Get Mystery Box with random crypto!

የትግራይ መምህራን ማኅበር የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የመምህራንን የ2015 ዓ.ም የአምስት ወራት | Tikvah-University

የትግራይ መምህራን ማኅበር የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የመምህራንን የ2015 ዓ.ም የአምስት ወራት ውዝፍ ደመወዝ እንዲከፍል ጥሪ አቀረበ፡፡

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ውዝፍ ክፍያውን ለመክፈል ቀደም ሲል ተስማምቶ እንደነበር የማኅበሩ ም/ፕሬዝዳንት ንግስቲ ጋረደ ለክልሉ ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ አስተዳደሩ ለመክፈል ቃል የገባውን የአምስት ወራት ደመወዝ አለመክፈሉን ም/ፕሬዝዳንቷ ገልፀዋል።

በክልሉ የሚገኙ መምህራንን የ17 ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም ሲሉ ሰልፍ መውጣታቸው ይታወሳል።

@tikvahuniversity