Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahuniversity — Tikvah-University
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Moe
Moh
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 214.39K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2024-04-12 11:33:52
2.5 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሕንጻዎች እና መሠረተ ልማቶች ግንባታ እያካሔደ መሆኑን ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ገለፀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው በበጀት ዓመቱ 25 የተለያዩ ሕንፃዎች እና መሠረተ ልማቶች በማስገንባት ላይ ይገኛል።

ግንባታዎቹ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅና የተማሪ ቅበላ አቅምን ለመጨመር የሚረዱ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ግንባታ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ ተስፋሁን ገብሩ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

የአስተዳደር እና የተማሪዎች አገልግሎት ሕንጻዎች፣ የመማሪያ ክፍሎች፣ የተማሪዎች ዶርሚተሪዎች፣ ቤተ-ሙከራዎች፣ አይ.ሲ.ቲ. ታወሮች እና ሌሎች መሠረተ ልማቶች በግንባታው መካተታቸውን ገልፀዋል፡፡

@tikvahuniversity
32.2K views08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 10:19:17
ጅማ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 778 ተማሪዎች ነገ ሚያዝያ 5/2016 ዓ.ም ያስመርቃል።

ከተመራቂዎቹ 26ቱ በሦስተኛ ዲግሪ እንዲሁም 350 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁቀ ሲሆን፤ ቀሪዎቹ 402 ተማሪዎች ደግሞ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች ናቸው፡፡

ከተመራቂዎቹ መካከል ብሔራዊ የመውጫ ፈተና ወስደው የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ 379 የዩኒቨርስቲው ጤና ኢንስቲትዩት የህክምና ተማሪዎች እንደሚገኙበት ታውቋል።

@tikvahuniversity
30.5K views07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 10:08:13
19ኛ ዙር የግራፊክስ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኢዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክስ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና ነገ ሚያዝያ 05/2016 ዓ.ም ይጀምራል።

    ቀድመው ይመዝገቡ!

100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
Advanced Graphics + Video Editing + Motion Graphics + Digital Marketing
15 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

ለበለጠ መረጃ፦  
0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
        ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት


Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn
32.6K views07:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-11 11:24:11
ወሎ ዩኒቨርሲቲ ከ STEMpower ጋር በመተባበር በሰሜኑ ጦርነት ውድመት የደረሰበትን ዩኒቨርሲቲውን ስቴም ማዕከል በድጋሜ በማቋቋም ሥራ ለማስጀመር እየሠራ መሆኑን ገልጿል፡፡

ማዕከሉ የ STEM ትምህርት እና የእንግሊዝኛ ቋንቋ ስልጠና ይሰጥ የነበረ ሲሆን በተጨማሪ የቤተ-ሙከራ ማዕከል እንዲኖረው ለማድረግ ይሠራል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity
22.5K views08:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-11 10:21:25
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የነበሩት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው መሾማቸው ተሰምቷል።

የኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸው ሥራ መጀመራቸውም ታውቋል፡፡

ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) ሦስተኛ ዲግሪያቸውን በእንስሳት እርባታ እና አመጋገብ ከ Humboldt-Universität zu Berlin አጊኝተዋል፡፡

@tikvahuniversity
26.3K views07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-10 17:12:53
#MoE

የአገር ውስጥ የምርምር ጆርናል አርታኢዎች እና አሳታሚዎች ለ Plagiarism ችግር ልዩ ትኩረት በመስጠትና ቅድመ ፍተሻ በማድረግ የምርምር ጆርናል ጥራትን እንዲያስጠብቁ ትምህርት ሚኒስቴር አሳሰበ።

በርካታ በአገር ውስጥ የሚታተሙ የምርምር ጆርናሎች ፅሁፎች (Manuscripts) የPlagiarism መጠናቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ከሚሰጠው ነጥብ በላይ መሆኑን በዚህ ዓመት ባደረገው የፍተሻ ሥራ ማረጋገጡን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በመሆኑም ከመጋቢት 30/2016 ዓ.ም. ጀምሮ የPlagiarism መጠኑ ከ 30% በላይ የሆነ የምርምር ጆርናል ለፍተሻ ብቁ የማይሆንና ዕውቅና የማይሰጠው መሆኑ ተገልጿል።

ለዚህም ሚኒስቴሩ የተሻሻለ መመሪያ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መላኩ ታውቋል።

@tikvahuniversity
35.9K views14:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-10 16:42:53
የኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ (Computer Programming) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን።

100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
መሠረታዊ የኮምፒውተር ትምህርትን አካቶ የሚሰጥ
C++, Java እና Python ፕሮግራሞች ከፍ ባለ ደረጃ (Advanced Level) በጋራ የሚሰጡበት

ለበለጠ መረጃ፦  
0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
        ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት


Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn
33.2K views13:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 19:42:30
#BahirDarUniversity

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የነበሩት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) ወደ ሌላ የመንግሥት ኃላፊነት መመደባቸው ተሰምቷል።

በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በዛሬው ዕለት ተፈርሞ የወጣ የውክልና ደብዳቤ፤ ፕ/ር እሰይ ከበደ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው የተወከሉ መሆናቸውን ያሳያል።

"በቀጣይ ውድድር ተደርጎ በቋሚነት ፕሬዝዳንት እስኪመደብ ድረስ ካለዎት የሥራ ኃላፊነት በተጨማሪ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ስራን እንዲሰሩ ውክልና የተሰጠዎት መሆኑን" እገልፃለሁ ይላል በሚኒስትሩ የተፃፈው የውክልና ደብዳቤው።

ፕ/ር እሰይ ከበደ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን በማገልገል ላይ የሚገኙ ሲሆን ባለፈው በኅዳር 2016 ዓ.ም ነበር በባዮ-ስታትስቲክስ መስክ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ በዩኒቨርሲቲው የተሰጣቸው።

ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው መሾማቸው ተሰምቷል።

@tikvahuniversity
41.0K views16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 18:39:28
የመውጫ ፈተና መቼ ይሰጣል?

የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ የሚወስዱ የቅድመ ምረቃ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች መረጃ ማሰባሰብ ሥራ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እየተከናወነ ይገኛል።

ተቋማቱ ለፈተና የሚቀመጡ ተማሪዎች የተሟላ መረጃ እስከ ሚያዚያ 5/2016 ዓ.ም ድረስ በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በኩል ተረጋግጦ እንዲላክ ትምህርት ሚኒስቴር ማሳሰቡ ተሰምቷል።

የመውጫ ፈተናው በሰኔ ወር አጋማሽ እንደሚሰጥ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity
48.8K views15:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 19:20:32
#AAEB

የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መካከለኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ሰኔ 4 እና 5/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከሰኔ 12 እስከ 14/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል።

ፈተናዎቹ በተጠቀሱት ቀናት በጠዋት እና ከሰዓት መረሐግብር እንደሚሰጡ ቢሮው ያወጣው የድርጊት ጊዜ ሰሌዳ ያሳያል።

@tikvahuniversity
27.5K views16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ