Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 213.59K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2024-04-24 19:44:54
ገቢራዊ እየሆነ የሚገኘው አዲሱ የትምህርት ፖሊሲ የምልክት ቋንቋን አለማካተቱ በክፍተትነት ሊታይ እንደሚገባ ተገለፀ።

መንግሥት አዲስ የትምህርት ፖሊሲ በማዘጋጀት ሥራ ላይ ማዋሏ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ ፖሊሲው የምልክት ቋንቋን ሳያካትት ቀርቷል።

ይህም በሰነዱ አካታችነትን ላይ ጥያቄ የሚያስነሳ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ትምህርት፣ ቋንቋና መስማት የተሳናቸው ባህል ጥናት ክፍል ኃላፊ ጳውሎስ ካሱ (ዶ/ር) ለመናኸሪያ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

በምልክት ቋንቋ ከቅድመ መደበኛ እስከ መሰናዶ ደረጃ የመምህራን መመሪያና የተማሪዎች መማሪያ መፃሕፍት ቢዘጋጁም፤ በስርዓተ ትምህርቱ የምልክት ቋንቋን አለመካተቱ በትምህርት ስርዓቱ ላይ የሚፈጥረው ክፈተት ከፍ ያለ ነው ብለዋል፡፡

የዘርፉ ባለሙያዎች የምልክት ቋንቋ በኢትዮጵያ ተጨማሪ የሥራ ቋንቋ ሆኖ ዕውቅና እንዲያገኝ ጥያቄ እያቀርቡ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ #መናኸሪያ_ሬዲዮ

@tikvahuniversity
20.4K views16:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 19:34:09
#የቻናል_ጥቆማ

ለኢንጂነሪንግ ተማሪዎች እና Construction ዘርፍ ላይ ለተሰማራችሁ በሙሉ

የኮንስትራክሽን፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ፣ የአርክቴክቸር ተማሪ ነዎት? በጠቅላላ ኮንስትራክሽን የተሰማሩ ባለሙያ ነዎት?

በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ የሌክቸር ትምህርቶች፣ መፃሕፍቶች፣ ቪዲዮዎች እና ጠቃሚ የኮንስትራክሽን ዕውቀቶች ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይቀላቀሉን!

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያዎች፣
አዲስ የሚወጡ የግንባታ ጨረታዎች፣
እጅግ ጠቃሚ የኮንስትራክሽን መረጃዎች፣
በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ሌክቸር የምታገኙበት፡፡

Join Us :-

on Telegram

https://t.me/ethioengineers1
https://t.me/ethioengineers1

on TikTok

tiktok.com/@ethiocons
tiktok.com/@ethiocons
18.4K views16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 15:26:07
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሁለት ካምፓሶች በፀጥታ ችግር ተዘግተው ተማሪዎች እንዲሸጋሸጉ መደረጋቸው ተሰማ፡፡

በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሥር የሚገኙት ዘንዘልማ እና ሰባታሚት ካምፓሶች በፀጥታ ችግር ምክንያት መዘጋታቸውን ሪፖርተር ዩኒቨርሲቲውን በመጥቀስ ዘግቧል።

በሁለቱ ካምፓሶች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ የግብርና፣ የጤና፣ የጂኦሎጂ እና የዲዛስተር ማኔጅመንት ተማሪዎች የፀጥታው ችግር እስኪቀረፍ ከተማ ውስጥ ባሉ ካምፓሶች ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ማድረጉን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ብርሃኑ ገድፍ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በዘንዘልማ እና በሰባታሚት ካምፓሶች ውስጥ ይማሩ የነበሩ በርካታ ተማሪዎች ከተማ ውስጥ ያሉ ካምፓሶች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው፡፡

ዘንዘልማ እና ሰባታሚት ካምፓሶች በሚገኙባቸው አካባቢዎች የተኩስ ድምፅ በየጊዜው እንደሚሰማ የገለፁት ም/ፕሬዝዳንቱ፤ በተማሪዎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ከአንድ ወር በፊት ወደተለያዩ የተቋሙ ካምፓሶች እንዲዘዋወሩ መደረጉን ገልፀዋል፡፡

በከተማዋ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲው ካምፓሶች ውስጥ በቂ ቦታ በመኖሩ ተማሪዎቹ ምንም ዓይነት መጉላላት ሳይደርስባቸው ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ነው ብለዋል፡፡

አሁን ላይ ከሁለቱ ካምፓሶች ውጪ በሌሎች ካምፓሶች ላይ ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር እንደሌለ ም/ፕሬዝዳንቱ ገልጸው፤ በባህር ዳር ከተማ ካለው አንፃራዊ ሰላም አኳያ በርካታ ተማሪዎች ምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡

ከሁለቱ ካምፓሶች ውጪ አለመረጋጋቱ የተሻሻለ ቢሆንም፤ አልፎ አልፎ የተኩስ ድምፅ እንደሚሰሙ ተማሪዎቹ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ የዘንድሮ ተመራቂዎች የምረቃ ቀን መቼ እንደሆነ እስካሁን እንዳልተነገራቸውም አክለዋል፡፡ #ሪፖርተር

@tikvahuniversity
25.4K views12:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 15:05:50
#ሴጅ_ማሰልጠኛ_ኢንስቲትዩት

ሰኞ ሚያዚያ 21/2016 ዓ.ም 2ኛ ዙር የካፒታል ገበያ ስልጠና ይጀምራል።

ኢንስቲትዩታችን በፋይናንስና ካፒታል ማርኬት ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

ብቁ በሆኑ መምህራን የሚሰጠው ስልጠናው፤ ከመሰረታዊ የካፒታል ገበያ ምንነት ጀምሮ እንዴት አንድ ግለሰብ ወይም ተቋም ከስጋት ነፃ በሆነ መንገድ በገበያው ላይ መሳተፍ እንደሚችል ያብራራል።

ለበለጠ መረጃ፦  0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
        ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት


Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn
23.8K views12:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 12:36:17
#MoE

በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑ ተፈታኝ ተማሪዎች እያንዳንዳቸው የአገልግሎት ክፍያ 500.00 (አምስት መቶ) ብር ብቻ እንደሚከፍሉ ትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ አሳውቋል።

የዚህን ደብዳቤ ትክክለኛነትና ከደብዳቤው ጋር በተያያዘ ያላቸውን ጥርጣሬ በርካታ ተፈታኝ ተማሪዎች ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አድርሰዋል፡፡

ደብዳቤው ትክክለኛ መሆኑን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አረጋግጧል፡፡ የተገለፁትም የኢሜይል አድራሻዎች ህጋዊ የተቋሙ አድራሻዎች እንደሆኑ ለማወቅ ችለናል፡፡

Note:

#ዩኒቨርሲቲዎች ተፈታኝ ተማሪዎች የከፈሉትን ብር ሰብስበው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000553176097 ለትምህርት ሚኒስቴር ገቢ ማድረግ እንዳለባቸው ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡

በተመሳሳይ ተቋማቱ ተፈታኞች የከፈሉበትን ደረሰኝ ኮፒ በኢሜይል አድራሻ antedefar@gmail.com እና lakbt2013@gmail.com መላክ ይኖርባቸዋል።

@tikvahuniversity
28.5K views09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 12:36:05
በአዲስ አበባ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎቻቸው የሞዴል ፈተና እየሰጡ ነው፡፡

ሞዴል ፈተናው ከትላንት ጀምሮ ለተከታታይ ሦስት ቀናት እንደሚሰጥ የተገለፀ ሲሆን፤ ተማሪዎቹን በቀጣይ በሰኔ ወር ለሚሰጠው ሀገር አቀፍ ፈተና ማዘጋጀት የሞዴል ፈተናው ግብ መሆኑ ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity
25.5K views09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 12:23:38
#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

በአገልግሎት አሰጣጣችንና በዕቃዎቻችን ጥራት ላይ ደንበኞቻችን ምስክሮች ናቸው።
ዛሬም ብዛት እንዲሁም ጥራት ሳንቀንስ እያስተናገድን እንገኛለ!

ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች፣ ለጌመሮች፣ ወ.ዘ.ተ.

አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ! የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምዎ ማየት ይችላሉ።

@sww2844
0928442662
0940141114

https://t.me/samcomptech
26.7K views09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 20:46:29
እስካሁን ጥሪ ያልተደረገላቸው የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ተማሪዎች

የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል።

ተማሪዎቹ ከታህሳስ ወር ጀምሮ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የአቅም ማሻሻያ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ፡፡

ይሁን እንጂ በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የተመደቡ ተማሪዎች እስካሁን ጥሪ አልተደረገላቸውም።

ዩኒቨርሲቲው በ2016 ዓ.ም አዲስ ለተመደቡ የጀማሪ መርሐግብር እና በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ለተከታተሉ ተማሪዎች መጋቢት 14/2016 ዓ.ም ጥሪ ሲያደርግ፤ በ2016 ዓ.ም ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ለተመደቡ አዲስ የሪሚዲያል ተማሪዎች ጥሪ ሳያደርግ ቀርቷል።

እነዚህ ተማሪዎች በቀጣይ ጥሪ ይደረግልናል በሚል በተስፋ ሲጠብቁ ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ከአንድ ወር በኋላም ዩኒቨርሲቲው ጥሪ አላደረገላቸውም።

"የትምህርት ጊዚያቸው እየባከነባቸው እንደሆነ"ና "አስቸጋሪ ጊዜያትን እያሳለፉ እንደሚገኙ" ለቲክቫህ አስተያየታቸውን የሰጡ ተማሪዎች፤ መንግሥት መፍትሔ እንዲሰጣቸው በተደጋጋሚ ጠይቀዋል።

የሪሚዲያል ፈተናው ይሰጣል ተብሎ በመንግሥት የተቀመጠው ጊዜ 45 ቀናት የቀሩት መሆኑ ሌላው ተማሪዎቹን እያሳሰበ ያለ ጉዳይ ነው።

ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎቹ መቼ ጥሪ እንደሚደረግ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮችን በስልክ እና በአጭር መልዕክቶች የጠየቀ ቢሆንም ምንም አይነት ምላሽ ማግኘት አልቻለም።

ተማሪዎቹ ወደሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተዘዋውረው የሚማሩበት ዕድል ካለ፣ አማራጭ የፈተና ጊዜ የሚዘጋጅላቸው ከሆነ እና በተያያዥ ጉዳዮች ላይ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ወይም/እና ትምህርት ሚኒስቴር የሚሰጡትን ምላሽ ወደናንተ እናደርሳለን።

@tikvahuniversity
37.3K views17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 16:12:17
#ጥቆማ

ጤና ሚኒስቴር የሚያስተዳድራቸውን አዲስ የህክምና ትምህርት ኢንሼቲቭ (NMEI) ትምህርት ቤቶች መቀላቀል የምትፈልጉ ዕጩዎች ማመልከት ትችላላችሁ፡፡

ሚኒስቴሩ በNMEΙ ስርዓተ ትምህርት የቅበላ ፖሊሲ መሰረት፣ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ህክምና ኮሌጅ አዲሱን የህክምና ትምህርት ኢንሼቲቭ (NMEI) ለመቀላቀል ፍላጎት ያላቸውን ዕጩዎች እንዲመለምል፣ የመግቢያ ፈተና እንዲሰጥ እና ውጤት እንዲያሳውቅ ውክልና ሰጥቶታል። ውጤት ከተገለፀ በኋላ ቀሪ ጉዳዮች በሚኒስቴሩ የሚከናወን ይሆናል፡፡

ለመመዝገብ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፦

➤ የመጀመሪያ ዲግሪ በጤና ሳይንስ እንዲሁም በባዮሎጂ እና በኬሚስትሪ

➤ CGPA ለሴቶች 2.75 እና ለወንዶች 3.0 ፤ ለአዳጊ ክልሎች ለሴቶች 2.5 እና ለወንዶች 2.75

➤ ከምርቃት በኋላ ቢያንስ ሁለት ዓመት የሥራ ልምድ

➤ ዕድሚያችሁ ከ35 ያልበለጠ

➤ የፖንሰርሺፕ ደብዳቤ ከምትሰሩበት የመንግሥት ተቋም ማምጣት የምትችሉ

➤ ራሳችሁን ስፖንሰር ማድረግ የምትችሉ ማመልከት ትችላላችሁ

የፅሁፍ ፈተና 60% የሚይዝ ሲሆን ከፍተኛ ውጤት የሚያመጡ 260 አመልካቾች 30% ለሚይዘው ቃለመጠይቅ ይመረጣሉ፡፡

ተከታዩን ሊንክ በመጫን ያመልክቱ፦
https://portal.sphmmc.edu.et/Web/Announcement/List?studyLevel=Undergraduate&instructionId=dc716240-4408-46d0-8da6-4ea0bf659bae

Note:

➧ ማመልከት የሚቻለው በኦንላይን ብቻ ነው፡፡
➧ የምዝገባ ጊዜ፦ ከሚያዝያ 10-22/2016 ዓ.ም
➧ የፅሁፍ ፈተና፦ ግንቦት 4/2016 ዓ.ም
➧ ቃለመጠይቅ፦ ግንቦት 11/2016 ዓ.ም
➧ ውጤት የሚገለፀው፦ ግንቦት 14/2016 ዓ.ም

@tikvahuniversity
37.7K viewsedited  13:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 11:00:23
#ጥቆማ

በአዲስ አበባ ትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ፍቃዱ የታገደበት የጊብስን አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና መውሰድ እንዲችሉ ምዝገባ እንዲያደርጉ የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ጥሪ አድርጓል፡፡

በዚህም የትምህርት ቤቱ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ምዝገባ ዛሬ ሚያዝያ 15/2016 ዓ.ም በጊብሰን የጉለሌ ብራንች መድኃኔዓለም 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እና በጊብሰን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ብራንች ብስራተ ገብርኤል ኢስት ዌስት አዳራሽ የሚካሔድ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በተጠቀሱት ቦታዎች ወላጆች/አሳዳጊዎች ተማሪዎችን በመያዝ ምዝገባ በዛሬው ዕለት እንዲያካሒዱ ቢሮው አሳስቧል፡፡

@tikvahuniversity
34.2K views08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ