤታቸው ፓንኬክ በልተው ሚወጡ ይኖሩ ይሆናል። የታክሲ ሰልፍ ላይ ግን አጋጥመውኝ አያውቁም።
ለአንድ ብጣሽ ቁርስ ወተት እንቁላል ዱቄት የሚያባክን ሰው ወይ መኪና አለው ወይ በራይድ ነው ሚንቀሳቀሰው። ድንገት ታክሲ ከተሰለፈ ይህንን ፅሁፍ እየፃፈ ነው

ጥሩ ቁርስ የጥሩ ቀን ማስጀመርያ ነው ይላል ኒቼ ኒቼ እንዲህ ያለ ነገር ይበል አይበል አላውቅም። ዮናስ ዘውዴ ይህንን ፖስት ካየው ግን ቀጣይ ብሔራዊ ቴአትር የሚዘጋጅ መድረክ ላይ ኒቼ እንዳለው ብሎ እንደሚጠቅሰው እርግጠኛ ነኝ

ሰው የሆዱን በዝምታ ቢሸሽግ ግንባሩን ግን በፍፁም መሸሸግ አይቻለውም። ለሊቱን አለሙን ሲቀጭ ያደረና በትራስ እጦት አንገቱ የተቀጨ መለየት ለኔ በጣም ቀላል ነው።
አንዲት ቆንጆ በአጠገባችን ስታልፍ ዞሮ ካላየ ወይ ባለቤቱ አጠገቡ አለች ወይም አንገቱ ተቀጭቷል። አለዚያ ሌላ ነገር እንድንጠረጥር እንገደዳለን።

መጠርጠር ስል ሰሞኑን ሀገር እንደሚበጠብጡ የተጠረጠሩ ሰዎች እየታሰሩ ነው ተብሏል። አሁንም ግን የዘራ በረሮ ሚሸጡ ሰዎችና ጌታ መጣልህ እያሉ ሚያስደነግጡን ሰዎች ከተማው ላይ በነፃነት እየተንቀሳቀሱ ነው።ከቴም ሰላም ማስከበር¡

ትላንት ስራ ውዬ በድካም ተርከም ተርከም እያልኩ አስፋልት ስሻገር በግብዳ ስፒከር "ጌታ እየመጣ ነው" ብሎ አንባረቁብኝ። በድንጋጤ መኪና ውስጥ ተወርውሬ ነበር። ጌታ ሳይመጣ እኔ ወደርሱ ሄጄ ነበር

የሆነው ሆኖ "ቡና ጠጥቶ ከቤት መውጣት የብልሆች መገለጫ ነው ይላል ኒቼ"

@wegoch
@wegoch
@paappii

By #Muaz jemal
4.6K viewsPapi, 04:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ