Get Mystery Box with random crypto!

የትምህርት ማስረጃዎችን የማጥራት ሥራ በክልሎች ደረጃ ተግባራዊ ሊደረግ ነው፡፡ በፌደራል ተቋማት | Tikvah-University

የትምህርት ማስረጃዎችን የማጥራት ሥራ በክልሎች ደረጃ ተግባራዊ ሊደረግ ነው፡፡

በፌደራል ተቋማት ላይ የተጀመረው ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን የመመርመር ሥራ በክልሎች ደረጃ እንደሚጀመርም የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ም/ዋ/ዳይሬክተር ቢኒያም ሔሮ ለአሐዱ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

ማስረጃዎችን የመመርመር ሥራው በጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ እንደሚመራ ም/ዋ/ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡

በቀጣይ የትምህርት ማስረጃዎችን በዲጂታል አማራጭ ብቻ ለመስጠት ሙከራ እየተደረገ እንደሆነም ኃላፊው አብራርተዋል፡፡

ማስረጃዎችን በመፈተሽና በማረጋገጥ የህግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እየተሠራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡ #AhaduFM

@tikvahuniversity