Get Mystery Box with random crypto!

#MoE የአገር ውስጥ የምርምር ጆርናል አርታኢዎች እና አሳታሚዎች ለ Plagiarism ችግር ልዩ | Tikvah-University

#MoE

የአገር ውስጥ የምርምር ጆርናል አርታኢዎች እና አሳታሚዎች ለ Plagiarism ችግር ልዩ ትኩረት በመስጠትና ቅድመ ፍተሻ በማድረግ የምርምር ጆርናል ጥራትን እንዲያስጠብቁ ትምህርት ሚኒስቴር አሳሰበ።

በርካታ በአገር ውስጥ የሚታተሙ የምርምር ጆርናሎች ፅሁፎች (Manuscripts) የPlagiarism መጠናቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ከሚሰጠው ነጥብ በላይ መሆኑን በዚህ ዓመት ባደረገው የፍተሻ ሥራ ማረጋገጡን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በመሆኑም ከመጋቢት 30/2016 ዓ.ም. ጀምሮ የPlagiarism መጠኑ ከ 30% በላይ የሆነ የምርምር ጆርናል ለፍተሻ ብቁ የማይሆንና ዕውቅና የማይሰጠው መሆኑ ተገልጿል።

ለዚህም ሚኒስቴሩ የተሻሻለ መመሪያ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መላኩ ታውቋል።

@tikvahuniversity