Get Mystery Box with random crypto!

ወግ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @wegoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 21.12K
የሰርጥ መግለጫ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @lula_al_greeko

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-05-28 11:14:53 iPhone ባይኖርህ iPhone ያለው ጓደኛ ይኑርህ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

  "መልክ ይስጠኝ እንጂ ሙያ ከጎረቤት እማራለሁ" ትላለች እናቴ።

"Snapchat ይኑር እንጂ ሙያ ከጎረቤት እማራለሁ" ዘመን ላይ ሳንደርስ በፊት።ዕድሜ ለካሜራ ጥራትና ለSnapchat እኔና መሰል መልከጥፉአውያን መልክን ትተን ስለሙያ መጨነቅ ከጀመርን ቆየን!በቀደም አንዷ የሰፈሬ ልጅ ቴሌግራሟ ላይ የለጠፈችውን ፎቶዋን አይቼ ጉድ ብዬ አልበቃኝ አለ!ሳውቃትኮ ትል ያላመጠው ቲማቲም ነው ምትመስለው!እንዲያውም የአፍንጫዋን ትልቅነት በተመለከተ እናቷ ወ/ሮ አበሩ ሲቀልዱባት

  "ዝንጀር እስቲ ወጡን አሽትችና ጨውን ንገሪኝ" ይሏታል።ሰፈር ውስጥ ሁሉም "ዝንጀር" ነው የሚላት...ዕውነተኛ ስሟ "ጤና"እስኪረሳ ድረስ!ታዲያ ዝንጀር ዩኒቨርስቲ ስትገባ አጎቷ ከካናዳ IPhone ላከላት።በሄደች በሳምንቷ "ለእታባ አሳይልኝ"ብላ ጊቢ የተነሳቻቸውን ፎቶዎቿን በቴሌግራም ላከችልኝ።

  ወ/ሮ አበሩ ስልኬን እያገላበጡ ፎቶውን አዩትና

  "ሚጡ...የዝንጀርን ፎቶ አምጭው እንጅ"
  "ይኸው ዝንጀር ናትኮ"
   "ክይ!ቅማላም!...መሀይም ነኝ እንጅ መቀለጃ ነኝ?"
   "ኧረ ማርያምን አበርዬ!ይኸ ባለፈው የገዙላት ቲሸርት አይደል እንዴ?"
   "የት ገብቶ ነው ያ ለምቦጭ?ያ ሁላ ቡግር ምን ዋጠው?"
   "አገሩ ተመችቷት ይሆናላ"
   "በሳምንት?እኔ መልኳ መለስ ቢል ብየ በየሳምንቱ የቅቤ ስቀፈቅፍ ኖሬ እዛ ኸዳ በሳምንት ይኸን ያህል ወዝ?ይች በልቶ ካጅ!""

ዝንጀር ለእረፍት ስትመጣ በስልኳ የተወሰኑ ፎቶዎች አስቀረሁና ፌስቡኬ ላይ ለጠፍኩ።ከዚህ ቀደም ለፎቶዎቼ የተሰጡኝን አስተያየቶች መለስ ብዬ ቃኘሁ።

  ጥሎብኝ አንድ መፅሀፍ ባነበብኩ ቁጥር ከመፅሃፉ ጋር ፎቶ ተነስቶ የመለጠፍ ልምድ አለኝ።''የኢትዮጵያ ታሪክ ከኖኅ እስከ ኢህአዴግ"ከሚለው መፅሐፍ ጋር ፀጉሬን አጎፍሬ ለተነሳሁት ፎቶ አንዱ ተንከሲስ እንዲህ የሚል አስተያየት አስቀምጦልኛል።

  "የ77ቱ ድርቅ መልክ ቢኖረው አንቺን ይመስላል።ዘቅዝቄ እንደ መጥረጊያ ብጠቀምሽ ጉራንጉሩ ሁላ አይቀርሽም ስታፀጅው።"

ዝቅ ብሎ ደግሞ ሌላኛው

   "አንቀፅ 39 ፊት!ፊትሽ የመገንጠል ስሜቴን ቀሰቀሰው!ከኢትዮጵያ ውጣ ውጣ የሚለኝ መጣ!" ብሎኛል።ወረድ ስል ደግሞ

  "ፀሀዩ ከሮ ጥላ ተወዶ ፊት!ፊትሽ ህልም ይመስላል...አይቼው ልጮህም አማረኝ ልሮጥም አማረኝ ግን አልቻልኩም...ፍቺና ወይ አስፈቺና ገላግይን አቦ!" ሌላው ደግሞ

"ይኸን ግንባር ይዘሽ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብትሄጂ የራስሽ ክልል ይኖርሽ ነበር!"

  ከኔ ፎቶ በላይ 'ኮመንቶቹ' ናቸው ላይክ ያገኙት።በዝንጀር iPhone ታሪክ ሳይቀየር በፊት...ከአሁኖቹ "ኮመንቶች" በጥቂቱ

   "ፍንጭትሽ ደስ ስትል...ካንቺ ፍንጭት ከኔ ዲምፕል 'ሼር' አርገን ለምን አንዲት ቆንጅዬ ልጅ አንወልድም?"

  "ዓይኖችሽ  አንድነት ፓርክን ያክላሉ።ፍቀጂልኝና ሰልፊ ልነሳባቸው"
   
  

ወይ iPhone ወይ iPhone ያለው ጓደኛ ይኑርህ!

ማዕዶት ያየህ(ዘማርቆስ)
(
@gize_yayeh)

15/09/2015 ዓ.ም.


@wegoch
@wegoch
@paappii
4.8K viewsPapi, 08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-24 12:29:15 #ለወንዶች_ብቻ

ይኸውልህ።

ዋቴ ብልጽግና በሳይንስ ሳይሆን በጥንቁልናና በትንቢት የሚያስተዳድራት አገር በአምስት አመት ውስጥ 1.5 ትሪልዮን ዶላር የጦርነት ኪሳራ አምጥታ፣ አሁን አለም ላይ የሌለ 107% Hyperinflation ውስጥ ገብታ ሕዝቦቿን በኑሮ ውድነት እየለበለበች፣ በ15 ቢልዮን ዶላር ቅንጡ ቤተ መንግስት ትሰራለች። ላቲንም በለው ኤዥያ፣ አፍሪቃም ጭምር - Developing Countries የተሰኙ አዳጊ አገራት ውስጥ ቅንጡ ቤተ መንግስት አይሰራም፤ ድሃ ናቸዋ!

ስማ ስማ።

በቀጣይ ሁለት አመታት ኑሮ ከዚህ በላይ ይወደዳል። Anarchy ይሰፍናል። ደሞዝህ ከወር እስከ ወር ስለማያደርስህ ከሚስትህ ጋራ ትጣላለህ፣ ትዳርህ ይበጠበጣል። ''አላቅልሽም አብቃቂ'' እያልክ በየቀኑ ልትጨቃጨቅ ነው። እሷም ''ብሩን ጠጣህበት፣ ተዝናናህበት'' ብላ ልትበጠብጥህ ነው።

መፍትሄውን እንካ።

1 - ቆጥብ፣ ወጪህን በ60% ቀንስ። ስለ Minimalism አንብብ። ከካናዳዊው የF.I.R.E አቀንቃኝ Mr Money Mustache፣ ስለ ችጋራም አኗኗር እና ስለ Early Retirement የጻፋቸውን ከጉግል አጥና።

-

2 - ዝም ብለህ ውለታ አትዋል። ቢሮክራሲ አትቀንስ፣ መረጃ በነፃ አታቀብል። ኮሚሽን ጠይቅ። ደልል። አስከፍል። ክፈሉ ለማለት አትፈር። ሰው ሁሉ አስከፍሎ ነው ቀላልና ከባድ ጉዳይ የሚያሳልጠው።

-

3 - ስረቅ። አጭበርብር። ጉቦ ተቀበል። የእጅ ውረዱ ማለትን ተለማመድ። ስራ ላይ በኔትዎርክ ተደራጅተህ ስረቅ። (አትመፃደቅ - የብልጽግና መንግስት የሱን ብሔር ሰዎች ሰብስቦ ዝረፉ ብሎ ሲያሰማራ አንተ ጨዋ ጨዋ ከሰራህ ተግጠህ ታልቃታለህ)

-

4 - ውጪ አገር ወንድም፣ እህት፣ ጓደኛ ካለህ - ''ገንዘብ ካልላክልኝ ሁለተኛ እንዳትደውል'' በለው። ዳያስፖራ ጨለል ነው፣ ቀውሶች ናቸው። ብቸኝነት ሲያገረጣቸው በየሳምንቱ ይደውሉልህ እና ስለ ኑሮ ውድነት ጠይቀውህ ራሳቸውን ያጽናናሉ። አስር ብር ግን አይፈለጡም።

''ስንቴ ልንገርህ፣ ደህና ገንዘብ፣ ወይንም ወሳኝ እቃ ካልላክልኝ ሁለተኛ አትደውል፣ ቢዚ ነኝ'' ብለህ ጆሮው ላይ ዝጋበት።

-

5 - ቅጥረኛ አትሁን። ደሞዝተኛ አትሁን። በጠዋት ወጥቶ የታክሲ ወረፋ ተሰልፎ፣ ሙሉ ቀን ሰርቶ፣ የአለቃን Expectations አሟልቶ፣ በወር መጨረሻ የተመታ ደሞዝ መቀበል #ያደነዝዛል። #ዶማ ያደርጋል። . . .ስራ ለቅቄስ? አትበለኝ። እሱማ ለራሴ ሰዎች የተያዘ ሚስጥር ነው፤ አልነግርህም።

-

ብቻ ይሄንን ጥሬ ሐቅ ልብ በል - በእነዚህ ሰዎች የስልጣን ዘመን እዚህ አገር ላይ ጠንክሮ መስራት #ያደኸያል።

-

አትፍዘዝ፣
ታመጣለህ መዘዝ!

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Eyob mihretab
5.3K viewsPapi, 09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-23 21:45:03 ...
ዝም ያለ መልክ ረጋ ያለ ሰውነት ያስደነግጣል?
ለምን እንደምደነግጥ እኮ ነው ያልገባኝ።
ልክ ሳየው ልቤ ምቱን ያፈጥነዋል፤ እጆቼ መንቀጥቀጥ ፊቴ መቅላት ይጀምራል። አይኖቼን ምን ለይ እንደማሳርፍ እንዴት ማውራት እንዳለብኝ ግራ እጋባለው። መንገድ ለይ ከሆንኩ ደግሞ ልክ ገና ከቤት እንደወጣ ሰው እግሬ ይማታብኛል፤ አየር ለይ የምረግጥ ይመስል እወላከፋለው። ስለ ራሴ የነበረኝ መረዳት ሚዛኑን ይስትና ፊቴ ለይ ያለች ትንሽዬ ነጥብ ትታየው ይሆን ብዬ ስጨነቅ ራሴን አገኘዋለው።

አይንን ያዝ በሚያደርግ መልኩ አይደለም አይኖቼን አስሮ ያቆያቸው፤ አንደበተ-ርትዑነቱም አይደለም ሲያወራ በሰማሁት የሚያሰኘኝ፤ በሩቅ በሚታየው ሞገሱም አይደለም ልቤን ሲያርደው የሚውለው።

እዩኝ በሚሉ መልኮች መሀል ነው የሱን ዝም ያለ ውበት ያየሁት፤ ከብዙ ተናጋሪዎች መሀል ገኖ ነው የሱ አድማጭነት እልፍ የሚያስወራኝ እልፍ የሚያፅፈኝ። ስክነት ያለው ህይወቱ ነው በሺህ ችኩል በሺህ ጥድፊያ መሀል ሁሉን አደብዝዞ እሱን ብቻ የሚያስመለክተኝ። የእውነቱን ኑሮ ነው ኑረቱን እንድወድለት ያስገደደኝ።

ያወራኝ እለት ቃላት ብቻ አልነበረም ከአንደበቱ የሰማሁት፤ ዝም ቢል እንኳን ብዙ መናገር የሚችል ገፅ ተችሮታል። እሱ ሲያወራ ስረታ እሱ ሲናገር ስርድ ይታወቀኛል። መቼ አምኜ መቼ እንደተቀበልኩት መቼስ ልቤን አሳልፌ እንደሰጠው እንጃ። ግን ከነበርኩበት ሁካታና ጥድፊያ አውጥቶ ሲያሰክነኝ ይሰማኛል። ዘመንን ማዘዝ ይችል ይመስል እሱ ጋር ስሆን የረሳሁት ሰላም የረሳሁት ፀጥታ በእርጋታ ከሚፈስ ጊዜ ጋር ዙሪያዬን ይከበኛል። ሰው ለመማረክ አለኝ የሚለውን የማንነት መልክ ይዞ ከውድድር አይሰለፍም ይልቁንስ ባለበት ይቆያል እንጂ። ከራሱ ጋር፤ የታይታ ካልሆነው ገዢ ስብዕናው ጋር።
እናም ሚዛን ልኬቱን ማጣት ይጀምራል። ከተናገሩት ሁሉ ይልቅ እሱ ይደመጣል፤ ከታዩት ሁሉ ይልቅ አይን ለማረፊያው እሱን ይናፍቃል፤ ከተገዳደሩት ሁሉ ይልቅ እሱ ሳይታገል ይጥላል። በቀደዱለት አይፈስም ነገር ግን በዙሪያው ያለውን ሁሉ ይዞ ወደ እራሱ መንገድ መሻገር ይቻለዋል።

"ይሄ ሰው ማንነው?" ያሰኘኛል፤ ማንነው? የጊዜው ኑረት እንዲህ የሚገላበጥለት። ማንስ ነው? ብቻውን ኑሮ በብዙ ሚረታው። እንዴት ሆኖለት ነው ሲያደምጥ መሰማት ሲመለከት ማውራት ለሱ የተቻለው። እንዴት ብረዳው እንዴት ቢገባኝ ነው ሚዛኔን በእሱ ተክቼ ሰው የማገዝፈው ከልኬት ማወረደው። ምኔን ቢያገኘው ምኔን ቢነካው ነው ዛሬ ገና መኖር የጀመርኩ ይመስል እጆቹ ካልያዙኝ የምንገዳገደው።

በዚህ ልክ የራስ ሰው በዚህ ልክ አዋቂ በዚህ ልክ አስተዋይ... ይሄ ሰው ማነው?

@wegoch
@wegoch
@paappii

By mahi
4.1K viewsPapi, 18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-23 18:45:53 ከተበሉስ አይቀር በጎጃም ቡዳ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

   ጎጃሜ ነኝ።ያውም ማርቆሴ!የበላይ ዛር የሚያክለፈልፈኝ!እናላችሁ አምና እናት ከተማ ማርቆስን ለቅቄ ለአስኳላ ወደባህር   አዝግሜ ኖሮ ጠሀዩ ልብ ልቤን ሲጠብሰኝ ጊዜ በሳምንቴ ተመልሼ ወደማርቆስ!

  "ኧግ 'የኢንበርስቲ' ተማሪ!ይኸ ነው እንግዲህ ?በሳምንት ምላሽ ሆነ?"ኮብራ ምላሷ ጎረቤታችን ስንቴ ናት የምትለክፈኝ።

"የረሳሁዋቸው እቃዎች ስላሉ ትምህርት ሳይጀመር ልውሰዳቸው ብዬ ነው።''
  ''ነው?እምምምምም" ከንፈሯን አጣማ ትታኝ ሄደች።ከስንቴ ጋር ስሆን የETV ዜና ሳይቀር ይናፍቀኛል።የመሰለ ገ/ሕይወት ለንቦጭ ሁላ ውል ይልብኛል።ከያዘች አትፈታማ!ጥቃቅን ማብራሪያን ፍለጋ ልብህን እንደ ሎሊ ፖፕ ትጠባዋለች ነው 'ምልህ!!

አሁን በቀደም ዕለት ሱሪ ለብሼ የማላውቀው እኔ ቬል ሱሪዬን ወትፌ ስመናቀር አገኘችኝና

"ኧሯ!ሚጡ...ሱሪ ሲያምርብሽ አንቺ!"

"አመሰግናለሁ ...ያው የጊቢ ተማሪ እንምሰል ብለን ነው!"

"ኧራ!ልበሽ ኧረ!ለማናባቱ ብለሽ ደሞ!ይወጭቀው!ስንት ገዝተሽው ነው?"አለችኝ ሱሪዬን ቀለሙ እስኪለቅ እያየች።

"ቀላል ነው...950 "

"ዘጠኝ ከአምሳይ?ሸጋ ነው አንች!ተየት ነው የገዛሽው?ተአዲሱ ገበያ ነው?"

"አዎ ከዛው ነው"

"አምሮብሻል ነጋ ይሙት!ተንግዲህ ቀሚስ እንዳትለብሽ እንዲያውም...እና..."አቋረጥኳት

"በይ እሺ ሰላም ዋይ ስንቴ ጓደኞቼ እየጠበቁኝ ነው""ብያት ሄድኩ።'እህ ብዬ ከሰማሁዋት የገዛሁበትን ቀንና ሰዓት...ያጋዛኝን ሰው...የሸጠልኝን ሰው ...የልብሱን ብራንድ...መጠየቋ አይቀርም።ደሞ 'አምሮብሻል' ይባልልኛል!( ሰፈር ውስጥ "እናንተ!ያች የወለላ ልጅ ተበላሽታ አይል!ያችን የዶሮ ኩላሊት እምታክል ቂጧን በሱሪ ወትፋ ስትሞላፈጥ አይቻት..."እንደምትል መች ጠፍቶኝ?ዶሮ ኩላሊት ባይኖራት ራሱ የኔን ቅጥነት ለማጉላት ሲሆን እነስንቴ ቤት አላት)

የረሳሁዋቸውን እቃዎች ሸክፌ ወደ ባህርዳር ከተመለስኩ በሁዋላ ከዶርም ጓደኞቼ ጋር ብዙ ጊዜ እሰጥ አገባ ውስጥ የሚከተን ነገር ነበር።"ጎጃሜ ቡዳ ነው " የሚሏት ነገር!

"ጎጃሜ ቡዳ ነው
ብለሽ ያወራሽው
ሰው ሰውን ሲበላ
የታባሽ አየሽው?"  ከአፌ የማይጠፋ ግጥም ሆነ። በጨዋታችን መሀል አቦሰም ጥለን ዕድሉ የኔ ከሆነ "ድሮስ ጎጃሜ!"ይላሉ አፋቸውን ሸርመም አድርገው።ነገሮች በአንድም በሌላም መንገድ የዕድል ገፃቸው ወደኔ ከዞረ "ጎጃሜ አይደለች?"የሚሉት ጥቂት አይደሉም።አንዱማ እንዲያውም የሆነ ቀን  'ላማክርሽ እፈልጋለሁ'ብሎ በቁምነገር ቀጠረኝና ተገናኘን።

"እየውልሽ ጊዜ...እእ...እንትን ነው"
"ምን?"
"የሆነች ልጅ ወድጄ..."
"ኧረ?ማናት?"
"አታውቂአትም"
"እና አናግረሀታል?"
"ለሱ ነውኮ የፈለኩሽ"
"እንዳናግርልህ?"
"ኧረ በንግግር የሚገባት አይደለችም ልጅቱ"
"እና ምን ላርግልህ?"
"ያ...ው...ጎጃሜ አይደለሽ?እናንተኮ እዚህ ነገር ላይ አትታሙም...መ...ስተፋቅር እንድትሰሪልኝ ወይ እንድታሰሪልኝ ነበር" ብሎኝ እርርርርርፍ!
     ከዚህም ከዚያም የጎጄን ቡዳነት ሲደጋግሙብኝ መገንፈሉን እየተውኩ እኔው ራሴ በራሴ መቀለድ ጀመርኩ።

"ጎጃሜ ቡዳ ነው
  ብለሽ ያወራሽው
  ሰውን ሰው ሲበላው
  የታባሽ አየሽው ?"

እል የነበርኩት ልጅ

"ቡዳ ነው ይሉታል
  ጎጃምን በሙሉ
መች ጣዕሙ ሊታወቅ
ሰው ይዘው ካልበሉ"  ማለት ጀመርኩ።በሊታን መምረጥ ቢቻል ከተበሉስ አይቀር በጎጃም ቡዳ!ፍቅር ነዋ ምትለፈልፈው!!

  ማዕዶት ያየህ(ዘማርቆስ)
(
@gize_yayeh)

15/09/2015 ዓ.ም.


@wegoch
@wegoch
@paappii
3.9K viewsPapi, 15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-22 21:27:09 ማንም በኬኔዲ እንዳይመጣብኝ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

   ኬኔዲ መንገሻን እንዴት እንደምወደውና ስስ ጎኔ መሆኑን ያወቁ አጠገቤ ሙዚቃውን ይከፍታሉ ።ተለክፌበት ነው መሰለኝ ድምፁን ከሰማሁ ጠላቴ ቤትም ሳልገባ አልቀርም።ለምን ቤተመንግስት አይሆንም?

  እና ኬኔዲን በተመለከተ የዛሬ ሁለት አመት ገደማ ያጋጠመኝ ትዝ አለኝ።ከቤታችን ጀርባ አንድ ፅድት ያለ ጊቢ ለብቻው ተከራይቶ የሚኖር የቅቤ ነጋዴ ነበር።ስሙን ቄስ ይጥራውና ቅዱስ ነበር ስሙ።

  ዘውትር ወደትምህርት ቤት ስሄድ ቪትዙን በአጠገቤ እያራመደ(ቪትዝ የያዘ ሰው እግረኛ ነው ሚመስለኝ ተርቱብኝ ከፈለጋችሁ)

"ሄይ ቆንጆ" ይለኛል የሚያኝከውን ማስቲካ እስከ ሮቡዕ ገበያ እያስጮኸ።

"እንዴት አደርክ ቅዱስ?"

"አለሁልሽ...'ወደክላስ' ነሻ?ልሸኝሻ!"

"ውይ በጣም አመሰግናለሁ...ጓደኛዬ እየጠበቀችኝ ነው።"

"ታዲያ ምን ችግር አለው?ልሸኛችሁአ...ደውይላት" እንደማይተወኝ ሳውቅ ለጓደኛዬ ደወልኩ።ከቤት ትምህርት ቤት ያለው መንገድ በህይወቴ እንደዚያ ቀን ረዝሞቦኝ የሚያውቅም አይመስለኝም።ንግግሩ...ቀልዱ...ሳቁ...ወላ አተነፋፈሱ ይኮሰኩሳል።የሆነ parasite አንጀቴ ውስጥ የሚላወስ እስኪመስለኝ ነው ያቅለሸለሸኝ።

"ይገርማችሁዋል በጣም ሰቃይ ተማሪ ነበርኩ።ግን ከልጅነቴ ጀምሮ እኛ ኢትዮጵያውያን ቅቤ ላይ ያለን inspiration እንዳስደነቀኝ ነው።ቅቤ መነገድ አብሮኝ ያደገ ህልሜ ነበር..."አላለም?ቅርድድ!ማትሪክን 1.2 አምጥቶ ከትምህርት ጋር መቆራረጡን ያልሰማን መስሎት!

"By the way Gize...you is very talented...why not singing to me?"ሲል ትምህርት ቤታችን በር ላይ መድረሱን አላስተዋለም ነበር።RIP English!

  ከቀናት በሁዋላ  እንዲሁ ወደትምህርት ቤቴ ሳዘግም ከአጠገቤ ሲደርስ ቪትዙን አቁሞ

  "ሃይ ጊዜ"አለኝ።
ፀጉሩን እንደ ኬኔዲ መንገሻ ተቆርጧል።የሱን የሚመስል ሸሚዝ...ሱሪ...ጫማ...ከመኪናዋ ሙዚቃ ማጫወቻ የኬኔዲ ሙዚቃ ይንቆረቆራል።

  "ተው አአትከልክሏት
   ታንኳኳው በሬን
   ገብቷት ከመጣች
    ወዳ መውደዴን
    .........................
   እንደ ዱር ዝንጀሮ
    ጫካ እንደለመደ
   ቤት መግባት ይጠላል
    እሷን የወደደ..."

ቪትዙ ማርቼዲስ ሆና ታየችኝ ብላችሁስ?ከምኔው መኪና ውስጥ እንደገባሁና ክፍል ገብቼ እንደተቀመጥኩ አላውቅም።ብቻ የኒውተንን ህጎች እየተማርኩ ጭንቅላቴ ላይ የሚያቃጭል ዜማ ነበር።

"...ትዝብት ነው እቴ ትዝብት ነው
    ትዝብት ነው እቴ ትዝብት ነው
    ወዳጅ ከዞረ ፊቱ
     ከጨከነ አንጀቱ...."

በኬኔዲ አትምጡብኝ!

ማዕዶት ያየህ (ዘማርቆስ)
(
@gize_yayeh)
14/09/2015 ዓ.ም.


@wegoch
@wegoch
@paappii
3.4K viewsPapi, 18:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 17:13:31
#Sunsethiking is hosting a Fun day hike to "Abaye lake and hot spring"

Hiking Date :- May 28, 2021 (ግንቦት 20).

Hiking #Cost:-  1800 ETB only

Departure: Piasa (Taitu Hotel)

Departure Time - 12:00 Am LT

    Package includes
  Transportation
  Bottled water
  Guide + scout
photography 
  Breakfast
  lunch

NB.

ID/ PASSPORT Mandatory!

walking hour:  3-5 hour (up to 12 km of walking)

suitable for: Medium, some basic skill required

for more join the
channel @sunsethiking
@sunsetphotography

tickets available at
      @Ribki ( +251926743929)
      @Gebriel_19 (+251984740577)
1.2K viewsLeul Mekonnen, 14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 08:29:07 አክስቴን እንዴት ፖለቲከኛ እንዳደረጉብኝ
።።።።።፡።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ጊቢያችን በሰጠን የ9ቀን  እረፍት ምን እንደምሰራበት ሳቅድ 5ኛው ቀን ላይ ደረስኩ...ያለ ቁምነገር!ወይ አላነበብኩ...ወይ ወግ ቢጤ አልሞነጨርኩ...ወይ ስካርፌን ጠምጥሜና ፀጉሬን አጎፍሬ የተነሳሁትን የአብዮተኛ ገጣሚት ፎቶ ፌስቡኬ ላይ አልለጠፍኩ...ብቻ የሆነ ቀን አክስቴ ዓይኔ ላይ ውል ስትልብኝ ተነሳሁና ቤቷ ሄድኩ።

"ቅንጭር ከየት ተገኘሽ?" አለችኝ።ከሲታነቴን ስታጋንን ነው "ቅንጭር"የምትለኝ።

"እታባ ደግሞ!እይ እስቲ እንዴት እንደወፈርኩ...ባህርዳርኮ ተመችቶኛል" ሰው ከሲታነቴን ሲነግረኝ ደሜ ነው ሚፈላው።

"አየሁት እቴ!ጣውላ ቂጥ!ምንሽ ነው የወፈረው?ያው የተላገ ጣውላ እንደመሰልሽ ነው!እንደው በምስክር ሞት ምናል ደህና ደህና ነገር ብትበይ?"

"ማነው ደግሞ ምስክር?"

"ምስክር ነዋ!"

"እኮ አላወቅሁትም"

"አይ እንግዲህ!አላወቅሁትም አይባልም አላወቅነውም ነው 'ሚባለው" ብላኝ እርፍ።ከመቀመጤ ሪሞቷን ቀሰረችና የጦፈ የፓለቲካ ክርክር ያለበትን ጣቢያ መርጣ ተደላድላ መከታተል ጀመረች።

"እታባ ኧረ ቀይሪው በማርያም!"

"ዝም በይ!ጁንታ!ምን ታውቂያለሽ ስለሀገር?ዝፈኝ አይበሉሽ እንጂ!"

"መቼስ ከሞት ዜና ዘፈን ይሻላል"

"እዬዬም ሲደላ ነው ቅንጭር!አታድርቂኝ !እዚሁ ደፍቼሽ መቃብርሽ ላይ ችግኝ እንዳልተክል!"

(ምንድነው ያስነኩብኝ ይችን ሴትዮ?ጊቢ ልሄድ ስል ልትቆርብ እያኮበኮበች አልነበር?ማነው የፖለቲካ ጋኔል ያስመታብኝ? )

"እታባ ቆረብሽ አይደል?"

"ሲኖዶሱን ከፍለውት በየት በኩል?"( ምንም ብጠይቅ መልሷ ውስጥ ፖለቲካ አለ)
ወዲያው  4ዓመት የሞላው የልጅ ልጇ(የአክስቴ ልጅ) ወዲህ ወዲያ እያለ ሲጫወት ድመታቸው ላይ ቆመባትና አስጮሀት ።አክስቴ ብስጭት ብላ አምባረቀችበት

"የ20ሚሊየኑ  ባስ እላይህ ላይ ይውጣ!አፍርጠህ ትገድላት?" ለደቂቃዎች ክርክሩን ስትከታተል ቆየችና

"ቅንጭር...ጥሩ ቀን መጣሽ...ያች እምትወጃት አለችልሽ ሂጅ አቅርቢና ብይ"አለችኝ።መኮረኒ በአትክልቴን እየበላሁ ቤቱ ግድግዳ ላይ የተለጠፉትን አዳዲስ ምስሎች መታዘብ ጀመርኩ።ከፊት ለፊት ያለው ግድግዳ ላይ የዘመነ ካሴን ምስል ከነ ንግግሩ የያዘ መጠነኛ ባነር ተሰቅሏል።ከዓመት በፊት እዚሁ ግድግዳ ላይ የመድሃኔዓለም ስዕለ-አድህኖ ተሰቅሎ እንደነበር ትዝ አለኝና ደነገጥኩ።የቀኝ ግድግዳው ላይ የቀድሞው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ምስል ተሰቅሏል።ከምስሉ በታች ያለውን ፅሁፍ ሳነብ ነው አክስቴ እንደለየላት የገባኝ።

"ባሏን ብታይ ውሽማዋን ጠላች ሆኖብኝ ነው ስትሞት ስለት ማስገባቴ!እሱ ቸሩ መድሃኔዓለም ነፍስህን በገነት ያኑራት!
                                     ያንተው ወይንሸት "


ወደሌላኛው ግድግዳ ስዞር አንድ ሱፍ ያጠለቀ ሰው  "ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኢትዮጵያ ነን" ከሚለው ንግግሩ ጋር ተዘቅዝቆ ተሰቅሏል።

"እታባ ይሄን ሁሉ አንቺ ነሽ የለጠፍሽው?"

"ኋላስ ማን ሊለጥፈው ኖሯል!ግድግዳ ኬኛ!"

"በይ ደህና እደሪ ልሂድ"

"ልሂድ አይባልም ...እንሂድ ነው ሚባለው ቅንጭር"

( )

ማዕዶት ያየህ(ዘማርቆስ)
(@gize_yayeh)

10/09/2015 ዓ.ም.

@wegoch
@wegoch
@wegoch
1.7K viewsPa[pi, 05:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 08:19:33 ዝንቁል
።።።።።።

ከአያቴ ስድቦች ሁሉ ግንባሬ ላይ የተለጠፈ እስኪመስለኝ ሳስበው የሚያሳፍረኝ ስድብ ነው...ዝንቁል!ከሆነ ጊዜ በሁዋላ ከስድብነት ወደ ቅፅል ስምነት ተቀየረና ሳልወድ "አቤት" የምልበት መጠሪያዬ ሆኖ አረፈው።

"ዝንቁል ነይ አያ ከባዱ መጧል ሰላም በይው"ትለኛለች የምወደው አጎቴ ሲመጣ።
"ምነው እማ ስንቄ ካልጠፋ ስም?"ይላል አጎቴ እየሳቀ።ሰው ስሜን ሰምቶ ሲስቅ ለጉድ ነው 'ምሸማቀቀው!አንገቴን ወደ መሬት ትክል!በተለይ አጎቴ ከሳቀ!
"ምን ላርጋት እህ ብልጠት ያልሰራባትን!ነክሮ የተዋትን ከባድሰው!እንደው ፍርጃ ነውኮ እናንተየ!ሰው እንዴት በአስራ አምስት አመቱ እሳትና ውሀ አይለይም?ወይ አንች የአብማይቱ አታሳይኝ የለሽ!"ትላለች ሞኝነቴን ስታጎላ።በእርግጥ ሱቅ ስላክ ባለሱቆቹ ይከስራሉ ብዬ ስለማስብ መልስ አልቀበልም ብዬ አልቅሼ አውቃለሁ...አልክድም አምና አያቴ ለእንግዳ ሰርታ ያስቀመጠችውን ድንች ወጥ አሙቂ ያለችኝ ጊዜ እንዲጣፍጥላትና እንድትመሰገን ብዬ ብርጭቆ ሙሉ ስኳር ጨምሬበታለሁ።

"የሆነስ እንደሆን ስሙ ተዋህዷት አለቅጥ ቂል ያረጋታል እንጂ ምን ይበጃታል እማ ስንቄ?"ይሄኔ የእማ ስንቄ ቀይ መብራት ይበራል።ርዕስ ታስቀይራለች።በስሜ አልያም በጅልነቴ ዙሪያ ምክር ወይ አስተያየት ቢጤ ሊሰጧት ከቃጡ መስሚያዋ ጥጥ ነው።

"አንተ ከባዱ...እንደው ያች በቅሎህ ተሻላት አደራህ?"ትላለች የዝንቁልነቴን መዝገብ ትከድንና።እሷ ለመጣ ለሄደው የሞኝነቴን ነገር ተናግራ አልታክታት ቢልም እኔ ግን መስማቱ መረረኝና አንድ ቀን እንዲህ አልኳት።

"እማ ስንቄ"

"ኧ!ስንቋ አለቀኮ ብያለሁ እችን የቋቁቻም ዘር!እሰሰይ!የቆሎ ጓደኛዋ መሰልኳት?"

"ሁለተኛ ዝንቁል እንዳትይኝ!እናቴ ያወጣችልኝ ወርቅ የሆነ ስም አለኝ!ማንጠግቦሽ በይኝ"

"የጠገበ አህያ ይውጣብሽና ያላልኩሽ እንደሁ ትመችኝ?" አኩርፌ ወደውስጥ ስገባ የጎረቤታችንን የእማ ዝማምን ድምፅ ሰማሁ።ዘውትር  እየተጨናበሱ የሚመጡት እሳት ሊጭሩ ነው...የምጭርላቸው እኔ ብሆንም ...የአያቴ ጥሪ ተከተለ

"ዝንቁል ነይ ለዝማም እሳት ጫሪላት"

ማዕዶት ያየህ(ዘማርቆስ)
(
@gize_yayeh)

08/09/2015 ዓ.ም.


@wegoch
@wegoch
@paappii
708 viewsDAVE / PAPI, 05:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 23:43:24
#Sunsethiking is hosting a Fun day hike to "Abaye lake and hot spring"

Hiking Date :- May 28, 2021 (ግንቦት 20).

Hiking #Cost:-  1800 ETB only

Departure: Piasa (Taitu Hotel)

Departure Time - 12:00 Am LT

    Package includes
  Transportation
  Bottled water
  Guide + scout
photography 
  Breakfast
  lunch

NB.

ID/ PASSPORT Mandatory!

walking hour:  3-5 hour (up to 12 km of walking)

suitable for: Medium, some basic skill required

for more join the
channel @sunsethiking
@sunsetphotography

tickets available at
      @Ribki ( +251926743929)
@Gebriel_19 (+251984740577)
1.3K viewsRibka Sisay, 20:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 12:32:14
#BOOKNOW
Hiking #outdoor #photography

Hiking to the majestic Mt. #Eerer with #Sunset Family.

Hiking Date :- May 7, 2023 (ሚያዝያ 29, 2015)

Hiking Cost #1400 ETB only

Departure: Taitu Hotel (Piyassa)

Departure Time - 12:00 LT

   
ID Card/Passport/Driving License is mandatory!

Brought to you by
    #Sunset_Hiking_Team

for more join the
channel @sunsethiking

@sunsetphotography

tickets available at
               @Ribki / +251926743959
              @Gebriel_19 / +251984740577
976 viewsRibka Sisay, 09:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ