Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 214.08K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2024-04-16 09:53:23
#AddisAbabaUniversity

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ ከአምስት ዓመታት በኋላ ዳግም ወደ ህትመት ሥራ መመለሱ ተሰምቷል።

ለዘመናት የተለያዩ የህትመት ውጤቶችን ለአንባብያን ሲያበረክት የቆየው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ፤ በግብርና፣ በኢኮኖሚ፣ በትምህርት እና በፓን አፍሪካኒዚም ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ስምንት መፃሕፍትን በማተመ ዳግም ሥራ መጀመሩን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

በሌላ መረጃ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመፃሕፍት አውደ ርዕይ በ 6 ኪሎ ካምፓስ (ዋናው ግቢ) ትናንት ተከፍቷል፡፡

በርካታ መፃሕፍት የቀረቡበት አውደ ርዕዩ፤ እስከ እሁድ ሚያዝያ 13/2016 ዓ.ም ለጎብኚዎች ክፍት ሆኖ ይቆያል።

@tikvahuniversity
37.8K views06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 14:49:59
ባለ ብዙ ሙያ ተመራቂው

ጅማ ዩኒቨርሲቲ ባሳለፍነው ቅዳሜ ካስመረቃቸው ተማሪዎች መካከል ባለ ብዙ ሙያ ተመራቂ የሆኑት ዶ/ር በዛብህ ብርሃኑ ይገኝበታል።

የቴሌቪዥን ድራማዎች ፅሁፍ ዝግጅት እና መፃሕፍት ማሳተም ዶ/ር በዛብህ የሚታወቅባቸው ሌሎች ጉዳዮች ናቸው፡፡

ዶ/ር በዛብህ በቅርቡ የሚያሳትመውን ጨምሮ አራት መፃሕፍትን የፃፈ ሲሆን፤ ስድስት ሲትኮም ድርሰቶችን በመድረስ ለህዝብ አድርሷል፡፡

በጥርስ ህክምና የዶክትሬት ዲግሪ ተመራቂው በዛብህ፤ በሀገራችን በተለያዩ ቴሌቪዥን የሚተላለፉ ተከታታይ ድራማዎች ላይ በደራሲነት ተሳትፏል፡፡

ዘጠነኛው ሺ ከ35 ክፍል በላይ፣ መስሪያ ቤት፣ ሳሎኑ፣ ዶክተሮቹ፣ ፊሽካዎቹ እና አንድ ላይ የተሰኙ ድራማዎች ላይ በደራሲነትና በዳይሬክተርነት ተሳትፏል። በርካታ የቴሌቪዥን እና የራዲዮ ማስታወቂያዎችንም አዘጋጅቷል።

ደራሲ እና የጥርስ ሐኪም ዶ/ር በዛብህ ብርሃኑ፤ በቅርቡ ለህትመት የሚበቃ "የአፍ ጤና አጠባበቅ ለልጆች እና ለወላጆች" የሚል መማሪያ መፅሐፍ አዘጋጅቶ ማጠናቀቁንም ገልጿል።

@tikvahuniversity
27.0K views11:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 14:33:12
#የቻናል_ጥቆማ

ለኢንጂነሪንግ ተማሪዎች እና Construction ዘርፍ ለይ ለተሰማራችሁ በሙሉ

የኮንስትራክሽ፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ፣ የአርክቴክቸር ተማሪ ነዎት?
በጠቅላላ ኮንስትራክሽን የተሰማሩ ባለሙያ ነዎት?

በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ የሌክቸር ትምህርቶች፣ መፃሕፍቶች፣ ቪድዮዎች እና ጠቃሚ የኮንስትራክሽን ዕውቀቶች ለማግኝት ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይቀላቀሉን!

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያዎች፣
የሚወጡ የግንባታ ጨረታዎች፣
እጅግ ጠቃሚ የኮንስትራክሽን መረጃዎች፣
በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ ሌክቸር የምታገኙበት

Join Us :-

on Telegram

https://t.me/ethioengineers1
https://t.me/ethioengineers1

on TikTok

tiktok.com/@ethiocons
tiktok.com/@ethiocons
24.9K views11:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 12:01:31
የትምህርት ማስረጃዎችን የማጥራት ሥራ በክልሎች ደረጃ ተግባራዊ ሊደረግ ነው፡፡

በፌደራል ተቋማት ላይ የተጀመረው ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን የመመርመር ሥራ በክልሎች ደረጃ እንደሚጀመርም የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ም/ዋ/ዳይሬክተር ቢኒያም ሔሮ ለአሐዱ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

ማስረጃዎችን የመመርመር ሥራው በጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ እንደሚመራ ም/ዋ/ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡

በቀጣይ የትምህርት ማስረጃዎችን በዲጂታል አማራጭ ብቻ ለመስጠት ሙከራ እየተደረገ እንደሆነም ኃላፊው አብራርተዋል፡፡

ማስረጃዎችን በመፈተሽና በማረጋገጥ የህግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እየተሠራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡ #AhaduFM

@tikvahuniversity
27.7K views09:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 14:14:42
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዳውሮ ታርጫ ካምፓስ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን 256 ተማሪዎች አስመርቋል።

በጤና ሳይንስና ህክምና ትምህርት መስክ በመጀመሪያ ዲግሪ መርሐግብር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁና የመውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡ 32 ተማሪዎች ተመርቀዋል።

ከተመራቂዎቹ መካከል 224ቱ በተለያዩ የድኅረ ምረቃ መርሐግብሮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል።

@tikvahuniversity
19.2K views11:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 11:40:07
ጅማ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ያሰለጠናቸውን 778 ተማሪዎች አስመረቀ።

ከተመራቂዎቹ 26 በሦስተኛ ዲግሪ፣ 350 በሁለተኛ ዲግሪ እንዲሁም 402 በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

በህክምና፣ በጥርስ ህክምና፣ በነርሲንግ፣ በሚድዋይፈሪ እና በፊዚዮቴራፒ የትምህርት መስኮች የሰለጠኑ የህክምና ተማሪዎች ከተመራቂዎቹ መካከል ይገኙበታል።

@tikvahuniversity
23.0K views08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 11:06:36
#MizanTepiUniversity

ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ አዲስ አመራር ተመድቦለታል።

ዋቆ ገዳ (ዶ/ር) የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው በትምህርት ሚኒስቴር ተመድበዋል።

ተረፈ ጌታቸው (ዶ/ር) ተጠባባቂ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት፣ ግርማ ጥላሁን (ዶ/ር) ተጠባባቂ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት እንዲሁም ይደግ ማሞ ተጠባባቂ የአስተዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ እና የቢዝነስ ልማት ም/ፕሬዝዳንት ሆነው መመደባቸው ተገልጿል።

አዲስ የተመደቡት አመራሮች ለአንድ ዓመት ተቋሙን እየመሩ እንደሚቆዩና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ምልመላ መመሪያ መሠረት ወደፊት በሚወጣ የውድድር ማስታወቂያ የቋሚ አመራሮች ምርጫ ይደረጋል ተብሏል።

@tikvahuniversity
22.2K views08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 10:43:05
ለበይነ መረብ (Online) ስልጠና ፈላጊዎች ምዝገባ ላይ ነን።

ፈጥነው ይመዝገቡ!

ባሉበት ሆነው በተመጣጣኝ ዋጋ የሚማሩበት
100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
በአካል ለሚማሩ ተማሪዎቻችን ያሉ ዕድሎችና የአሰጣጥ ደረጃችን በሙሉ እንደተጠበቁ ይቀጥላሉ።

ለበለጠ መረጃ፦  
0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
        ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት


Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn
21.7K views07:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 19:26:25
#WolaitaSodoUniversity

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ እና ድኅረ ምረቃ መርሐግብር ያሰለጠናቸውን 256 ተማሪዎች ነገ ሚያዝያ 5/2016 ዓ.ም ያስመርቃል።

ተማሪዎቹ ነገ በተቋሙ ዳውሮ ታርጫ ካምፓስ በሚካሔድ የምረቃ ስነ-ስርዓት እንዲመረቁ የዩኒቨርሲቲው ሴኔት በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

በዩኒቨርሲቲው ጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ በቅድመ ምረቃ መርሐግብር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁና የመውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡ 32 ተማሪዎች እንደሚመረቁ ተገልጿል።

በተለያዩ የድኅረ ምረቃ መርሐግብሮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 224 ተማሪዎች እንደሚመረቁ ታውቋል።

@tikvahuniversity
29.5K views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 15:08:48
#የሥራ_ቅጥር_ጥቆማ

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በስምንት የጤና ሙያ መስክ የሥራ መደቦች ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 48
➤ የትምህርት ደረጃ፦ ከመጀመሪያ ዲግሪ ጀምሮ
➤ የሥራ ልምድ፦ ዜሮ ዓመት
➤ የሥራ ቦታ፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ
➤ የማመልከቻ ጊዜ፦ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት
➤ የምዝገባ ቦታ፦ አዲስ አበባ ቦሌ ርዋንዳ ኤምባሲ ፊት ለፊት በሚገኘው የዲላ የኒቨርሲቲ ጉዳይ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ወይም ዲላ ዩኒቨርሲቲ በኦዳያአ ግቢ የሰው ኃብት አስተዳደር ቢሮ ቁ. G1/012

Note:
በድረ-ገጽ የተመዘገባችሁ አመልካቾች ለፈተና ስትጠሩ የትምህርት ማስረጃችሁንና ተያያዥ ስነዶችን ዋናውና የማይመለስ ኮፒ ይዛችህ መቅረብ ይኖርባችኋል፡፡

የትምህርት ማስረጃችሁ ከአገር ውስጥ ትምህርት ተቋማት ከሆነ ዋናውና ኮፒ እንዲሁም በውጭ አገራት ትምህርታችሁን የተከታተላቹ የአቻ ግመታ ሰነድ ማረጋገጫ ማቅረብ ይጠበቅባችኋል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ፦ 0926208813

@tikvahuniversity
33.7K views12:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ