Get Mystery Box with random crypto!

ወግ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @wegoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 21.12K
የሰርጥ መግለጫ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @lula_al_greeko

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-04-03 10:48:43 ጠላ እየጠጣን ከጓደኞቼ ጋ ተሰባስበን እየቀደድን ሳለ ፦

ምድር ላይ የትኛውን ገጠመኝህን በይበልጥ ትወዳዋለህ የሚል ቀደዳ ጀመርን

ፍሬንድ ቀጠለ

"አንድ እለት እሁድ ጠዋት እናቴ ቡና እየጠጣች ፣ እየመከረችኝ ፣ እየመረቀችኝ ፣ እየሰደበችኝ ሳለ

በጣምምም ደስስ የሚልሽ ምን ብታገኝ ነው  አልኳት  አጠያየቄ ድንገት ነበር

ላሊበላ ፣  አክሱም ጽዮን ፣ ውቅሮ ማርያም ካዲ ብሄድ ደስ ይለኛል አለቺኝ

ፊቷ ላይ ያለው ምኞት የደስታ ዳር ይመስል ነበር።  ። በነጋታው ስጣደፍ ሄጄ ቢሮ አንድ መቶ ሺ ብር  ተበደርኩ ፍቃድ ወሰድኩ

ሎተሪ ደረሰኝ ብያት  ላሊበላ ፣  አክሱም ጽዮን ፣ ውቅሮ ማርያም ካዲ ወሰድኳት   ደስስ አላት ፀለየች  ፣ ለነዲያን መፀወተች ፣ እጄን ይዛ መረቀቺኝ ። 

ከዛ ከተመለስን በኋላ ሶስት ወርም አልቆየች ትንሽ አሞት ሞተችብኝ። ሳለቅስ ፣ ሳዝን ያፅናናኝ እና ያበረታኝ ህልሟን ማሳከቴ ነበር

ቀጠለ ሌላ ፍሬንድ ፦

"አንድ ቀን ክላስ ቀጥቼ ዩኒፎርሜን እንደለበስኩ  ጠላ ቤት ደቅ ብዬ አባቴ ከጓደኞቹ ጋር  ከች አለ ሳየው ስካሬ ጠፋ ።

ልጄ ነው ብሎ ለፍሬንዶቹ  አስዋወቀኝ ። ሃይለኛ ስለነበር እዛው ካልገደልኩ ይላል ብዬ ነበር። ምንም አላለኝም ። እንደውም የጠጣሁበትን ከነ ፍሬንዶቼ ከፈለልኝ ። ቀድሜው ወጣሁ ፦

አላመንኩትም የሚገድለኝን አገዳደል እያሰብኩ  ስፈራ ስቸር እቤት አምሽቼ ገባሁ ። እሱ ምንም አላለኝም ።

በሳምንቱ "ጋሻው ዛሬ ትምህርት የለህም አይደል "

"አዎ"
"በቃ ዛሬ አብረን እንዋል አለኝ" እሺ ብዬው የሚሰራበት
አብረን ሄድን

ውሎውን አዋለኝ ። የሆነ ህንፃ ይጠብቃል ፣ ህንፃው ጋ የሚቆም መኪና ይጠብቃል ፣ መኪና ያጥባል ።

የጠበቀበትን እና ያጠበበትን  ብር እንዲሰጡት ደጅ ይጠናል ፤ ትንሹም ትልቁም ይጠራዋል ፣ ያዙታል ያን ቀን አባቴ በጣም አሳዘነኝ

ከፊቱ ገሸሽ ብዬ አለቀስኩ

እንዴት እንደሚያሳድገኝ ያኔ ነው የገባኝ ። ምን እያለ እንደመከረኝ ፣ በእኔ ጉዳይ ለምን እንደሚናደድ ገባኝ

የዛ ቀን ህይወቴ ተቀየረ ።

ሌላ ፍሬንድ ቀጠለ ፦

"አንድ ቀን  እቃ ጠፍቶኝ ቤታችንን ሳምሰው
የታናሽ እህቴ ዲያሪ አገኘሁት በማላውቀው ምክንያት የማስሰውን ነገር ትቼ ደቅ ብዬ ማንበብ ስጀምር ።

ጥጋቤ ፣ ድፍረቴ እልሄ ተነፈሰ ። የግሩፕ ጠብ አጓጉል ውሎዬ ጣጣ  ለመጀመሪያ ጊዜ ገባኝ። ለመጀመሪያ ጊዜ መፍራት ጀመርኩ ፤ ለቤተሰባችን ምን ያህል እንደማስፈልግ ማስታወሻዋ ነገረኝ" 

ለካ አንዳንድ ቀን ብቻውን ዘመን  ያህላል !!

   by Adhanom Mitiku

@wegoch
@wegoch
@paappii
516 viewsDAVE / PAPI, 07:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 10:21:10 ይሉኝታ(ክፍል 2)

  ያገኘኝ ሁሉ ሲልከኝና ሲያዘኝ ውዬ የዛለ ሰውነቴን እየጎተትኩ ቤቴ እገባለሁ።እናቴ የቡና እቃዎቿን እያቀራረበች በመሀል ቀና እያለች ስታስተውለኝ ትቆይና

"አዋጥተው እንደገዙት መጋዣ ሲጭኑህ ይውላሉ አይደል?እንደው እምቢ አልፈጠረብህም አቡሽ?እምቢ አትልም?"

"ይረግሙኛል ብዬ ነውኮ"

"ኤዲያ!የረገሙህስ እንደው?አንድ ሳህን  ጤፍ ይገዙልህ መሰለህ?አዬ አለመታደል!እንዲህ እብን ሆነህ ትቀር?አድገሀልኮ ደስታ!18 ሞላህኮ!ልጅ አትባል ከንግዲህ"
ስትለኝ በመሀል አንድ ድምፅ አቋረጣት

"እንዴት ውላችሁዋል እናንተ?"እያሉ ወደውስጥ ዘለቁ እትየ አትጠገብ።እኚህን ሴትዮ ሳያቸው ያጥወለውለኛል።በነገር ሰው ሲወጉ ወደርም የላቸው።በቀደም ከመሸ ተልኬ ስወጣ ከማህሌት(የሰፈሬ ልጅ) ጋር ሱቅ ተገናኘንና የሆነ ያልሆነውን እያወራን ስንራመድ እትየ አትጠገብ በዛ ረጅም ቁመታቸው ሀውልት መስለው ከፊትለፊታችን ተገነጨሩ።ማህሌት ትከሻ ላይ ጣል ያረኩትን እጄን በፍጥነት አውርጄ ሰላምታ አቀረብኩላቸው።በውሉ ያልተሰማኝን ነገር አልጎምጉመው ሄዱ።በነጋታው ቤታችን መጡና

"እንዴት ውላችሁዋል ቤቶች?"አሉ በጎንዮሽ እያገረመረሙኝ።ወዲያው ወደኔ ዘወር አሉና

"ደስታ...ምነዋ ዛሬስ የጋሽ አለሙ ልጅ የት ሄዳ ነዋ?"አሉኝ።በአስማት እንዳደረቁኝ ሁላ ቀጥ ብዬ ቀረሁ።አባቴ

"ኧ?ደሞ የጋሽ አለሙ ልጅ እዚህ ምን ታረጋለች ?" ጥያቄአዊ አስተያየቱን እያነጣጠረብኝ።

"አብረው አያጠኑም እንዴት?ትናንት እዚህ አምሽታ ስትወጣ ያየሁዋት መስሎኝ"ብለው እርርርፍ!ምን ያልተመኘሁላቸው እርግማን አለ?ሙሴ በበትሩ ለድድ ሩብ ጉዳይ የሆነ ጥርሳቸውን ቢያረግፈው ደስታዬ! ኢያሱ ያቆማት ፀሀይ እንትናቸውን ለምች ትስጠው!ሌላ ክፉ አልመኝም!

"ኧረ ማታኮ ሱቅ ተገናኝተን እየሸኘሁዋት ነው ያዩን እዚህ አላመሸችም"አልኩኝ እየተርበተበትኩ።

እናቴ 'ለዚህም ደርሰሀላ?!'አይነት አስተያየት አየችኝ።እየተጎተቱ መጥተው የነገር መርዛቸውን አርከፍክፈውት ሄዱ።ከዛ ወዲህ ቤታችን ሲመጡ በጤና አይመስለኝም።እስኪወጡ ሱባኤ እይዛለሁ።ዛሬ ደግሞ ምን ሊሉኝ ነው እያልኩ ስብሰለሰል

"ደስታየ...ነገ ትምህርት አለህ?"አሉኝ።

ይቀጥላል

ማዕዶት ያየህ(ዘማርቆስ)
(gize_yayeh)

@wegoch
@wegoch
@paappii
603 viewsDAVE / PAPI, edited  07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 10:49:47 ይሉኝታ(ክፍል 1)


  እግዜሩ ያለ የሌለ አቅሙን ሙጥጥ አድርጎ የሰራውን ይሉኝታ ሁሉ የሆነ ጊዜ ላይ መሸከም ከብዶት ሳለ ወደ ቀራንዮ ጫፍ መስቀሉን ሲጎትት ቀረብ ብሎ እንዳገዘው ምስኪን እኔም ጠጋ ብዬ"አባት ሆይ! ይህን ሁሉ ይሉኝታ ብቻህን?ባይሆን ትንሽ ላግዝህ !"ብዬ ያንን ለምድር ለሰማይ የከበደ ይሉኝታ ተቀበልኩት።እሱም በይሉኝታ መቅረቤን አይቶ "ላለው ይጨመርለታል"በሚለው መርህ በእገዛ ሰበብ የተቀበልኩትን ይሉኝታ መልሶ ሳይወስድልኝ ቀረ።እነሆ እኔም ከዛ ወዲህ ትልቅ ትንሹ  ሲያሻው እንደ ስጋጃ እየረገጠ፣ሲፈልግ እንደማስቲካ እያላመጠ፣ባስ ካለም እንደ እንቧይ እያፈረጠ በይሉኝታዬ እኔው ላይ ዳንኪራውን ይመታል።

  "ልጅ ደስታ!እስቲ ና ወዲህ" ይሉኛል እማ አልጣሽ ከመንገዱ ጫፍ ወገባቸውን ይዘው ይቆሙና።

  እማ አልጣሽን ሳያቸው አስማተኛ አሮጊት ይመስሉኛል።በፈገግታቸው ተሸፍኖ ያለውን ከባድ ቁጣ ከእግዚአብሔር በላይ ሳልፈራው አልቀርም።እንደው አንዲት ነገር አዝዘውኝ እምቢ ብላቸው  ፈገግ ያለ ገፃቸውን በቅፅበት ክስክስ ያደርጉና በቅርባቸው ያለ ጭራሮ ቢጤ አንስተው ድግምት ነገር እያነበነቡ መሬቱን ጫር ጫር ቢያደርጉት ሽንቴን ልሸና ምናምኔን አውጥቼ ባንከፈረርኩበት እንደ እንጨት አድርቀው የሚያስቀሩኝ ይመስለኛል።ወይ ስፈራቸው!

  "አቤት እማ አልጣሽ" እላለሁ አጠገባቸው ስደርስ።

"ደስታየነህ...እንደው መቸም አንዴ ሲፈጥርህ የአሮጅትና የሽማግሌ መጫወቻ ሁን ብሎሀል...አንተም ጣድቅ ነህ መቸም አልታዘዝም አትልም...እንደው እሱ መድሀኔዓለም ምቀኛህን ውጋት ይዘዝበት!"

"አሜን እማማ"

"እንደው ያችን እላይ መንደር ያለችዋን አትጠገብን አወቅሀትም አይደል?"

"እትየ አትጠገብ የጋሽ ባህሩን ባለቤት አይደል?"

"እ...የባህሩ ምሽት!ሰልስትና እለታ ቸግሮኝ 50 ሳህኔ ማሽላ ተበድሬአት ነበር...አሁን የሻለቃ(ሻለቃ ማለት በደርግ ጊዜ በውትድርና ያገለግል የነበረ ባለቤታቸው ነው።)  ጡረታ ሲመጣ ሸምቸ መግባቴ ነው...ንስማ አድርሰህላት ና ጀታየነህ እመርቅሀለሁ"አሉኝ እግራቸው ስር በማዳበሪያ ታስሮ ወደተቀመጠው እህል እያዩ።የእትዬ አትጠገብን ቤት ርቀት ሳስብ ማዳበሪያው ገና ሳልሸከመው ደከመኝ።በመንገዴ የማገኛት ክፉ አቀበት ከጦሳ ተራራ ገዝፋ ብትታየኝም 'እምቢ' ግን አልልም።ይሉኝታዬን ለማን ሸጬው?

  እንደፈረደብኝ ያንን በግምት 65 ኪሎ የሚሆን ማዳበሪያ ተሸከምኩትና መንገዴን ጀመርኩ።እትየ አልጣሽ ከሁዋላዬ ሲመርቁኝ አልፎ አልፎም በሞኝነቴ ሙድ ቢጤ ሲይዙብኝ ይሰማኛል።

"ተባረክ ደስታየነህ ብሩክ ሁን!አሁን የማን ልጅ እሽ ብሎ ይታዘዛል በዚህ ዘመን?እድሜ ይስጥህ!ወገብህን ተውልቃት፣እጅህን ተቁርጥማት ይሰውርህ!"ይሉና ደሞ ድምፃቸውን ዝቅ አድርገው

"አይይይ እንደው መድሃኔዓለም!እንደው እንዲህ ማንም የሚጭነው አህያ ሆኖ ይቅር!ኧረ አህያስ ሲበዛባት ትለግማለች..." ሲሉ ከነሸክሜ ዞር ስል እንደገና ድምፃቸውን ሞቅ ያደርጉና

"እንጀራ ይውጣልህ ደስታየነህ!ምቀኛህን እግሩን ያልምሸው የኔ ዓለም!ውለህ ግባልኝ ክፉ አይንካህ!" ይሉኛል።

ይቀጥላል

ማዕዶት ያየህ

17/07/2015 ዓ.ም.

@wegoch
@wegoch
@paappii
751 viewsDAVE / PAPI, 07:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-21 06:47:38 ቃለመጠይቁ___

ጥያቄ: ሀገሪቷ ዳግም ኢጣሊያንን ያሸነፈችው መቼ ነው?

መልስ: ትግሉ ለአምስት አመታት እየተደረገ ቢቆይም በ1933 ዓ.ም. በድል ተደምድሟል።

ጥያቄ: በእዚህ ጦርነት ከፍተኛ ሚና የተጫወቱ ሰዎችን ስም ዝርዝር ጥቀስ?

መልስ: በሂደቱ ውስጥ በርካታ ሰዎች አስተዋጽኦ አድርገዋል። ስም መዘርዘር ከጀመርኩ አንዱን አንግሶ ሌላውን አንኳስሶ ይሆንብኛል።

ጥያቄ: ሙስና የሀገሪቱ ዋነኛ ጠላት ነው ብለህ ታስባለህ?

መልስ: ይሄንን ጉዳይ እያጣራ ያለ መንግስት ያቋቋመው ኮሚቴ አለ። ኮሚቴው የሚያወጣውን ሪፖርት ካየሁ በኋላ መልስ ልሰጥበት እችላለሁ።

ቃለመጠይቅ አድራጊዎቹ የሥራ አመልካቹ በሰጠው መልስ እጅግ በመርካትና በመደነቅ ውጤቱን ደጅ ሆኖ እንዲጠባበቅ እንዲሁም ለሌሎቹ የሥራ አመልካቾች ጥያቄዎቹን እንዳይነግራቸው አስጠንቅቀው አሰናበቱት።

••••

ወጣቱ የሥራ ተወዳዳሪ ከክፍሉ እንደወጣ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገባው አመልካች ምን ምን ጥያቄ እንዳቀረቡለት እንዲነግረው ይነዘንዘው ጀመር። ወጣቱም "ለቃለመጠይቅ አድራጊዎቹ ጥያቄውን ለሌላ አመልካች እንደማልናገር ቃል ገብቻለሁ።'" ሲል ይመልሳል።

ሌላኛው ተወዳዳሪ ጥቂት አሰብ ካደረገ በኋላ "እሺ መልሶቹን ነገረኝ?!" ብሎ ይጠይቀዋል።

ወጣቱም ቃለመጠይቅ አቅራቢዎች "ጥያቄዎቹን ለማንም እንዳትናገር!" ብቻ ብለው እንዳስጠነቀቁት በማስታወስ "መልሶቹን አትንገር አላሉኝም!" ብሎ ለእራሱ ካወራ በኋላ የመለሳቸውን ሶስት መልሶች ለሌላኛው አመልካች ይነግረዋል። የተነገረውም አመልካች መልሶቹን በልቦናው መዘገበ።

•••

ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ሁለተኛው አመልካች ለቃለመጠይቁ ወደ ውስጥ ተጠርቶ ገባ።

ጥያቄ: መቼ ነው የተወለድከው?

መልስ: ትግሉ ለአምስት አመታት እየተደረገ ቢቆይም በ1933 ዓ.ም. በድል ተጠናቅቋል።

ቃለመጠይቅ አድራጊዎች በመልሱ እንደተደናገሩ ወደ ሁለተኛው ጥያቄ ይሄዳሉ...

ጥያቄ: የአባትህ ስም ማን ይባላል?

ሙልስ: በሂደቱ ውስጥ በርካታ ሰዎች አስተዋጽኦ አድርገዋል። ስም መዘርዘር ከጀመርኩ አንዱን አንግሶ ሌላውን አንኳስሶ ይሆንብኛል።

ቃለመጠይቅ አድራጊዎቹ ግራ ተጋብተው..

"ያምሀል እንዴ ሰውዬ?!"

"ይሄንን ጉዳይ እያጣራ ያለ መንግስት ያቋቋመው ኮሚቴ አለ። ኮሚቴው የሚያወጣውን ሪፖርት ካየሁ በኋላ መልስ ልሰጥበት እችላለሁ!"
••••

ምንጭ: ድረገጽ


@wegoch
@wegoch
@paappii
1.1K viewsDAVE / PAPI, 03:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 09:02:24 ጃሃ
.
.
.
ፀሀፊ እንኳ አልነበርኩም... ነገር ግን ይሁዳነቴን አምኖ የሀጢያት ባልደረባዬ የሆነኝ ሰው ያጋራኝን ታሪክ እውነት እና ውሸትን ባንድ መደርደሪያ ላይ አስቀምጦ በግማሽ ብርጭቆ አረቄ ከሚጠፋ እኔነቴ መሀል ተራ ሰጥቼው ልሰድረው አልፈለኩም። እርግጥ ፊያሜታን በዓሉ የገለፃትን ግማሽ የአዳም ተባረኪን እሩብ ልገልፅለት አልችልም እንደ ዴዝዴሞናም እያጎን ፈጥሬ ኦቴሎዋን አላሳጣለት ይሆናል። ቢሆንም የልጅነት ልቤ የግጥም ዛሩ ወጥቶለት የቄሳርን ለቄሳር ግጥምን ለነበእውቀቱ ብሎ እንደ ጲላጦስ እጁን ታጥቦ ብዕር ጥሎ ሲጋራ ካነሳ  ከዓመታት በኋላ እህ ማለት አሰኘኝ። ......"እኔ ምልህ"አለኝ ሲጋራ አጫጫሴን በትኩረት ካየ በኋላ ሲጋራ ምን ያህል እንደምወድ ቢያውቅም ምክንያቴን ግን ጠይቆኝ አያውቅም እኔም መልስ አልነበረኝ።

"እኔ ምልህ የውሀ አይነት ስሜት ታወቃለህ?"
ማለት የተረጋጋ ማለትህ ነው? አልኩት
"NO መልክ የሌለው ይሄ ነው ልትለው የማትችለው ዓይነት"
"እኔንጃ እእእ....." ምን እንደምመልስለት እያሰላሰልኩ ወገቧ ላይ የደረሰችውን ትንባሆ አቀበልኩት ጨዋታችን እንዲቋረጥ አልፈለኩም ሲያወራ ደስ ይላል። ታሪኩ ያለፍኩበትን ያስታውሰኛል። ሀሳቡ ዞሬ ላላየው የማልኩትን ትናንቴን እንድቃኘው ደጀን ሆኖኝ ያውቃል።

"ስለሷ ሳስብ ውሀነት ነው የሚሰማኝ" አለ ሁለቴ ስቦ ሲጋራውን ቂጡ ጋር ካደረሰ በኋላ......."በማይታይ ውበት..በሚረብሽ ፀባይ....ሴትነት ባልጎላበት ለዛ የተደበቀ ውብ እና አሳዛኝ ነብስ እንዳላት የተረዳው ቀን ክርስቶስ ሳይመጣ ይሁዳን ለመሆን ለምን ቸኮልሽ? ልላት አስብና "ዋ ይሄን ግራ የገባው ወሬህን እዛው" የሚል መልሷ እንደሚከተለኝ ስለማውቅ መልሼ እተወዋለሁ ።ሁሌም እንዲ ናት ጥያቄው ካልገባት ወይም መመለስ ካልፈለገች ቁጣ ይቀናታል።እና ስለሷ ባሰብኩ ቁጥር ስሜቴ ውሀ ይሆንብኛል።
አንዳንዴ ወድጃቸው ከነበሩት ሴቶች ዝርዝር ውስጥ እፈልጋት እና ከግርጌ አካባቢ እንኳ ሳጣት ግራ እጋባለው።

እንደምጠላትም ማመን አልችልም። መቼም ማፍቀሬን በግላጭ አግኝታ ከእግር ጥፍሬ እስከ ራስ ፀጉሬ ያለተቀናቃኝ መጣ ከጣለችው ይሁዲት ጋር ላወዳድራት አልችልም። ብቻ ጎኗ ቆሜ አለው ማለት በከበባት ጦር መሀል ገብቶ መፎከር ያምረኛል። እንድትስቅ እፈልጋለው...ጥሎባት ደሞ አትስቅም ፈገግ ካለችም ከስንት አንዴ ነው። የልጅ ነፍስ አላት ..ንፁህ መዓዛ ያለው..የሚጣራ አይነት.......
ሳያት ይቀለኛል.. ለብ ባለ ውሀ ሻወር የመወሰድ አይነት የመታደስ ስሜት ይሰጠኛል። ለስላሳ ሙዚቃ የመስማት ያህል እርጋታ ይከበኛል በናት ጉያ ስር እንደመወሸቅ ያለ ድፍረት ማንም የማይደርስብኝ ያህል ልበሙሉ ሆናለው ።
ስሰማት የአለም እውነት ሁሉ ውሸት ይሆንና ሀቅ ከሷ ወዲያ ላሳር ስል እውላለው። የፍቄ ትረካና የጂጂ ዘፈን ለጆሮዬ ያስጠላኛል ። ማርያምን አልወዳትም!!! ማታ ስገባ አላልማትም ሳያት ልቤ ምቱን አይቀይርም አትናፍቀኝም ላያት አልራብም። ሳያት ግን በሰራችው የሾክ አጥር ስር ሾልኬ ማራኪ ነፍሷን ሳይ እውላለሁ እገረማለሁ እራሴን እረሳለሁ ...እጠፋለሁ አ.ይ.ገ.ባ.ት.ም እላለው... ከዚ የተሻለ ይገባታል... ያለችበትን ቦታ የከረመችበትን ህይወት ቃኘውት አዲስ አልሆነብኝም የኔ አለም ውሰጥ ያለች ይመስለኛል ..አይገባትም ነበር በፍፁም!! ...."
በመጨረሻ ቃሉ ማብቂያ ራሴን አሰብኩ ዘመን ወደ ኋላ መለሰኝ እሷን የኔን አሰብኳት ወዲያው አዲስ ሲጋራ ለኮሰ ።ተቀበልኩት አይገባውም ነበር.....
ምንአልባት የሚገባው ......

@ wegoch
979 viewsLeul Mekonnen, 06:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 08:55:29
Hiking to "Koremash", Menelik armory depot.

Hiking Date :- Mar 26, 2023 ( መጋቢት 17, 2015)

Departure:- Piyasa Tayitu Hotel

Departure Time - 1:00Am Local time

contribution per person:- 1100 ETB
      and for foreigners 25 dollar

Package

- Transportation
  Breakfast
  Bottled water
  Entrance with Guide
  Photograph
  Lunch

Activities:
trekking, historical place visitation,
  talent performance(if any) and fun game.

Suitable for:
medium
average fitness
average basic skill required

NB.
ID or Passport is Mandatory!

For more info join
channel @sunsethiking
@sunsetphotography

reservation @Gebriel_19  (0984740577 or 0926743929)
981 viewsLeul Mekonnen, 05:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 20:12:54
Hiking to "Koremash", Menelik armory depot.

Hiking Date :- Mar 26, 2023 ( መጋቢት 17, 2015)

Departure:- Piyasa Tayitu Hotel

Departure Time - 1:00Am Local time

contribution per person:- 1100 ETB
      and for foreigners 25 dollar

Package

- Transportation
  Breakfast
  Bottled water
  Entrance with Guide
  Photograph
  Lunch

Activities:
trekking, historical place visitation,
  talent performance(if any) and fun game.

Suitable for:
medium
average fitness
average basic skill required

NB.
ID or Passport is Mandatory!

For more info join
channel @sunsethiking
@sunsetphotography

reservation @Gebriel_19  (0984740577 or 0926743929)
1.1K viewsLeul Mekonnen, 17:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 23:22:06
እየተደገሰልህ ነው!!!

ሽር ጉድ ...ጉድ ጉድ...ጉድ ሽር

እንደ ገብስ ቆሎ ገባ ወጣ ያለ
ሱፍ የተጣለበት

ቀንህን ለማድመቅ ..ለማሞቅ ተነስተው

መሰሉህ??

እየደገሱልህ አሻሮ ባሻሮ
ጌሾ
የሙሾ ጠላ

ድግስስስስ ላዘን ጥንስስስስ ....
...........
Apr 21,2021
Ribka Sisay
..........
@ribkiphoto
229 viewsRibka Sisay, 20:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 21:39:14 ትዝታ ዘ Elementary (፰)
_____

ወ/ሮ መስከረም ወደ ክፍል ገባች! ... 'አርት' አስተማሪያችን (እድሜዋ በአንቺና አንቱ መሐል ሆኖ ተቸገርን!!) ... አጭር ወፈር ያሉ ሴትዮ ናቸው! ... አጭር ሰው ነገረኛ ነው ይባላል! እሳቸውም የተለዩ አይደሉም! ... በየሳምንቱ አዳዲስ የግርፋት አይነት ያስተዋውቃሉ። ... ግርፊያው በደረጃ የተደለደለ ነው፣ አርት ደብተር ረስቶ/ትቶ የመጣ፣ የተሰጠ የቤት ስራ ያልሰራ፣ እያስተማረች የሳቀ/ች፣ እያስተማረች ያወራ እያለ በቅደም ተከተል ይወርዳል! ...

ዛሬ እኔና ዮሐንስ አርት ደብተር ይዘን አልመጣንም! ... ከግርፋት እንዴት እንደምናመልጥ ከሰልፍ ላይ ጀምሮ እያውጠነጠንን፣ እየተከራከርን ነው የቆየነው! ... በስተመጨረሻ ተስማማን- "አሞናል ብለን እንውጣ" !! ...

⨳⨳

«አርት ደብተራችሁን አውጡ !!»
ክፍሉ ተንኮሻኮሸ ... ተማሪው ደብተሩን እያወጣ ጠረጴዛው ላይ ይዘረጋል! ...
እኔና ዮሐንስ ትወናችንን ልንጀምር ነው! ...
«ያላመጣችሁ ኑ ውጡ!»
ትወናችን ተጀምሯል ...
ዮሐንስ ጠረጴዛው ላይ ተኛ! ... እኔ ከዳሁት! ... ወ/ሮ መስከረም በሁለቱ መደዳ መሐል ሆነው ነው የሚያረጋግጡት ከፊት ወደኋላ ከመሄዳቸው በፊት ጎን ለጎን ያሉትን ቼክ ያደርጋሉ! ... ሀሳቡ ብልጭ ያለለኝ ድንገት ነው (ዮሐንስ ይቅር በለኝ!!) ... ወ/ሮ መስከረም ከኛ ፊት የሚቀመጡትን ዴስክ ቼክ አድርጋ ከጎን ወዳሉት ስትዞር ቼክ ተደርገው ከታለፉት ተማሪዎች ደብተር ተቀበልኩና ፊቴ ዘረጋሁት ! ...

⨳⨳

አሁን እኛ ጋር ደርሳለች!
«ተነስ አንተ ውሪ!» ዮሐንስን ነው!
ዝም ጭጭ! ወይ ፍንክች!
«ምናባቱ ሆኖ ነው?!» ጥያቄው ለኔ ነው ...
«አሞት ነው!»
«አሁን ነው ከቅድም ጀምሮ?»
«ከቅድም ጀምሮ!»
መምህሯ ዮሐንስን መነቅነቅ ጀመሩ ...
«ተነስ! ደብተርህን አሳይና ተኛ!»
አዪዪ! ... አይሁንልህ የተባለ ልጅ!
ዮሐንስ ሆዬ ወይ ፍንክች! ...
«ተነስ ነግሬሃለሁ! ... ተኝተህ ሞተሃል!»
ዮሐንስ ተነሳ ... ፊቱን አጨፍግጎ ዓይኑን እያሸ ነው ...
«ደብተርህን አውጣ!»
አሁንም ዓይኑን እያሸ ነው ...
«እስከወዲያኛው ሳላጋድምህ ደብተርህን አውጣ!»
የዮሐንስ "እንቅልፍ" ብን ብሎ ጠፋ! ...
«አ....ላ...መ...ጣ...»
ዷዷ! ... ቿቿ! ...ጯጯጯጯ! ...

@wegoch
@wegoch
@paappii

By abdu s aman
595 viewsDAVE / PAPI, 18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 19:16:56 .....
ይህ ቀን ግን እንደተለመዱት ቀናት አይሆንም።

መነሻህ ለይ ስራዎችህን ሰዎች እንዲረዱትና ትኩረት እንዲሰጡት ትሻለህ፤ ቢያበረቱህ፣ ቢያደንቁህ፣ ከጎንህ ቢቆሙ ምነኛ በወደድክ ግን የነገሮች መልክ ሌላ ነው። ሲደክምህ ከማንም ምንም መጠበቅ ታቆምና የተለመደው ስራህን ትቀጥላለህ ብዙ አንድ አይነት ቀናት በአንድ መልክ ያልፋሉ። ከብዙ ቀናት መካከል ግን በሆነችዋ ቀን ነገሮች ይለዋወጣሉ፤ ይህቺ ቀን ላንተ የቀደመውን ተግባርህን የምትፈፅምባት የተለመደች እለት ለሰዎች ግን አንተን አጥርተው የሚያዩባት ልዩ ቀን። ድንገት ሰዎች ለአንተ ትኩረት መስጠት፣ ስራዎችህን ማድነቅ፣ ማሞገስና ማክበር ይጀምራሉ ትደነግጣለህ!
"ልክ እንደተለመደው እኮ ነው" ማለት ይቃጣሀል ግን ለፈጣሪ ስራውን የሚሰራባት ቀን ናትና ለብዙ የትላንት የድካም ቀናቶችህ በዚች አንዲት እለት እጥፍ ድርብ አድርጎ ይክስሀል፤ በዝምታ የሆነውን ሁሉ ትቀበላለህ።

ይህ ቀን ግን እንደተለመዱት ቀናት አይሆንም።

ላደረከው ክፋት ምላሹ ዝምታ ሲሆን ልብህ እየደነደነ ይመጣል፤ የቀድሞ "ምን ይመጣብኝ ይሆን?" የሚለው ፍርሀትህ "ማን ምን ያመጣል?" ወደሚለው ድፍረት ይሸጋገራል ክፋትን በትንሽ ትንሹ ትለማመዳለህ። ለስራህ በጩኽት ይቀጣህ የነበረው ህሊናህ ልክ ምንም ያላደረክ ይመስል ዝም ይልሀል፤ እናም ልክ ካንተ በላይ ሰው ከምድር በላይ ገዢ የሌለ ይመስል ትታበያለህ። የተለመደውን በደል በምትፈፅምባት አንዲት ቀን ግን ፈጣሪ የስራህን ሁሉ ማብቂያ ያደርገዋል።
እንደ ተራራ የገዘፈው እንደ ሰናፍጭ ያልታየህን ቁልል ባልጠበከው ጊዜና ቦታ ይንደዋል፤ በራስህ የክፋት ካብ ፍራሽ ስር ምንምና ማንም ሆነህ ትቀራለህ፤ ይህ ቀን እንደተለመዱት ቀናት አይሆንም።

የፈጣሪ አንዲት እለት አንተ በጠበከው ጊዜና ቦታ አትመጣም የተለየ ፅድቅ ወይ የተለየ ክፋት ባልሰራህባት በአንዷ ቀን ግን የስራህ ሁሉ ማጣፊያ ይሆናል።

ፈጣሪም ሰውም ያላየህ ሲመስልህ ልብህን ከቶ አይክፋው በመልካም ጎዳናህ ለይ ሆነህ በዝምታ አምላክህን ጠብቀው።

ፈጣሪም ሰውም ያላየህ ሲመስልህ በክፋት ጎዳናህ ለይ በማን አለብኝነት እንዳሻህ አትረማመድ አይደለም ቆሞ መሄድ አጎንብሶ እንኳን ምህረት ማግኘት  ለታደሉት ብቻ ይሆን ይሆናል።
ለክፋትህም ልክ አበጅለት ምክንያቱም ይህ ቀን እንደተለመዱት ቀናት አይሆንም።

@wegoch
@wegoch
@wegoch

By mahlet
1.0K viewsDAVE / PAPI, 16:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ