Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 213.59K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2024-04-10 16:42:53
የኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ (Computer Programming) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን።

100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
መሠረታዊ የኮምፒውተር ትምህርትን አካቶ የሚሰጥ
C++, Java እና Python ፕሮግራሞች ከፍ ባለ ደረጃ (Advanced Level) በጋራ የሚሰጡበት

ለበለጠ መረጃ፦  
0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
        ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት


Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn
33.2K views13:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 19:42:30
#BahirDarUniversity

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የነበሩት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) ወደ ሌላ የመንግሥት ኃላፊነት መመደባቸው ተሰምቷል።

በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በዛሬው ዕለት ተፈርሞ የወጣ የውክልና ደብዳቤ፤ ፕ/ር እሰይ ከበደ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው የተወከሉ መሆናቸውን ያሳያል።

"በቀጣይ ውድድር ተደርጎ በቋሚነት ፕሬዝዳንት እስኪመደብ ድረስ ካለዎት የሥራ ኃላፊነት በተጨማሪ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ስራን እንዲሰሩ ውክልና የተሰጠዎት መሆኑን" እገልፃለሁ ይላል በሚኒስትሩ የተፃፈው የውክልና ደብዳቤው።

ፕ/ር እሰይ ከበደ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን በማገልገል ላይ የሚገኙ ሲሆን ባለፈው በኅዳር 2016 ዓ.ም ነበር በባዮ-ስታትስቲክስ መስክ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ በዩኒቨርሲቲው የተሰጣቸው።

ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው መሾማቸው ተሰምቷል።

@tikvahuniversity
41.0K views16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 18:39:28
የመውጫ ፈተና መቼ ይሰጣል?

የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ የሚወስዱ የቅድመ ምረቃ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች መረጃ ማሰባሰብ ሥራ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እየተከናወነ ይገኛል።

ተቋማቱ ለፈተና የሚቀመጡ ተማሪዎች የተሟላ መረጃ እስከ ሚያዚያ 5/2016 ዓ.ም ድረስ በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በኩል ተረጋግጦ እንዲላክ ትምህርት ሚኒስቴር ማሳሰቡ ተሰምቷል።

የመውጫ ፈተናው በሰኔ ወር አጋማሽ እንደሚሰጥ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity
48.8K views15:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 19:20:32
#AAEB

የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መካከለኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ሰኔ 4 እና 5/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከሰኔ 12 እስከ 14/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል።

ፈተናዎቹ በተጠቀሱት ቀናት በጠዋት እና ከሰዓት መረሐግብር እንደሚሰጡ ቢሮው ያወጣው የድርጊት ጊዜ ሰሌዳ ያሳያል።

@tikvahuniversity
27.5K views16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 18:05:17
#MoE

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎችን የራስ ገዝ ሽግግር የሚያሳልጡ ፍኖተ ካርታ እና መመሪያ ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ።

የዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ መሆን ተቋማቱ በአስተዳደራዊ፣ አካዳሚያዊ እንዲሁም በሰው ሃብትና ፋይናንስ አስተዳደር ጉዳዮች ነፃነትን ከተጠያቂነት ጋር የሚያገኙበት የአሰራር ስርዓት እንደሆነ በሚኒስቴሩ የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለኢዜአ ተናግረዋል።

የዩኒቨርሲቲዎችን የራስ ገዝ ሽግግር ለማሳለጥ የሚያስችሉ የፍኖተ ካርታ እና የመመሪያ ዝግጅት በቅርቡ ተጠናቀው ወደ ሥራ እንደሚገቡ ጠቁመዋል።

ዘጠኝ ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ለማድረግ እየተሠራ ሲሆን ተቋማቱ ከአደረጃጀት ጀምሮ ለሽግግሩ የሚያግዟቸውን ተግባራት እያከናወኑ እንደሆነ ኃላፊው አስረድተዋል።

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ ራስ ገዝ ለመሆን የሰው ኃይል፣ ሃብት የማመንጨት አቅም፣ የመሰረተ ልማትና የፋይናንስ አስተዳደር ስርዓታቸው እንዲሁም ዓለም አቀፍ ትስስራቸው እንደሚታይ ገልፀዋል። #ENA

@tikvahuniversity
30.0K views15:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 10:38:39
Dambi Dollo

ትላንት በደረሰ የመኪና አደጋ ሦስት የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ሠራተኞች ህይወት አልፏል፡፡

በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ 'አይራ ቅርንጫፍ' የዕረፍት ቀናት (Weekend) ትምህርት አስተምረው ሲመለሱ የነበሩ መምህራን ባጋጠማቸው የመኪና አደጋ ሁለት መምህራን እና አንድ አሽከርካሪ ህይወታቸው ሲያልፍ፣ በ12 ሰዎች ላይ ደግሞ ጉዳት መድረሱን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

በአደጋው ህይወታቸው ላለፈ የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች ዛሬ ጠዋት የሽኝት ፕሮግራም ተደርጓል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በሠራተኞቹ ህልፈት የተሰማውን ሐዘን በመግለፅ፤ ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጆቻቸው መፅናናትን ተመኝቷል።

@tikvahuniversity
34.5K views07:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-07 09:09:40 የክብር ዶክትሬት ዲግሪ አሰጣጥ

"ግልጽ የሆነ መመርያ እስከሚወጣ ድረስ የክብር ዶክትሬት እንዳይሰጥ ተከልክሏል።"
- የትምህርት ሚኒስትሩ

የተበታተነ አሠራርን ለመቅረፍ ግልጽ የሆነ መመርያ እስኪወጣ ድረስ ዩኒቨርሲቲዎች የክብር ዶክትሬት የሚባል ነገር መስጠት እንዲያቆሙ እንደተነገራቸው የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገለፁ፡፡

ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት ‹‹የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ "የዶክትሬት ዲግሪና የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሽልማት በኢትዮጵያ" በሚል ጭብት ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተካሔደ ምሁራዊ ውይይት ወቅት ነው።

በኢትዮጵያ የክብር ዶክትሬት ሲሰጥ በተበታተነ ሁኔታ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች መስጠት እንዲያቆሙ ውሳኔ መተላለፉን ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ አሰጣጥን በተመለከተ መመርያ እያዘጋጀ መሆኑንና መመርያውንም በዚህ ዓመት አጠናቆ ለመጨረስ ሒደት ላይ እንደሆነ ሚኒስትሩ አክለዋል፡፡

በኢትዮጵያ እስካሁን 79 ሰዎች የክብር ዶክትሬት ዲግሪ እንደተሰጣቸው አስረድተው ከነዚህም 68 በመቶ የሚሆነው ለክልል ሰዎች የተሰጠ እንደሆነ ገልጸዋል።

በመድረኩ የመነሻ ጽሑፍ ያቀረቡት ፕ/ር ማስረሻ ፈጠነ በበኩላቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ ዩኒቨርሲቲዎች የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሲሰጥ አካዳሚያዊ ያልሆነ ዕውቅናን በመንተራስ እንደሆነና ተሸላሚዎችም ካላቸው ክህሎት፣ ስብዕና እንዲሁም ያበረከቱት አስተዋጽኦ ጋር በተያያዘ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ዩኒቨርሲቲዎች የክብር ዶክትሬት ዲግሪ አሰጣጥን የተመለከተ መመርያ እንዳላቸው አንስተዋል።

በኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ በርካታ ሰዎችን እያሳሰበ የመጣው ጉዳይ ዩኒቨርሲቲዎች የራሳቸው ሰው የሚሉትን ብቻ በመምረጥ የክብር ዶክትሬት እየሰጡ መሆኑ ነው ብለዋል፡፡

የክብር ዶክትሬት ዲግሪን ከዩኒቨርሲቲዎች የሚያገኙ ሰዎች ጭምር እንደመጠሪያ እንደሚጠቀሙበትና ይኼም በጣም የተሳሳተ ነገር እንደሆነ ገልጸው፣ በርካታ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችም ይኼንን ድርጊት እንደሚፈጽሙ አስታውሰዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲዎች የክብር ዶክትሬት ዲግሪ የሰጧቸው ሰዎች ያልተገባ ድርጊት ከፈፀሙ፣ የክብር ዶክትሬት ዲግሪውን መንጠቅ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡ #ሪፖርተር

@tikvahuniversity
41.3K views06:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-07 09:09:31
34.8K views06:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 13:18:43
የትግራይ መምህራን ማኅበር የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የመምህራንን የ2015 ዓ.ም የአምስት ወራት ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፍል ጥሪ አቀረበ፡፡

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ውዝፍ ክፍያውን ለመክፈል ቀደም ሲል ተስማምቶ እንደነበር የማኅበሩ ም/ፕሬዝዳንት ንግስቲ ጋረደ ለክልሉ ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ አስተዳደሩ ለመክፈል ቃል የገባውን የአምስት ወራት ደመወዝ አለመክፈሉን ም/ፕሬዝዳንቷ ገልፀዋል።

በክልሉ የሚገኙ መምህራንን የ17 ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም ሲሉ ሰልፍ መውጣታቸው ይታወሳል።

@tikvahuniversity
20.7K views10:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 12:55:07
ቅዳሜ ሚያዝያ 05/2016 ዓ.ም 19ኛ ዙር የግራፊክስ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኢዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክስ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና ይጀምራል።

    ቀድመው ይመዝገቡ!

100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
Advanced Graphics + Video Editing + Motion Graphics + Digital Marketing
ከ15 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

ለበለጠ መረጃ፦  
0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
        ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት


Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn
21.0K views09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ