የትምህርት ማስረጃዎችን የማጥራት ሥራ በክልሎች ደረጃ ተግባራዊ ሊደረግ ነው፡፡
በፌደራል ተቋማት ላይ የተጀመረው ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን የመመርመር ሥራ በክልሎች ደረጃ እንደሚጀመርም የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ም/ዋ/ዳይሬክተር ቢኒያም ሔሮ ለአሐዱ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
ማስረጃዎችን የመመርመር ሥራው በጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ እንደሚመራ ም/ዋ/ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡
በቀጣይ የትምህርት ማስረጃዎችን በዲጂታል አማራጭ ብቻ ለመስጠት ሙከራ እየተደረገ እንደሆነም ኃላፊው አብራርተዋል፡፡
ማስረጃዎችን በመፈተሽና በማረጋገጥ የህግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እየተሠራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡ #AhaduFM
@tikvahuniversity