Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 213.59K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2024-04-13 11:06:36
#MizanTepiUniversity

ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ አዲስ አመራር ተመድቦለታል።

ዋቆ ገዳ (ዶ/ር) የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው በትምህርት ሚኒስቴር ተመድበዋል።

ተረፈ ጌታቸው (ዶ/ር) ተጠባባቂ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት፣ ግርማ ጥላሁን (ዶ/ር) ተጠባባቂ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት እንዲሁም ይደግ ማሞ ተጠባባቂ የአስተዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ እና የቢዝነስ ልማት ም/ፕሬዝዳንት ሆነው መመደባቸው ተገልጿል።

አዲስ የተመደቡት አመራሮች ለአንድ ዓመት ተቋሙን እየመሩ እንደሚቆዩና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ምልመላ መመሪያ መሠረት ወደፊት በሚወጣ የውድድር ማስታወቂያ የቋሚ አመራሮች ምርጫ ይደረጋል ተብሏል።

@tikvahuniversity
22.2K views08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 10:43:05
ለበይነ መረብ (Online) ስልጠና ፈላጊዎች ምዝገባ ላይ ነን።

ፈጥነው ይመዝገቡ!

ባሉበት ሆነው በተመጣጣኝ ዋጋ የሚማሩበት
100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
በአካል ለሚማሩ ተማሪዎቻችን ያሉ ዕድሎችና የአሰጣጥ ደረጃችን በሙሉ እንደተጠበቁ ይቀጥላሉ።

ለበለጠ መረጃ፦  
0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
        ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት


Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn
21.7K views07:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 19:26:25
#WolaitaSodoUniversity

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ እና ድኅረ ምረቃ መርሐግብር ያሰለጠናቸውን 256 ተማሪዎች ነገ ሚያዝያ 5/2016 ዓ.ም ያስመርቃል።

ተማሪዎቹ ነገ በተቋሙ ዳውሮ ታርጫ ካምፓስ በሚካሔድ የምረቃ ስነ-ስርዓት እንዲመረቁ የዩኒቨርሲቲው ሴኔት በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

በዩኒቨርሲቲው ጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ በቅድመ ምረቃ መርሐግብር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁና የመውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡ 32 ተማሪዎች እንደሚመረቁ ተገልጿል።

በተለያዩ የድኅረ ምረቃ መርሐግብሮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 224 ተማሪዎች እንደሚመረቁ ታውቋል።

@tikvahuniversity
29.5K views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 15:08:48
#የሥራ_ቅጥር_ጥቆማ

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በስምንት የጤና ሙያ መስክ የሥራ መደቦች ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 48
➤ የትምህርት ደረጃ፦ ከመጀመሪያ ዲግሪ ጀምሮ
➤ የሥራ ልምድ፦ ዜሮ ዓመት
➤ የሥራ ቦታ፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ
➤ የማመልከቻ ጊዜ፦ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት
➤ የምዝገባ ቦታ፦ አዲስ አበባ ቦሌ ርዋንዳ ኤምባሲ ፊት ለፊት በሚገኘው የዲላ የኒቨርሲቲ ጉዳይ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ወይም ዲላ ዩኒቨርሲቲ በኦዳያአ ግቢ የሰው ኃብት አስተዳደር ቢሮ ቁ. G1/012

Note:
በድረ-ገጽ የተመዘገባችሁ አመልካቾች ለፈተና ስትጠሩ የትምህርት ማስረጃችሁንና ተያያዥ ስነዶችን ዋናውና የማይመለስ ኮፒ ይዛችህ መቅረብ ይኖርባችኋል፡፡

የትምህርት ማስረጃችሁ ከአገር ውስጥ ትምህርት ተቋማት ከሆነ ዋናውና ኮፒ እንዲሁም በውጭ አገራት ትምህርታችሁን የተከታተላቹ የአቻ ግመታ ሰነድ ማረጋገጫ ማቅረብ ይጠበቅባችኋል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ፦ 0926208813

@tikvahuniversity
33.7K views12:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 11:33:52
2.5 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሕንጻዎች እና መሠረተ ልማቶች ግንባታ እያካሔደ መሆኑን ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ገለፀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው በበጀት ዓመቱ 25 የተለያዩ ሕንፃዎች እና መሠረተ ልማቶች በማስገንባት ላይ ይገኛል።

ግንባታዎቹ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅና የተማሪ ቅበላ አቅምን ለመጨመር የሚረዱ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ግንባታ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ ተስፋሁን ገብሩ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

የአስተዳደር እና የተማሪዎች አገልግሎት ሕንጻዎች፣ የመማሪያ ክፍሎች፣ የተማሪዎች ዶርሚተሪዎች፣ ቤተ-ሙከራዎች፣ አይ.ሲ.ቲ. ታወሮች እና ሌሎች መሠረተ ልማቶች በግንባታው መካተታቸውን ገልፀዋል፡፡

@tikvahuniversity
32.2K views08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 10:19:17
ጅማ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 778 ተማሪዎች ነገ ሚያዝያ 5/2016 ዓ.ም ያስመርቃል።

ከተመራቂዎቹ 26ቱ በሦስተኛ ዲግሪ እንዲሁም 350 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁቀ ሲሆን፤ ቀሪዎቹ 402 ተማሪዎች ደግሞ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች ናቸው፡፡

ከተመራቂዎቹ መካከል ብሔራዊ የመውጫ ፈተና ወስደው የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ 379 የዩኒቨርስቲው ጤና ኢንስቲትዩት የህክምና ተማሪዎች እንደሚገኙበት ታውቋል።

@tikvahuniversity
30.5K views07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 10:08:13
19ኛ ዙር የግራፊክስ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኢዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክስ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና ነገ ሚያዝያ 05/2016 ዓ.ም ይጀምራል።

    ቀድመው ይመዝገቡ!

100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
Advanced Graphics + Video Editing + Motion Graphics + Digital Marketing
15 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

ለበለጠ መረጃ፦  
0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
        ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት


Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn
32.6K views07:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-11 11:24:11
ወሎ ዩኒቨርሲቲ ከ STEMpower ጋር በመተባበር በሰሜኑ ጦርነት ውድመት የደረሰበትን ዩኒቨርሲቲውን ስቴም ማዕከል በድጋሜ በማቋቋም ሥራ ለማስጀመር እየሠራ መሆኑን ገልጿል፡፡

ማዕከሉ የ STEM ትምህርት እና የእንግሊዝኛ ቋንቋ ስልጠና ይሰጥ የነበረ ሲሆን በተጨማሪ የቤተ-ሙከራ ማዕከል እንዲኖረው ለማድረግ ይሠራል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity
22.5K views08:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-11 10:21:25
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የነበሩት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው መሾማቸው ተሰምቷል።

የኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸው ሥራ መጀመራቸውም ታውቋል፡፡

ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) ሦስተኛ ዲግሪያቸውን በእንስሳት እርባታ እና አመጋገብ ከ Humboldt-Universität zu Berlin አጊኝተዋል፡፡

@tikvahuniversity
26.3K views07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-10 17:12:53
#MoE

የአገር ውስጥ የምርምር ጆርናል አርታኢዎች እና አሳታሚዎች ለ Plagiarism ችግር ልዩ ትኩረት በመስጠትና ቅድመ ፍተሻ በማድረግ የምርምር ጆርናል ጥራትን እንዲያስጠብቁ ትምህርት ሚኒስቴር አሳሰበ።

በርካታ በአገር ውስጥ የሚታተሙ የምርምር ጆርናሎች ፅሁፎች (Manuscripts) የPlagiarism መጠናቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ከሚሰጠው ነጥብ በላይ መሆኑን በዚህ ዓመት ባደረገው የፍተሻ ሥራ ማረጋገጡን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በመሆኑም ከመጋቢት 30/2016 ዓ.ም. ጀምሮ የPlagiarism መጠኑ ከ 30% በላይ የሆነ የምርምር ጆርናል ለፍተሻ ብቁ የማይሆንና ዕውቅና የማይሰጠው መሆኑ ተገልጿል።

ለዚህም ሚኒስቴሩ የተሻሻለ መመሪያ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መላኩ ታውቋል።

@tikvahuniversity
35.9K views14:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ