Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 213.59K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2024-04-27 12:34:09
Ready to empower the next generation of learners?

Join us on EdTech Mondays for an eye-opening discussion on Financing EdTech Startups in Ethiopia! Discover how investors are igniting innovation and driving change in the education landscape, overcoming unique challenges to support promising ventures. From bridging the digital divide to enhancing learning outcomes, explore the transformative potential of investing in EdTech startups. Tune in and be part of the movement to revolutionize education in Ethiopia!

Monday, April 29th at 8:10 pm on Fana FM 98.1 for insights that matter.

#EdTechEthiopia #EducationInnovation #JoinTheConversation #Ethiopia #DigitalLiteracy #TechnologyInEducation #EdTechMondaysEthiopia #EquityInEducation #Ethiopia #DigitalLiteracy #ShegaMedia #MastercardFoundation
16.2K views09:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-27 10:22:28
#ይጠንቀቁ

"ሰርተፊኬት የሚያሰጡ ነጻ የኦንላይን ስልጠና " የሚሉ ማስታወቂያዎች በማኅበራዊ ትስስር ገጾች እየተዘዋወሩ መሆኑን ተመልክተናል፡፡ ማስታወቂያዎቹ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎችን እንዲሁም የትምህርት ሚኒስቴርን ስም ይጠቅሳሉ፡፡

ይሁን እንጂ እነዚህ ማስታወቂያዎች ሐሰተኛ መሆናቸውን ዩኒቨርሲዎቹ አረጋግጠዋል፡፡

"የተቋሜን ስም በመጠቀም የሚፈፀም የማጭበርበር ተግባር ሰለሆነ የሚመለከተው ሁሉ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስባለው" ብሏል መቐለ ዩኒቨርሲቲ፡፡

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተመሳሳይ የማስጠንቀቂያ መልዕክት ከጥቂት ሳምንታት በፊት አውጥቶ እንደደነበር አይዘነጋም፡፡

"በተለያዩ ድረ-ገጾች እና ማኅበራዊ ሚዲያዎች የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ስም እና አርማ በመጠቀም ከሚተላለፉ ሐሰተኛ መረጃዎች እንዲጠነቀቁ" ብሏል ዩኒቨርሲቲው፡፡

@tikvahuniversity
21.1K views07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-26 14:56:21
#የሥራ_ቅጥር_ጥቆማ

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሥራ መደቦች መምህራንና ቴክኒካል ረዳቶች አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 19
➤ የትምህርት ደረጃ፦ የመጀመሪያ እና 2ኛ ዲግሪ
➤ የሥራ ልምድ፦ ዜሮ ዓመትና ከዚያ በላይ
➤ የሥራ ቦታ፦ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
➤ የማመልከቻ ጊዜ፦ ከሚያዝያ 17/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት
➤ የምዝገባ ቦታ፦ አዲስ አበባ አሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት በሚገኘው የትምህርት መሳሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት ቢሮ ወይም ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር ህንጻ 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. B-4

ለተጨማሪ መረጃ፦ አ.አ. 0111-26-01-24 ፖ.ሳ.ቁ. 1362

@tikvahuniversity
30.8K views11:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-26 14:40:28
ማክሰኞ ሚያዚያ 22/2016 ዓ.ም 20ኛ ዙር የግራፊክስ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኢዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክስ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና ይጀምራል።

ቀድመው ይመዝገቡ!

100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
15 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት
Advanced Graphics + Video Editing + Motion Graphics + Digital Marketing በአንድ ላይ

ለበለጠ መረጃ፦  0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
        ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት


Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn
27.3K views11:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-26 11:31:44
ወልድያ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ምክትል ፕሬዝዳንቶች ተመድበውለታል፡፡

ካሳሁን አህመድ (ዶ/ር) የወልድያ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ፣ ምርምር ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተመድበዋል፡፡

ማርየ በለጠ (ዶ/ር) የዩኒቨርሲቲው አስተዳደርና ቢዝነስ ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው በትምህርት ሚኒስቴር እና በቦርድ አፅዳቂነት ተመድበዋል፡፡

አዲስ የተሾሙት አመራሮች ከተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ትውውቅ አድርገዋል፡፡

@tikvahuniversity
29.0K views08:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 18:43:29
#YHMC

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ለመጀመሪያ ጊዜ በዲግሪ መርሐግብር ማስተማር ጀመረ።

ኮሌጁ በዛሬው ዕለት 79 ተማሪዎችን በመቀበል በዲግሪ መርሐግብር ትምህርት መስጠት መጀመሩ ተሰምቷል።

ኮሌጁ በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም ማስተማር የጀመረባቸው መስኮች፦

➤ በድንገተኛ ሕክምና ነርስነት (Emergency and Critical Nursing)

➤ በጨቅላ ሕጻናት ነርስነት (Neonatal Nursing)

➤ በአጠቃላይ ነርስነት (Comprehensive Nursing)

➤ በላቦራቶሪ ባለሙያ (Medical Lab)

@tikvahuniversity
33.9K views15:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 18:43:00
#የፈተና_ጥሪ

ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት እና በቴክኒካል አሲስታንት የሥራ መደቦች ባለሙያዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቅርቡ ላወጣው ማስታወቂያ ላመለከቱ የፈተና ጥሪ አድርጓል።

ለፈተና የተመረጡ ባለሙያዎች በተቋሙ የቴሌግራም ገፅ በመግባት መመረጣቸውን ይመልከቱ
https://t.me/dkulatestnews/74

ለፈተና የተመረጣችሁ ሚያዝያ 21/2016 ዓ.ም የተጠየቀውን መስፈርት አሟልታችሁ በዩኒቨርሲቲው የሰው ሃብት አስተዳደር ቢሮ እንድትቀርቡ ተብሏል።

@tikvahuniversity
31.0K views15:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 15:41:31
በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ አርጀንቲናውያን መንግሥት ለሕዝብ ዩኒቨርሲቲዎች በሚሰጠው ድጎማ ላይ ጭማሪ እንዲያደርግ ለመጠየቅ በሀገሪቱ መዲና ቦነስ አይረስ ሰልፍ ወጥተዋል፡፡

ባለፈው ዓመት ወደ ስልጣን የመጡት የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሐብየር ሚሌይ የመንግሥትን ወጪ መቀነስ ላይ ትኩረት በማድረግ ይታወቃሉ፡፡

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሶሻሊስት ርዕዩተ ዓለም አስተሳሰብ መጠመቂያ ማዕከላት በመሆናቸው የበጀት ቅነሳ እንደተደረገባቸው ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል፡፡

ይሁን እንጂ በሀገሪቱ ምርጥ የሚባሉ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የበጀት እጥረት ፈተና እንደሆነባቸው ይገልጻሉ፡፡ ምርጥ ከሚባሉ የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የሆነው ቦነስ አይረስ ዩኒቨርሲቲ፤ የበጀት ድጎማ ጭማሪ ካልተደረገለት በበጀት እጥረት ምክንያት በሦስት ወራት ውስጥ ሊዘጋ እንደሚችል ይፋ አድርጓል፡፡

ዛሬ በሀገሪቱ መዲና ቦነስ አይረስ የተደረጉ ሰልፎች ለዩኒቨርሲቲዎቹ የሚደረግ የበጀት ድጎማ ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ የሚጠይቁ ነበሩ፡፡ #BBC

@tikvahuniversity
30.4K views12:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 12:52:39
#ጥቆማ

ለ Fulbright African Research Scholars Program (FARSP) ያመልክቱ!

የዩኒቨርሲቲ መምህር ነዎት? ምርምርዎትን በዩናይትድ ስቴትስ ማከናወን ይሻሉ?

ዓመታዊው የፉልብራይት አፍሪካ የምርምር ምሁራን ፕሮግራም (FARSP) 2025/26 ለአመልካቾች ክፍት ሆኗል፡፡

የማመልከቻ ጊዜው እስከ ሐምሌ 8/2016 ዓ.ም ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡

ለማመልከት
https://apply.iie.org/fvsp2025

ለማንኛውም አይነት ጥያቄ እንዲሁም ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ተከታዩ አድራሻ የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲን ያናግሩ፦ PASAddisExchanges@state.gov

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
31.5K views09:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-24 19:55:19
#ጥቆማ

የእንግሊዘኛ ቋንቋ ምዘና ፈተና (IELTS Test) በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ይውሰዱ፡፡

የብሪቲሽ ካውንስል IELTS የፈተና ማዕከል የIELTS ፈተና ግንቦት 17/2016 ዓ.ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ይሰጣል፡፡

ፈተናውን ለመውሰድ የአመልካቾች ምዝገባ በመከናወን ላይ ይገኛል።

ሁለት አይነት የ IELTS ፈተናዎች (IELTS Academic and IELTS General Training) መውሰድ ለሚፈልጉ አመልካቾች እንደሚሰጡ ተገልጿል፡፡

የብሪቲሽ ካውንስል ድረ-ገፅ ላይ በመግባት ኦንላይን መመዝገብ ይችላሉ
https://ethiopia.britishcouncil.org/exam/ielts/dates-fees-locations

ለፈተናው ዝግጅት የሚያስፈልግዎትን ስልጠና እና ምክር ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ማግኘት ይችላሉ።

ለበለጠ መረጃ፦ 0925629589

@tikvahuniversity
21.2K views16:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ