Get Mystery Box with random crypto!

ወግ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @wegoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 21.12K
የሰርጥ መግለጫ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @lula_al_greeko

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-05-01 07:22:18
ሥዕል ለማሳል በ+251984740577
ወይም @gebriel_19 ላይ  ፎቶ  በመላክ በ ተመጣጣኝ ዋጋ  ማዘዝ ይችላሉ!


@seiloch
@seiloch
1.7K viewsLeul M., 04:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 12:50:52 ድቅድቁ መሀል ያሉ ፋኖሶች
(ካሊድ አቅሉ)

የቦሌ መድሃኒያለም ቤተክርስትያንን አጥር ይዤ ቁልቁል አዘግማለው ፀሀይዋ እየሸሸች ለምሽት ምድርን ልታስረክብ ሽር ጉድ እያለች ነው ። የቤተክርስትያኑ አስተምሮት ለመስማት በጉዞዬ መሀል ጆሮዬን ለባለ ግርማ ሙገስ ድምፅ ባለቤት አባት ሰጠው " እውነተኛ  ደግ ጎተራው ሞላ አልሞላ እንብላ ብሎ ለምስኪን የቤቱን በር በሰፊው ሚከፍት ነው ። በሩን ዘግቶ አቅሉን እስኪስት ከተመገበ ብሃላ የከመረው መብል አላልቅ ሲለው ካደረማ ይበላሻል ለምስኪን እንስጠው ያሉት ደግ ነን ለማለት ሲዳዳቸው ይታያል ፤ ሞኞች ምስኪኑማ ተርቦ በራቹ ላይ እያለ ከርችማቹ መለሳቹት እኮ ያለ ሰዓቱ የመጣ ፈውስ ይባስ ቁስሉን ያመረቅዘዋል ። በጥሙ ሰዓት ያልደረሰ ውሃ ህይወቱ ካጣ ብሃላ እንደ ወንዝ ብታዘንቡለት አስክሬኑን ከማጠብያነት ውጪ ምን መላ ፈይዶ ? ስትሰጡ ኪሳቹ እስኪሞላ አትጠብቁ 'የመቅዶንያ ሰዎች ካላቸው ጥልቅ ድህነት ላይ ይሰጣሉ ' ይልም የለ ቃሉ"


ከመቅደሱ  ስለ ደግነት ሚማርክ ትምህርት ሲሻገር የኔዋ ደግ ባለቤቴ ፌቴ ላይ ድቅን አለችብኝ ሁሉን ነገርዋን ተቆጣጠረች ድግነትዋን ግን እንዴት ፋታ ትስጠው እጅዋ እና ልብዋ በምንም ቢከረቸሙ ከመከፈት አይታቀቡም ልግስና የመኖርዋ ዋስትና ነው ካልሰጠች የመኖርዋ ትርጉም ይጠፋታል ። አስተነፋፈስዋ ሚስተካከለው በቻለችው አቅም ክንድዋን ስትዘረጋ ነው ውይ ታድላ የነደደው ማፍቀሬ ላይ ቤንዝል አርከፈከፈችበት ቸርነትዋ አንገበገበኝ ከሷ ሌላ ማሰብ ተሳነኝ ። አንዳንድ ሰው አለ ደግሞ ክፉ ሰው እራሱ ደግ ሚለው ፍጥረተ አለሙን ሚያነቃቃ በመራር ከማጣፈጥ አልፎ ድባቡን በሙላ ሚቀይር አፍንጫችንን ይዘን በምንሄድበት መንገድ "ውይ ደስ የሚል ሽታ " ብለን የጠላነውን መንገድ በፍቅር ደጋግመን እንድንመላለስ ሚያረጉን እህቶች, አባቶች , እናት ,አክስት , ጓደኛ ጎረቤት ወዘተ . . . . .  አሉ አበቃልን ብለን የቁም ሞት ሊወርሰን ሲሰናዳ ከመንጋጋው ሚያድኑን . . . ህይወትን በእንባ ብቻ እንዳንከትባት የሳቅን ዙፋን ይዘው ከተፍ ሚሉልን ጭንቅን መውጫ መሰላሎች ድቅድቁ መሃል ያሉ ፋኖሶች  . . . . ።

~    ~    ~   ~   ~

@wegoch
@wegoch
@wegoch
2.1K viewsDAVE / PAPI, 09:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 22:14:19
Hiking #outdoor #photography

Hiking to the majestic Mt. #Eerer with #Sunset Family.

Hiking Date :- May 7, 2023 (ሚያዝያ 29, 2013)

Hiking Cost #1400 ETB only

Departure: Taitu Hotel (Piyassa)

Departure Time - 12:00 LT

    Package includes

  Transportation
Lunch
  Bottled water
  Guide
photography 
  Snack
  So Much Fun
NB.

ID Card/Passport/Driving License is mandatory!

Brought to you by
    #Sunset_Hiking_Team

for more join the
channel @sunsethiking

@sunsetphotography

tickets available at
               @Ribki / +251926743959
              @Gebriel_19 / +251984740577
2.8K viewsRibka Sisay, 19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 16:30:04 ከሚያነበው መጽሐፍ ገጽ ውስጥ የሰርግ ወሬ ሲነፍስበት ላፍታ ንባቡን ገታ አድርጎ፤ ሶፋ ላይ ተደላድላ ስልክ ላይ ያፈጠጠችውን ልጁን አያት። የእድሜዋ መናር አሳሰበው። ደግሶ ድሮ የመመረቅ እና የመጎረር፣ የመደነቅ ስሜት በአምሮት ናጠው።

"ለምን ነው ፍቅረኛ ይዘሽ ወደ ትዳር ጎዳና ማትራመጂው? እስከመቼ እንዲሁ በዋል ፈሰስ ትባክኛለሽ?" አላት።

ዐይኗን ከስልኳ ሳትነቅል "መች አለና" የሚል መልስ አሽቀነጠረች።

"ምኑ?"

"ፍቅርም፣ ሁነኛ ፍቅረኛም"

መልሷ ከነከነው። ህልምን ፈርቶ እንዴት ከመተኛት ያፈገፍጋል ሰው? "ፍቅር ላንቺ ምንድን ነው?"

"ክርስቶስ"

መልሷ ግማሽ ልቡን ሀሴት አጠጣው፤ ግን ድፍን መልስ አይወድም። "አብራሪው!"

"በቃ ለሚወዱት ሰው እስከሞት ድረስ ታምኖ መጓዝ፤ ያውም ያለማፈግፈግ፣ አሁን ያለው ወንዱም ሴቱም ታምኖ ሚሄደው ተቃቅፎ የልቡን እስኪያደርስ፤ ስጋውን እስኪያስደስት፣ ኪሱን እስክታልብ ነው። ስሜት እና ብልጠት እንጂ ፍቅር የለም አባ" ምርር አለች።

"ምን ያህል የፍቅር ሰው ነኝ ትያለሽ? ፍቅርንስ በገለጽሽው መንገድ ለመኖር ምን ያህል ዝግጁ ነሽ?"

ጨነቃት!
መልስ ከውስጧ ተሰለበ።
ዝም አለች!
ዝምታዋን ታክካ ራሷን መመርመር ያዘች።

#ኤልዳን
by @eldan29

@wegoch
@wegoch
@paappii
2.7K viewsDAVE / PAPI, 13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 07:02:00 ለመሆኑ ለትዳር እንዴት ተመራረጣችሁ? ሲባሉ

“ያው አስተሳሰቡ
ህልሙ
እውኑ
ምናምን የሌለ ተመቸኝ።" ብለው ያዝጉሃል።

ይቺ መልስ ግን deep inside የምርጫ ቅስቀሳ እንደሆነች ሁላችንም እናውቃታለን።

እርግጠኛ አደለሁም
ብቻ 2009 ላይ ይመስለኛል
አዲስ አበባ ውስጥ ለፍርድ ቤት ከቀረቡ ክሶች መካከል ከ57 በመቶ በላይ የሚሆኑት የፍቺ መሆናቸውን አስታውሳለሁ። ጊዜው ስለረዘመ ቁጥሩ ላይ ስህተት ልፈጥር እችላለሁ

አንዳንዴ የተጋነነ impression ይዞ ወደ ትዳር መግባት የማታ የማታ የሚያመጣው መዘዝ ይህ ነው አይባልም።

በቀደም አንድ ጓደኛየን ልጠይቀው ቤቱ ሄጄ ነበር።
ሚስቱ አንድ የሚንቦራች ልጅ እየጠበቀች የቤተሰብ ጨዋታን ስታይ ደረስኩ።

ባልሽ የለም እንዴ?

ፊቷን ሀዘን እየመተረው ፈልፈላውን እያሳየችኝ
"እሱ 'ኮ ነው።”

ምን ተፈጥሮ ነው?

“በቃ ነጋ ስጭኝ ነው!
ጠባ ስጭኝ ነው!
ምግብ ላቀርብ ጎንበስ ካልኩ ዘሎ ጉብ ነው!
ተው ብለው አልሰማኝ አለ።
አሁን እንደምታየው ነው እየመነመነ እየመነመነ እየመነመነ ሄዶ የትልቁ ልጃችንን እኩያ መስሎ አረፈው። እስኪ አንተ ፍረደኝ አሁን ይሄ ባል ነው መጥገር?"

አናደደኝ
ገላመጥኩት
እዛው ሚስቱ ክንድ ላይ ሽጉጥ እንዳለ
"ካቹፓራ ሳያት አያስችለኝም” አለኝ

በሌላ ቀን ደግሞ
ሚስቱ ደጅ ላይ ኩርሲ ላይ ተቀምጣ አንድ አራስ ራቁቱን ጭኗ ላይ አስተኝታ ሰውነቱን በቅባት እያሸች ፀሀይ ታሞቀዋለች።

ባልሽስ?

እንባዋ ዠደደደደ እያለ ጭኗ ላይ የተኛውን አራስ ቂጡን ቸብ ቸብ አደረገችው

ባሏ ነበር
አደነጋገጤ

ባል ቀና ብሎ የእንጀራ እናቱን እየጠባ
ምን አለኝ?

“ጉጉጋጋ”

እንባየ ደርሶ ግጥም አለ

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Tamiru temesgen
3.3K viewsDAVE / PAPI, 04:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 22:24:56 አባቴ እናዝናለን ፡ ካሁን በኋላ በምድር ላይ የሚቆዩት ግፋ ቢል ለስድስት ወራት ያህል ነው ።
........

እኚህ በምስሉ ላይ የሚታዩት አባት  Stamatis Moraitis የሚባሉ በወጣትነት ዘመናቸው ሀገራቸው ግሪክን በወታደርነት ያገለገሉ ሰው ናቸው ።
እና በአንድ ወቅት ልጆቻቸውን እና የልጅ ልጆቻቸውን ለመጎብኘት በሄዱበት አሜሪካ ትንሽ ህመም ይሰማቸውና ወደ ሆስፒታል ይሄዳሉ ።
ሀኪሙ  ግሪካዊውን ሰው በተለያየ አይነት የህክምና ዘዴ ከመረመረ በኋላ ፡ ሰውየው በማይድን የሳንባ ካንሰር እንደተያዙና ፡ ካሁን በኋላ በህይወት የሚቆዩት ለስድስት ወራት እንደሆነ ነገራቸው ።  የዶክተሩን  የምርመራ ውጤት ካዩ በኋላም ዘጠኝ አባላት ያሉት የዶክተሮች ቡድን ፡ ስለውጤቱ ትክክለኛነት ፈረሙበት ።

ይህን የሰሙት ሚስተር Stamatis አዘኑ ፡ ወደልጆቻቸው ቤት ከተመለሱ በኋላም መርዶውን ነግረዋቸው ተያይዘው ተላቀሱ ።
እንግዲህማ ወደ ሀገሬ ግሪክ ልሂድ ፡ ሞቴ እዛ ይሁን ቀብሬም  አባት አያቶቼ ባረፉበት ቦታ ይፈፀማል በማለት ፡ ከጥቂት ቀናት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገራቸው ግሪክ ተመለሱ ።

Stamatis Moraitis ወደ ግሪክ ከተመለሱ በኋላ ምንም እንኳን ከስድስት ወራት በኋላ እንደሚሞቱ ፡ በአስር ሀኪሞች የተፈረመ ፡ ወረቀት ቢይዙም ፡ ለወትሮ ከሚሰሩት ስራ አልታቀቡም ።
በህይወታቸው ውስጥ የተከሰተ ምንም አይነት ለውጥ እንደሌለ ቆጥረው ፡ እንደድሮው አትክልቶቻቸውን ይንከባከባሉ ፡ ወራት ለቀረው እድሜ ፡ ለመድረስ አመታትን የሚፈልጉ ፍራፍሬዎች ይተክላሉ ፡

እንዲህ እንዲህ እያሉ ፡ ሳይታወቅ ያቺ የቀጠሮ ወር ደረሰችና ፡ ለመሞት ቀናትን  መቁጠር ጀመሩ ። ግን  ምንም የለም ። ሰውነታቸው ደክሞ ከዛሬ ነገ ድንገት እወድቅ ይሆን እያሉ በስጋት በመጠባበቅም  ፡ ስድስት ወሩን አለፉት ።
ሰባተኛ ወር ገባ ። ምንም የለም ።
አመት አለፈ ። ሰውየው ጭራሽ ንቁና ብርቱ መሆን ጀመሩ ። ሁለት ሶስት አመት አለፈ ። እንዲህ እንዲህ እያለ ፡ አስር አመት ሆናቸው እንደውም  ፡ በፊት አልፎ አልፎ ይሰማቸው የነበረው የህመም ስሜት ራሱ ጠፋ ።

እናም በአስረኛ አመታቸው ፡ ልጆቻቸውና ፡ የልጅ ልጆቻቸው ወደ ሚኖሩበት አሜሪካ ሄደው ሊያዩዋቸው ፈለጉና ወደዛ ተጓዙ ።
ካሁን አሁን መርዶ እንሰማ ይሆን ብለው ለአመታት የጠበቁት ዘመዶቻቸው ጋር በአካል ተገናኙ ።
...........
ከቀናት ቆይታ በኋላ ፡ ከዛሬ አስር አመትበፊት ፡ ለመሞት ስድስት ወራት ብቻ እንደሚቀራቸው የነገሯቸው ዶክተሮች ያሉበት ሆስፒታል ሄደው ሰላም ሊሏቸው በዛውም አስሩም ዶክተሮች የፈረሙበትን ወረቀት ለዶክተሮቹ  ሊያሳዩዋቸው ያዙና ወደ ሆስፒታሉ ሄዱ ።
ነገር ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ፡ አንድም ዶክተር ማግኘት አልቻሉም ። ሁሉም ሀኪሞች በተለያየ ጊዜ በህመም አልፈዋል ።
......
ግሪካዊው Stamatis Moraitis ከአስር አመታት በፊት ይህን ምርመራ ሲያደርጉ የስልሳ አመት አዛውንት ነበሩ ። እና ይሞታሉ ከተባሉ በኋላ ለሌላ ለ42 አመታት በህይወት ኖረው ፡ በ102 አመታቸው ከጥቂት አመታት በፊት አልፈዋል ።
.............
ጥያቄው  አስር ዶክተር ፈረመ ?  ሳይሆን ፡  ከላይ ተፈርሟል ወይ ነው  ።

@wegoch
@wegoch
@wegoch

By wasihun
316 viewsDAVE / PAPI, 19:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 13:18:22 ውርስ!
•••
ቅርንጫፌ ውስጥ ካሉ ቆጣቢ ደንበኞች መካከል ትልቅ ተቀማጭ ገንዘብ ያለው ደንበኛ ነው። በየጊዜው የሚያስቀምጠው ገንዘብ ሲጨምር እንጂ ሲቀንስ አይቼ አላውቅም። ታታሪ ሰራተኛ፣ ባተሌ እንደሆነ ገንዘብ ሊያስገባ ለብሶት የሚመጣው የቆሸሸ የሥራ ቱታ ምስክር ነው። አንድ ትልቅ ጋራዥ እንዳለው አጫውቶኛል።
ለተወሰኑ ወራት ዐይቼው ስለማላውቅ አሳስቦኝ ስልኩ ላይ በተደጋጋሚ ስደውል ስልኩ አይሰራም።
                             *
አንድ ቀን ጠዋት አዳፋ፣ ለሐዘን ቀለም የተነከረ ነጠላ የለበሱ፣  እጅግ የተጎሳቆሉ እናትና ፊቷ በማድያት የጠቆረ ሴት ከእኔ ቀድመው ቢሮ ጠበቁኝ።
ወንበሬ ላይ ተደላድዬ እንደተቀመጥሁ የፍርድ ቤት የውርስ ውሳኔ እንዲሁም ከባንኩ ዋናው መሥሪያ ቤት የህግ መምሪያ የተሰጠ አስተያየትና የባንክ ደብተር አቀበሉኝ። የባንክ ደብተሩን ስገልጸው ከታታሪው ደንበኛዬ ፎቶ ጋር ተፋጠጥኩ።
"ምን ሆኖ ነው?!"
"ሥራ ቦታ አደጋ ደርሶበት አረፈ ልጄ!" አሉኝ - አሮጊቷ።
የሰማሁትን ለማመን አልቻልኩም። እጅግ ደነገጥሁ። የፍርድ ቤት ውሳኔውን አነበብኩት የውርስ ውሳኔው በቅርንጫፋችን ያለው ገንዘብ ለእናቱና ለእህቱ እንዲካፈል የሚያዝዝ ነው። እንዲህ የተጎሳቆሉት ሴት በእርግጥም የእዚያ የባተሌ፣ የእዚያ በየሳምንቱ በብዙ ሺህ ብሮች ሂሳቡ ላይ የሚያስገባ፣ የእዚያ ሚሊዮን ብሮች ሒሳቡ ላይ ያጠራቀመው ደንበኛዬ እናት መሆናቸው እጅግ ገረመኝ።
"እግዚአብሔር ያጽናዎ እናቴ! ነፍስ ይማር! እጅግ የማከብረው ደንበኛዬ ነበር። እጅግ ታታሪ ሰው ነበር። ስልኩ ላይ ደጋግሜ ስደውል የማይነሳው ለካ ለእዛ ነበር ለካ?! ወይኔ ወንድሜ!" አልኋቸው።
"ይኸው እንዲህ ጥሎ ለሚሞተው ገንዘብ 'ሥራ፣ ሥራ!' ሲል የት ወደቅሽ ሳይለኝ፣ ታምሜ ሳይጠይቀኝ፣ ቁራሽ ተቸግሬ ሳይረዳኝ፣ እህቱን ሳይረዳ፣ የዘመድ ለቅሶ በልቶ፣ ከዘመድ ተቆራርጦ ማንም ሳያስበው በድንገት ሞተ። ሲሞት ተደወለለኝ፣ መጥቼ ቀበርኩት። የማህጸን ማሟሻዬ፣ የበኩሬ ነበር፣ ሙት አይወቀስም ይሉኛል፣ እኔ ግን ስወቅሰው እኖራለሁ።" አሉኝ በእንባ ብዛት የሞጨሞጨ አይናቸውን በአዳፋ ነጠላቸው ጫፍ እየጠረጉ።
"አይዞዎት እናቴ! በርታ ይበሉ! እርሱስ ቢሆን ይሄ ይመጣል ብሎ አለች አሰበ?! ያው ህይወት ሩጫ ናት፣ ምናልባት አልሞላ ብሎት..."
አላስጨረሱኝም።
"እድሜዬ ካለቀ፣ መቃብሬ ከተማሰ ብር አውርሶኝ፣ የልጅነት ፍቅሩን ነፍጎኝ፣ መኖሬን እንድጠላ አድርጎኝ ሞተ። በህይወት መኖሩ ብቻ መጽናዬ ነበር። ልጄ እናት አለችህ?!"
"አዎን እማ!"
"ዛሬን ጠይቃት፣ 'እንዴት አደርሽ' በላት። ሞት መምጫው ስለማይታወቅ ለነገ ምንም አታሳድር ልጄ። ልጄ ሲለፋበት የኖረውን፣ እኔን ያስተወውን ብሩን ወረስኩ፣ ፍቅሩን ግን ሳያወርሰኝ ሞተ። እኔ እንደምወድደው አውቃለሁ እርሱም ያውቃል፣ ወጣትነቴን ሰውቼ ያለአባት አሳድጌዋለሁ። እንደሚወድደኝ ሳያሳየኝ፣ እንደሚወድደኝ ሳላውቅ ሞተ" አሉኝ።
                               ****
የውርስ ገንዘቡን አካፍያቸው እንደጨረስኩ ከጓደኞቼ ጋር ዱባይ ሄጄ ልዝናና ከቆጠብኩት ብር ወደ ላይ ግማሹን አውጥቼ ለእናቴ ከላኩላት በኋላ ስልክ ደውዬ "እማ በዓል አብሬሽ ነው የማከብረው፣ ለበዓል ጨምርልኝ ያልሽኝን ብርም አስገብቼልሻለሁ፣ አወድሻለሁ እማ!" አልኳት።
ባልተለመደ ባህሪዬ የተገረመችው እናቴ "ምን ነው ጥልዬ በቀን መጠጣት ጀመርክ እንዴ?!" ስትል ጠየቀችኝ።
እንደምወዳት የምነግራት ሞቅ ሲለኝ ብቻ ስለነበረ አልተቀየምኳትም።
                           •••••
ሐሳብ ወለድ ታሪክ!

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Tilahun Girma Ang
1.3K viewsDAVE / PAPI, edited  10:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 16:32:15 በዚህ ዘመን ሰው ሆድ እንዲብሰው እንደማድረግ ቀላል ነገር የለም ። ሰዉ እንዳለ ስስ ሆኗል ። ቀኑ እንዲጨረብ ትንሽ ምክንያት ይበቃዋል ።

አጠገብህ ያለውን ስራ ፈት በብሄርህ ምክንያት ነው ስራ ያላገኘኸው ብትለው ሲብሰከሰክ ይውላል ።

አንዱ ጓደኛህ ሲደውልልህ "እየነዳሁ ነው መልሼ እደውልልሃለሁ" ብትለው ቀኑን ሙሉ ይቆዝማል ።

የሆነችን ልጅ "በጣም ወፍረሻል" ብትላት ለጊዜው የሆነ የሆነ ነገር ትልህና መስታወት ፊት ቆማ ትብሰለሰላች ። 

እስኪ አንዱ ሲስቅ ጠብቀህ  "ሳይኖርህ አትሳቅ" በለው ፤ ወዲያው ይከስማል።

እፊቱ እንግሊዘኛ ስታወራ የሚከፋው ሰውም አለ።

አፍቅሮ የተጎዳ ሰው "እህህህ" እንዲል የፌስቡክ ጨለምተኞች ከblack and white ፎቶ ጋር የሚለጥፉት አጭር ጽሑፍ ይበቃዋል ።

ናፋቂውን ምንም አትበለው ፤ ገና ደመና ሲያይ ውስጡ ይረበሻል ።

ለማልቀስ "ፍቅርሽ ነው የጎዳኝ" የሚል ዘፈን ብቻ የሚበቃው አለ ።

ደህና ነሽ ? ስትላት እንባዋ ግጥም የሚል አለች ።

ህልምህ ምን ነበር ? ብለህ ብትጠይቀው የማይከፋው አለ ? ።

ፀሐይ ሲመታው ብቻ ኑሮ የሚመረው አለ ።

ሰዉ እንደ ድሮው ረጅም የታክሲ ሰልፍ የመጠበቅ አቅም የለውም ። መኪና የለኝም ወይም የራይድ የለኝም ብሎ ያዝናል ።

እና ይሄ በሆዱ እንባ ያጠራቀመ ህዝብን ማስለቀስ ምን ሞያ ይጠይቃል ?

ከባዱ ነገር ተስፋ መስጠት ነው ። ተስፋ  ስጠው ስልህ ምክረው ማለቴ አይደለም ። ከምር ተስፋ ስጠው ። አስቀው ። አለሁ በለው ። ራሱን እንዲችል አድርገው ። ባዶ ሆዱን አትሰክሰው ። አብልተህም አትሰክሰው ። ዕድል ስጠው ። እመነው ። እቀፋት ። ተቃቀፉ ። ምናምን...

Via: Hab HD

@getem
@getem
@getem
173 viewsDAVE / PAPI, 13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 15:16:43 የምወድደው አለቃዬን ዛሬ አገኘሁት፣ ከዓመታት በኋላ። ያለፈውን ጊዜ አንስተን እንደ አዲስ ተሳሳቅን። በተለይ የሚከተለውን ገጠመኜን።
*
ባንክ ተቀጥሬ አመት ያህል እንደሆነኝ አንድ እሁድ እለት ከጓደኞቼ ጋር ኳስ ለማየት ከቤት ወጣን። ይሁንና ኳስ እያየን ድራፍት እየጠጣን የነበርን ጎረምሶች ባላሰብነው ሁኔታ በከተማው የሚገኙ አንድ ባለሀብት ባስወረዱልን ውስኪ እስከ እኩለ ሌሊት ስንራጭ አመሸን።

ጠዋት ላይ አንድ ጓደኞዬ ቤት ስነቃ ፣ እራሴን መሸከም አቅቶኛል። ቤቱ በመጠጥ ሽታ ተሞልቷል። በእርግጠኝነት በእዚህ መልኩ ሥራ መሄድ እንደማልችል ስለገባኝ ወደ አለቃዬ ስልክ ደውዬ...

"ዘመድ ስለሞተ ለመቅበር ወደ ገጠር እየሄድኩ ስለሆነ ፍቃድ ፈልጌ ነበር..." ስል ፈቃድ ጠየቅኩ።

ተፈቀደልኝ።

መሀል ላይ ሌላ መስሪያ ቤት የሚሰራ ጓደኛዬም ከእንቅልፉ ነቅቶ ወደ ቢሮው ደውሎ ለቅሶ ገጥሞኛል በማለት ሥራ ካስፈቀደ በኋላ የእኔን ጠየቀኝ።

"እንዲህ ሀንጎቨር ሳይለቅቀኝ ሥራ ገብቼማ የመጠጥ ሽታ ስጋብዛቸው አልውልም። እኔም አለቃዬ ጋ ደውዬ ዘመድ ሞቶብኛል ብዬ ዋሸሁ። ጌታ ይቅር ይበለኝ!" አልኩት።

"እኔማ አሁን ላይ ዘመዶቼን በሙሉ ጨርሼ በጎረቤት ሞት ምናምን ማስፈቀድ ጀምሬአለሁ" አለኝ። ተሳሳቅን።

ይሁንና እየተሳሳቅን ሰዐት ለማየት ስልኬን ሳነሳ ሳላውቅ ነክቼው ኖሮ አለቃዬ ጋ ደውሎ እየቆጠረ አገኘሁት። በእርግጠኝነት ንግግራችንን ሰምቷል። ቆሌዬ ተገፈፈ፣ መሬት ተከፍታ እንድትውጠኝ ተመኘሁ። ነግቶ አለቃዬን እንዴት ፊቱን እንደማየው ሲጨንቀኝ ዋለ፣ ማታም በሐሳብ ስገላበጥ፣ እንቅልፍ ባይኔ ሳይዞር ነጋ።

በማግስቱ ጭንቀት እየተጫጫነኝ፣ ልቤ እየደለቀ፣ አንገቴን ደፍቼ ወደ ምሰራበት ባንክ ሄድኩ። አለቃዬ እንደወትሮው በጠዋት ቢሮ ገብቷል። በጭንቀት እንደተዋጥኩ ፊቴን ከስክሼ ይቅርታ ለመጠይቅ ወደ እርሱ ሄድኩ።

ልክ እንዳየኝ ፊቱ ከንዴት ይልቅ በፈገግታ እንደተሞላ "ቀብር ደረስክ?!" ሲል ጠየቀኝ። ዝም አልኩ። ከፊቴ ላይ መሳቀቄን አንብቦ ነው መሰለ የእኔን ምላሽ ሳይጠብቅ...

"አይዞህ! አትጨነቅ። እኔም የሆነ ጊዜ ላይ እንዳንተው ጎረምሳ ነበርኩ። እረዳለሁ። ሌላ ጊዜ እንዳትዋሸኝ። አሁን ወደ ሥራህ ሂድ" አለኝ።
***

@wegoch
@wegoch
@paappii
1.3K viewsDAVE / PAPI, 12:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 10:51:13 ወግ ብቻ pinned «ጠላ እየጠጣን ከጓደኞቼ ጋ ተሰባስበን እየቀደድን ሳለ ፦ ምድር ላይ የትኛውን ገጠመኝህን በይበልጥ ትወዳዋለህ የሚል ቀደዳ ጀመርን ፍሬንድ ቀጠለ "አንድ እለት እሁድ ጠዋት እናቴ ቡና እየጠጣች ፣ እየመከረችኝ ፣ እየመረቀችኝ ፣ እየሰደበችኝ ሳለ በጣምምም ደስስ የሚልሽ ምን ብታገኝ ነው  አልኳት  አጠያየቄ ድንገት ነበር ላሊበላ ፣  አክሱም ጽዮን ፣ ውቅሮ ማርያም ካዲ ብሄድ ደስ ይለኛል አለቺኝ…»
07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ