Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxslijoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.17K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ምንማማርበት :መዝሙር: ስብከቶች ይተላለፋል !

መንፈሳዊ ትምህርቶች : መንፈሳዊ ጥያቄዎች : ስብከት : መዝሙር : ይቀርብበታል #ጉዞው ገዳማት #ሰማህታት ታሪክ ይቀርባል!
FacebookGroup : ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ይቀላቀሉ ::

#shear

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-25 07:04:18 #የሰንበትን_ቀን_ትቀድሰው_ዘንድ_አስብ

‹‹ስድስት ቀን ስራ፣ተግባርህም ሁሉ አድርግ በሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፡፡እግዚአብሔርም በሰባተኛው ቀን አርፏልና ስለዚህ እግዚአብሔር የሰንበትን ቀን ባርኮታል ቀድሶታል፡፡ ›› (ዘጸ 20፡10-11)

#ሰንበት_ማለት_ምን_ማለት_ነው ?

ሰንበት ማለት አቆመ፣አረፈ ማለት ነው፡፡ይህ ቀን የጌታ ዕረፍት የተባረከም ቀን ነው፡፡ከማንኛውም ሥጋዊ ሥራ ተቆጥበን የእግዚአብሔርን ውለታ የምናስብበት ቀን ነው፡፡ ሰው እረፍት ያስፈልገዋል፡፡ የሰንበት ቀንም የተፈጠረው ለዚህ ነው፡፡ (ዘዳ 5፡14)፣(ማር 2፡38)
ከሳምንቱ ሰባት ቀናት መካከል ለእረፍት የተቀደሰው የተባረከው ዕለት ሰንበት ብቻ ነው፡፡ ስለሌሎች ቀናት የተነገረው ‹‹ ያ መልካም እንደሆነ አየ››የተባለው ብቻ ነው፡፡ ሰንበትን ግን ባርኮታል ቀድሶታል፡፡ (ዘፍ 1፡12፣ 18፡20፣ 25፡31)

በሐዲስ ኪዳን ለክርስቲያን ሁለት ሰንበት አለ ቀዳሚት ሰንበት(ቅዳሜ) እና ሰንበተ ክርስቲያን(እሑድ)
ቀዳሚት ሰንበት (ቅዳሜ)
ጌታ ያረፈባት ለእስራኤል ዘሥጋ የታዘዘው ሰንበት ነው፡፡ ይህ ቀን እስራኤላውያንን እግዚአብሔር አምላክ ከግብፅ ባርነት ወደ እረፍት እንዳወጣቸው ያመለክታል፡፡ዘዳ5-2-16 በእግዚአብሔር እና በህዝቡ መካከል ምልክት ነበረ ሰንበትን አለማክበር ግን ከባድ ቅጣት ያስከትል ነበር፡፡ (ዘጸ 3፡17) ፣ (ሕዝ 20፡12) ፣ (ዘኁ 15፡32-36)
ፈሪሳውያን በነበራቸው የተሳሳተ አመለካከት በሰንበት ቀን እንኳን መልካም ሥራን አይሰሩም ነበር፡፡ስለዚህም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ተወቅሰዋል፡፡ (ማቴ 12፡14) ፣ (ሉቃ 4፡16)

#ሰንበተ_ክርስቲያን_(እሑድ)

ይህች ቀን ለሳምንቱ መጀመሪያ፣ጌታችን ሥነ ፍጥረትን መፍጠር የጀመረበት ጌታ የተነሣበት፣መንፈስ ቅዱስ የወረደበት እንዲሁም ጌታችን ዳግመኛ በክብር የሚመጣበት ዕለት ስለሆነ ሰንበተ ክርስቲያን እንለዋለን፡፡ በሰንበተ ክርስቲያን (በጌታ ቀን) የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ልዩ ትኩረት በመስጠት ይሰባሰቡ ነበር፡፡ (ሐዋ 20፡7) ፣ገንዘብ ያዋጡበት ነበር (1ኛቆሮ 16፡2) ፣ በሥርዓተ ዓምልኮ የሚተጉበት፣የጌታችን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን የሚቀበሉበት ዕለት ነበር፡፡ (ዮሐ 20፡1-24) ፣ (ሐዋ 2፡11-14)

በቤተክርስቲያን ታሪክ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ዕለተ እሑድ የክርስቲያኖች ሰንበት ናት በማለት ሥራ እንዳይሰራባት አዋጅ አስነግሮ ነበር፡፡ ምንም እንኳን ይህቺ ዕለት በሐዲስ ኪዳን መከበር የጀመረ ቢሆንም በብሉይ ኪዳን ከፋሲካ በፊት የሰንበት (የቀዳሚት) ማግስት በመባል በኩራት እና ቀዳሚያት የሚያቀርቡበት ቀን ነበር፡፡ (ራዕ 1፡10)

በቀዳሚት ሰንበት ቅዱስ እግዚአብሔር ከሥራው ሁሉ አርፎ ሥጋዊ እረፍትን ለሰው እንዳስተማረ በዚህች ቀን (በሰንበተ ክርስቲያን) በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት የተገኘውን የዘላለማዊ የነፍስ ዕረፍት የምናስብበት ነው፡፡ (ዕብ 4፡1-10)

#የሰንበት_ቀን_መሰጠት_ዓላማ

የሰው ልጅ ባሕርይ ደካማ ነውና እግዚአብሔር ሰንበትን ሰራለት፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ደካማ ባህሪያችንን ስለሚያውቅ ከሳምንቱ ዕለታት አንዱ ሰንበት እድርጎ ለዕረፍት ሰጠን፡፡ ከድካማችን የተነሳ በዕለቱ መስራት አንችልምና ሰንበት ለሥጋችን ጠቃሚ ነው፡፡ ነገር ግን ሰንበት የተሰጠበት ምክንያት ሰው በዚህ ዓለም ሲደክም ስጋውን ብቻ ሲያገለግል እንዳይኖር የአምላኩን ውለታ እያሰበ በመንፈሳዊ አገልግሎት ፀንቶ እንዲኖር ነው፡፡ ዘጸ 5-14-15

ለምልክት

አምላካችን እግዚአብሔር እንደተናገረው ሁሉ ሰንበት የዘላለማዊ እና የመንፈሳዊ ዕረፍታት ምልክት ሆኖ የተሰጠ ጸጋ ነው፡፡ ዘጸ 31-13 ሰንበት ለሚመጣው ዘላለማዊ ዕረፍት ምሳሌ ሆኖ የተሰጠ የብሉይ ኪዳን ሕግ ነው፡፡ በህጉ መሰረት በሰንበት ዕረፍተ ሥጋ ይደረጋል፡፡ይህም ለኋላው ዘመን ለድኅነተ ነፍስ ምሳሌ ነው፡፡ በሐዲ ኪዳንም የተገለጠው የክርስቶስ ትንሳኤ በሰንበተ ክርስቲያን ተፈፅሟል፤ ሰንበተ ክርስቲያንም የሰው ልጆች ለዘለዓለም አርፈው ከእግዚአብሔር ጋር በደስታ የሚኖሩበት ምስጢረ ትንሣኤ የተገለጠባት የድኅነት ቀን ናት፡፡

#ሰንበትን_እንዴት_ማክበር_ይገባል?

ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰንበት ለመንፈሳዊ ሥራዎች(አገልግሎቶች) የተሰጠች መሆኗን ለማስተማር በሰንበት ድውያንን ይፈውስ፣ በምኩራብ እየተገኘም ያስተምር ነበር፡፡ (ዮሐ 5፡2-11 ፣9-14)፣(ሉቃ 14፡1-6)
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለመፍቅረ ሰንበት አይሁድ ስለሰንበት አከባበር ሲያስተምራቸው ‹‹ከእናንተ አንድ በግ ያለው በሰንበትም በጉ በጉድጓድ ቢወድቅበት ይዞ የማያወጣው ማን ነው? እንግዲህ ሰው ከበግ እንደምን አይበልጥም? ስለዚህ በሰንበት መልካም ሥራን መሥራት ተፈቅዷል›› ብሏል።

ማቴ12-10-13 ክርስቲያን ሰንበትን ሲያከብር እንደጌታችን ትምህርት መንፈሳዊ ሥራን በመሥራት ይገባል እንጂ ልክ እንደ አይሁድ ያጠፈውን ሳይዘረጋ የዘረጋውን ሳያጥፍ ሊያሳልፍ አይገባም፤ሰንበት ስለ ሰው ተፈጥሯል።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር!!!
    Join @ortodoxslijoch
4.9K views04:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-23 06:45:20 ኪዳነ ምህረት

ኪዳነምህረት ስንል የምህረት ቃልኪዳን ማለት ነው፡፡በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው፡፡


  እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምድራዊ ቆይታዋ ዘውትር ወደ ክርስቶስ መካነ መቃብር ጎለጎታ እየወረደች ትፀልይ ነበር፡፡ ልጇ እና ወዳጇ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገችው ልመናና ፀሎት ተመልክቶና ሰምቶ የምህረት ቃል ኪዳን ገባለት ፡፡


እንኳን የእናቱን ፀሎት እና ልመና ቀርቶ ዘውትር በሀጥያት የምንዘፈቀውን እኛን ክፉዎቹን የሚሰማ አምላክ ስለ አንቺ ፣ ስለ እናቴ ክብርና ፀጋ ስል ይኸው ቃሌ ብሎ ቃልኪዳን አደረገ፡፡
« ከመረጥሁት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ። … » መዝ, 89 : 3 እንዲል መፅሐፉ፡፡

ስሟን ለሚጠሩ፣ በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት ቃልኪዳን ሰጥቷታል ፡፡

ታላቁ መፅሐፍ እንዲህ ይላል፦
". . . ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ። " ኦሪት ዘፍ. 9 : 16

በዚህም መሠረት ቃልኪዳኗን ምክንያት በማድረግ ኪዳነ-ምህረት እያልን እንጠራታለ

እንኳን ለ«ኪዳነምህረት» አደረሳችሁ። የእመቤታችን ምህረት እና ረድዔት፤በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን!!!
         @ortodoxslijoch
         @ortodoxslijoch
6.2K views03:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-22 06:35:56 በሕይወትህ በረከት እንዲበዛልህ አመስጋኝ ሁን! ”

          

በሕይወታችን ብዙ ልናሟላቸው የምንፈልጋቸው ነገሮች
ይኖራሉ። ጠቢቡ ሰለሞን በመጽሐፈ መክብብ 1:7 ላይ ሲናገር
" ፈሳሾች ሁሉ ወደ ባሕሩ ይሄዳሉ ባሕሩ ግን አይሞላም "
ይላል።

ይህም ምን ቢሰጠው የትኛውም ያህል ቢትረፈረፍለት
የሰው ልጅ ምኞትና ፍላጎት ማለቂያ የለውምና። እኛም ገንዘብ፤
ስራ፤ ፍቅር፤ ዝና፤ ስልጣን፤ በምኞት ቋጠሯችን ውስጥ
ካካበትናቸው ጥቂቶቹ ናቸው።
መመኘቱ ባልከፋ …..ነገር ግን ብዙዎቻችን የሌለንን ስንመለከት
ያሉንን ነገሮች ዓይን እንነፍጋቸዋለን ስለዚህ መጠየቅ እንጂ
ማመስገን ይሳነናል፤ በዚህም ሁልግዜ ጠያቂዎች እንጂ
አመስጋኞች አይደለንም። ልብ በሉ ምኞቶቻችን ሁሉ ሊሳኩ
የሚችሉት ባለን ነገሮች መጀመሪያ መደሰት እና ማመስገን
ስንጀምር ነው።

ለምሳሌ፦ አንድ ወዳጃችን በችግራችን ደርሶ ረዳን እንበል፤
ላደረገልን እርዳታ ምስጋና ካልሰጠነው እንዴት ብሎ በሌላ
ችግራችን ይደርስልናል?፤ አምላካችን እግዚአብሔርም
ላደረገልን ነገር ባመሰገንነው ቁጥር ሌሎች ልመናችንን ሰምቶ
በበረከት ላይ በረከት ያትረፈርፍልናል።

ስለዚህ ሁልግዜ
አመስጋኝ አንደበት ሊኖረን ይገባል።
ነገር ግን በምስጋና ፈንታ “በቂ ገንዘብ አላገኝም”፤ “ኑሮዬ
ምስቅልቅሉ የወጣ ነው” ፤ “መልካም የትዳር አጋር
አላገኘሁም”፤ “ስኬታማ አይደለሁም” " እግዚአብሔር
አይሰማኝም" የምንልና የምንማረር ከሆነ ያለንን ነገሮች
እንዳናይ ከማድረጋቸውም በላይ በረከታችንን የማራቅና ያለንም
በረከት ልናጣና ልንነጠቅ እንችላለን።
ብዙዎቻችን ግን ይህንን አንረዳም።

ለደቂቃ ልቦናችንን ሰብስበን
ካስተዋልነው እያንዳንዶቻችን በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ብንሆን
እንኳን፤ ልናመሰግን የምንችልበት ብዙ ምክንያቶች አሉን።

እንደው ዋጋቸውን እያራከስን ነው እንጂ እያንዳንዶቻችን ሌሎች
የሚመኟቸው ነገሮች እኛ ጋር ዋጋ አጥተው ተቀምጠዋል።

ለምሳሌ፦ የአልጋ ቁራኛ የሆነ ሰው በህይወቱ የሚመኘው ነገር
ሙሉ ጤንነትን ሆኖ ሳለ፤ ጤነኛው ሰው ግን ስላለው ጤና
አለማመስገኑ አይገርምም?
ካስተዋልነው አንዲት ቃል ህይወታችንን በርግጥም

ትለውጣለች….. ለጠቢብ ሰው አንዲት ቃል ይበቃዋል ይባል
የለ በማቴዎስ ወንጌል 25:29 “ ላለው ሁሉ ይሰጠዋል
ይበዛለትማል…. ለሌለው ግን ያው ያለውም እንኳን
ይወሰድበታል” የሚለው ቃል የሚያስረዳን ሁላችንም ለተሰጠን
ማንኛውም መክሊት መጀመሪያ ምስጋና እናቅርብ ያኔ…ሌሎች
በረከቶቻችንን፣ ይመጣሉ።
እግዚአብሔርንም ስለሰጠን ነገር ሁሉ ካመሰገንነው ባለን ላይ
ሁሉ ለመጨመር አያመነታም ።

                    ሼር

      Join @ortodoxslijoch
5.9K views03:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-21 07:48:03 አስተማሪ ምክር ከመጽሐፍ ቅዱስ አንብቡት
# ለጭንቀትና # ፍርሃት መፍትሄ የሆኑ ጥቅሶች
«===========
፩• ጽኑ አይዞአችሁ አትፍሩ ከፊታቸውም አትደንግጡ አምላክህ እግዚአብሔር እርሱ ከአንተ ጋር ይሄዳል።/ዘዳ 31÷6/
፪• በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ። \ፊሊጵ 4÷6/
፫• በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና አይዞህ አትፍራ።/ኢያሱ 1÷9/
፬• ሰላሜን እሰጣችኋለሁ ልባችሁ አይታወክ።/ዮሐ 14÷27/
፭• እግዚአብሔርን ፈለግሁት መለሰልኝም ከመከራዬም ሁሉ አዳነኝ። /መዝ 34÷4/
፮• የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ።/ቆላስ 3÷15/
፯• የሰላምም ጌታ ራሱ በሁሉ መንገድ ዘወትር ሰላምንይስጣችሁ። /2ኛ ተሰሎ 3÷16/
፰•እግዚአብሔር እረዳቴ ነው አልፈራም ሰው ምን ያደርገኛል። /መዝ 118÷6/
፱• ፍፁም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም። /1ኛ ዮሐ 4÷18/
፲• እርሱ ስለ እናተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት። /1ኛ ጴጥ 5÷7/
# ከሰዎች # ጋር # በሰላም # ለመኖር # የሚረዱህ # ምክሮች
=====================================
፩• ስትሰጥ ምላሽ አትጠብቅ። /ምሳሌ 21÷26/
፪• ካለመጠርጠር እመን። /1ኛ ቆሮ 13÷7/
፫•ይቅር ስትል ቂም አትያዝ። \ቆላስ 3÷13_14/
፬• የሰው ንግግር ሳታቋርጥ አዳምጥ።/ምሳ 18
፭•ሰዎች ላይ ክፉ አታስብ። /ፊልጵ 2÷14/
፮• መልስ ስትሰጥ አትከራከር። /ምሳ 17÷1/
፯• ቃልህን ጠብቅ። /ማቴ 5÷37/
፰• ለመስማት እንጂ ለመናገር አትፍጠን።/ ያዕቆ 1÷19/
፱• በሁሉም ነገር ትግዕስተኛ ሁን። \1ኛ ቆሮ 13÷4/
፲• ይቅር መባባልን ሁሌም አትዘንጋ። /ኤፌሶ 4÷31_32/
# ለትዳር # ጠቃሚ # ምክር
=====================================
፩• ሁልግዜም ትዳርህን አጥብቀህ ያዝ። /ማር 10÷9/
፪• ለትዳርህ ታማኝ ሁን። /ምሳሌ 5÷15_23/
፫•ለመንፈሳዊ ውጊያዎች ዝግጁ ሁን። /ኤፌ 6÷11\
፬• ፈተናዎችን ለማለፍ ልብህን ጠብቅ። /ምሳ 4÷23/
፭• በጸሎት መጽናት እዳለብህ አትዘንጋ። /ሮሜ 12÷12/
፮• ባለቤትህን አፍቃሪ ሁን።/1ኛ ቆሮ 13÷7/
፯• በሁሉም ነገሮች አመስጋኝ ሁን።/1ኛ ተሰሎ 5÷18/
፰• የተበደልከውን አትቁጠር። /1ኛ ቆሮ 13÷5/
፱• አነጋገርህ በቅንነት የተሞላ ይሁን።/ ምሳ 16÷24/
፲• ሁልጊዜም ይቅር ባይ ሁን። /ማቴ 18÷21_22/
# ጠቃሚ # ምክር
====================================
፩• እግዚአብሔርን ከሁሉም በፊት አስቀድም።/ማቴ 6÷33/
፪• ሳታቋርጥ ጸልይ። \1ኛ ተሰሎ5÷17_18/
፫• በሁሉም አመስግን።/ መዝ 100÷4/
፬• ቃልህን ጠብቅ። /ሮሜ 4÷21/
፭• ይቅር በል። /ቆላስ 3÷13/
፮• በትጋት ስራ። /ቆላስ 3÷23/
፯• ሁልግዜ እውነትች ተናገር። /ምሳሌ 12÷22/
፰• ቸርና ርኅሩህ ሁን። \ኤፌ 4÷32\
፱• እርስ በርሳችሁ ተጽናኑ። \1ኛ ተሰሎ 4÷18/
፲• እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ። 1ኛ ጴጥሮ 1÷22/
5.8K views04:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-20 06:40:08 “30" የመፅሐፍ ቅዱስ ትዛዛት፦!
"---------------------------------"
1:-እርስ በርሳችሁ አትጣሉ::(ዘፍ 45:24)
2:_እርስ በርሳችሁ ሐሰት አትነጋገሩ::(ዘሌ 19:11)
3:_እርስ በርሳችሁም ተስማሙ::(ማር 9:50)
4:_እርስ በርሳችሁ አታንጎራጉሩ::(ዮሐ 6:43)
5:_እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ::(ሮሜ 12:10)
6:_እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ::(ሮሜ 12:10)
7:_እርስ በርሳችሁ በአንድ ሀሳብ ተስማሙ::(ሮሜ 12:16)
8:_እርስ በርሳችሁ ከመዋደድ በቀር ለማንም እዳ አይኑርባችው::(ሮሜ 13:8)
9:_እርስ በርሳችሁ በአንድ ሐሳብ መሆንን ይስጣችሁ::(ሮሜ 15:5-6)
10:_እርስ በርሳችሁ ተቀባበሉ::(ሮሜ 15:7)
11:_እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ::(ሮሜ 16:16)
12:_እርስ በርሳችሁ አትከላከሉ::(1ኛ ቆሮ 7:5)
13:_እርስ በርሳችሁ ተጠባበቁ::(1ኛ ቆሮ 11:33)
14:_እርስ በርሳችሁ እንደ ባሪያወች ሁኑ::(ገላ 5:13)
15:_እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፍፉ ተጠንቀቁ::(ገላ 5:15)
16:_እርስ በርሳችሁ በፍቅር ታገሱ::(ኤፌ 4:2)
17:_እርስ በርሳችሁ ቸሮችና ሩህሩሆች ሁኑ::(ኤፌ 4:32)
18:_እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ::(ኤፌ 5:19)
19:_እርስ በርሳችሁ ትዕግስትን አድርጉ::(ቆላ 3:13)
20:_እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገስፁ::(ቆላ3:16)
21:_እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተፅናኑ::(1ኛ ተሰ 4:18)
22:_እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ::(1ኛ ተሰ 5:11)
23:_እርስ በርሳችሁ በሰላም ሁኑ::(1ኛ ተሰ5:12-13)
24:_እርስ በርሳችሁ ለሁሉም መልካሙን ለማድረግ ትጉ::(1ኛ ተሰ 5:15)
25:_እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ::(ዕብ 3:13)
26:_እርስ በርሳችሁ አትተማሙ::(ያዕቆ 4:11)
27:_እርስ በርሳችሁ በሐጥያታችሁ ተናዘዙ::(ያዕቆ 5:16)
28:_እርስ በርሳችሁ እንግድነትን ተቀባበሉ::(1ኛ ጴጥ 4:9)
29:_እርስ በርሳችሁ አገልግሉ::(1ኛ ጴጥ 4:10)
30:_እርስ በርሳችሁ እየተዋደዳችሁ ትህትናን እንደ ልብስ ታጠቁ::(1ኛ ጴጥ5:5)

#አምላካችን እንደ ቃሉ እንኖር ዘንድ
ፍቅር፣ሰላም አንድነትን ያድለን!!!

"የጌታ የእየሱስ ክርስቶስ ፀጋ የእግዚአብሔርም
ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ህብረት ከሁላችን ጋር ይሁን::አሜን
2ኛ ቆሮ 13:14

    #shear .....
Join @ortodoxslijoch
7.4K views03:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 15:48:23 ​​​​ሰኔ 12 #የቅዱስ_ሚካኤል ዓመታዊ በዓል!

እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለእናታችን ቅድስት አፎሚያ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል እናታችን ቅድስት አፎሚያን ከጠላት ዲያብሎስ እጅ ያዳነበት ፣ እናታችን ቅድስት አፎሚያ እረፍቷ ነው ።እግዚአብሔር ከቅዱሱ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ፣ ከእናታችን ቅድስት አፎሚያ በረከት ተካፋይ ያድርገን ።

በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡

ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡

ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡

ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ ባያት ጊዜ ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ፣ ሌላ ባል አግብታ፣ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡

ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ፤ እነሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ፤ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡

በሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡

ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና “የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?” በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡

ለጊዜው “በኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም” ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን “ድረስልኝ” እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡

የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሠኔ ፲፪ ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡

ይህች የታመነች ቅድስት አፎምያ በሰላም እስክታርፍ ጊዜ ድረስ የተጓዘችበትን መንፈሳዊ ጎዳና አስተውለን ይሆን? አስቀድማ ከባሏ ጋር አንድ ሆና በታማኝነት ፈጣሪዋን አገለገለችው፡፡ በኋላም የባሏን ኑዛዜ አክብራ ምንም እንኳን ኃጢአት ባይሆንባትም በሁለተኛ ትዳር ራስዋን ማጠላለፍ አልፈለገችም፡፡ በጎ ሥራ አብልጣ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ተፋጠነች እንጂ፡፡

ሰይጣን ልጅ አለመውለዷን ተጠቅሞ ያቀረበላትን የጋብቻ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ “መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ መናፍስት ከእግዚአብሔር እንደሆኑ መርምሩ” ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የታዘዘውን መመሪያ ተጠቅማ ሰይጣንን በተወክሎ እግዚአብሔር ተቃውማ አሸነፈችው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን ርዳታ ያገኘችውና በሰላም ዐርፋ ወዳገለገለችው እግዚአብሔር በክብር የሔደችው በጽናት ተጋድላ ነው፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጸሎቷ ይማረን፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኃይል ሁላችንንም ይጠብቀን፣ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
           Join @ortodoxslijoch
8.4K views12:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 10:12:41 #የሰንበትን_ቀን_ትቀድሰው_ዘንድ_አስብ

‹‹ስድስት ቀን ስራ፣ተግባርህም ሁሉ አድርግ በሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፡፡እግዚአብሔርም በሰባተኛው ቀን አርፏልና ስለዚህ እግዚአብሔር የሰንበትን ቀን ባርኮታል ቀድሶታል፡፡ ›› (ዘጸ 20፡10-11)

#ሰንበት_ማለት_ምን_ማለት_ነው ?

ሰንበት ማለት አቆመ፣አረፈ ማለት ነው፡፡ይህ ቀን የጌታ ዕረፍት የተባረከም ቀን ነው፡፡ከማንኛውም ሥጋዊ ሥራ ተቆጥበን የእግዚአብሔርን ውለታ የምናስብበት ቀን ነው፡፡ ሰው እረፍት ያስፈልገዋል፡፡ የሰንበት ቀንም የተፈጠረው ለዚህ ነው፡፡ (ዘዳ 5፡14)፣(ማር 2፡38)
ከሳምንቱ ሰባት ቀናት መካከል ለእረፍት የተቀደሰው የተባረከው ዕለት ሰንበት ብቻ ነው፡፡ ስለሌሎች ቀናት የተነገረው ‹‹ ያ መልካም እንደሆነ አየ››የተባለው ብቻ ነው፡፡ ሰንበትን ግን ባርኮታል ቀድሶታል፡፡ (ዘፍ 1፡12፣ 18፡20፣ 25፡31)

በሐዲስ ኪዳን ለክርስቲያን ሁለት ሰንበት አለ ቀዳሚት ሰንበት(ቅዳሜ) እና ሰንበተ ክርስቲያን(እሑድ)
ቀዳሚት ሰንበት (ቅዳሜ)
ጌታ ያረፈባት ለእስራኤል ዘሥጋ የታዘዘው ሰንበት ነው፡፡ ይህ ቀን እስራኤላውያንን እግዚአብሔር አምላክ ከግብፅ ባርነት ወደ እረፍት እንዳወጣቸው ያመለክታል፡፡ዘዳ5-2-16 በእግዚአብሔር እና በህዝቡ መካከል ምልክት ነበረ ሰንበትን አለማክበር ግን ከባድ ቅጣት ያስከትል ነበር፡፡ (ዘጸ 3፡17) ፣ (ሕዝ 20፡12) ፣ (ዘኁ 15፡32-36)
ፈሪሳውያን በነበራቸው የተሳሳተ አመለካከት በሰንበት ቀን እንኳን መልካም ሥራን አይሰሩም ነበር፡፡ስለዚህም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ተወቅሰዋል፡፡ (ማቴ 12፡14) ፣ (ሉቃ 4፡16)

#ሰንበተ_ክርስቲያን_(እሑድ)

ይህች ቀን ለሳምንቱ መጀመሪያ፣ጌታችን ሥነ ፍጥረትን መፍጠር የጀመረበት ጌታ የተነሣበት፣መንፈስ ቅዱስ የወረደበት እንዲሁም ጌታችን ዳግመኛ በክብር የሚመጣበት ዕለት ስለሆነ ሰንበተ ክርስቲያን እንለዋለን፡፡ በሰንበተ ክርስቲያን (በጌታ ቀን) የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ልዩ ትኩረት በመስጠት ይሰባሰቡ ነበር፡፡ (ሐዋ 20፡7) ፣ገንዘብ ያዋጡበት ነበር (1ኛቆሮ 16፡2) ፣ በሥርዓተ ዓምልኮ የሚተጉበት፣የጌታችን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን የሚቀበሉበት ዕለት ነበር፡፡ (ዮሐ 20፡1-24) ፣ (ሐዋ 2፡11-14)

በቤተክርስቲያን ታሪክ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ዕለተ እሑድ የክርስቲያኖች ሰንበት ናት በማለት ሥራ እንዳይሰራባት አዋጅ አስነግሮ ነበር፡፡ ምንም እንኳን ይህቺ ዕለት በሐዲስ ኪዳን መከበር የጀመረ ቢሆንም በብሉይ ኪዳን ከፋሲካ በፊት የሰንበት (የቀዳሚት) ማግስት በመባል በኩራት እና ቀዳሚያት የሚያቀርቡበት ቀን ነበር፡፡ (ራዕ 1፡10)

በቀዳሚት ሰንበት ቅዱስ እግዚአብሔር ከሥራው ሁሉ አርፎ ሥጋዊ እረፍትን ለሰው እንዳስተማረ በዚህች ቀን (በሰንበተ ክርስቲያን) በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት የተገኘውን የዘላለማዊ የነፍስ ዕረፍት የምናስብበት ነው፡፡ (ዕብ 4፡1-10)

#የሰንበት_ቀን_መሰጠት_ዓላማ

የሰው ልጅ ባሕርይ ደካማ ነውና እግዚአብሔር ሰንበትን ሰራለት፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ደካማ ባህሪያችንን ስለሚያውቅ ከሳምንቱ ዕለታት አንዱ ሰንበት እድርጎ ለዕረፍት ሰጠን፡፡ ከድካማችን የተነሳ በዕለቱ መስራት አንችልምና ሰንበት ለሥጋችን ጠቃሚ ነው፡፡ ነገር ግን ሰንበት የተሰጠበት ምክንያት ሰው በዚህ ዓለም ሲደክም ስጋውን ብቻ ሲያገለግል እንዳይኖር የአምላኩን ውለታ እያሰበ በመንፈሳዊ አገልግሎት ፀንቶ እንዲኖር ነው፡፡ ዘጸ 5-14-15

ለምልክት

አምላካችን እግዚአብሔር እንደተናገረው ሁሉ ሰንበት የዘላለማዊ እና የመንፈሳዊ ዕረፍታት ምልክት ሆኖ የተሰጠ ጸጋ ነው፡፡ ዘጸ 31-13 ሰንበት ለሚመጣው ዘላለማዊ ዕረፍት ምሳሌ ሆኖ የተሰጠ የብሉይ ኪዳን ሕግ ነው፡፡ በህጉ መሰረት በሰንበት ዕረፍተ ሥጋ ይደረጋል፡፡ይህም ለኋላው ዘመን ለድኅነተ ነፍስ ምሳሌ ነው፡፡ በሐዲ ኪዳንም የተገለጠው የክርስቶስ ትንሳኤ በሰንበተ ክርስቲያን ተፈፅሟል፤ ሰንበተ ክርስቲያንም የሰው ልጆች ለዘለዓለም አርፈው ከእግዚአብሔር ጋር በደስታ የሚኖሩበት ምስጢረ ትንሣኤ የተገለጠባት የድኅነት ቀን ናት፡፡

#ሰንበትን_እንዴት_ማክበር_ይገባል?

ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰንበት ለመንፈሳዊ ሥራዎች(አገልግሎቶች) የተሰጠች መሆኗን ለማስተማር በሰንበት ድውያንን ይፈውስ፣ በምኩራብ እየተገኘም ያስተምር ነበር፡፡ (ዮሐ 5፡2-11 ፣9-14)፣(ሉቃ 14፡1-6)
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለመፍቅረ ሰንበት አይሁድ ስለሰንበት አከባበር ሲያስተምራቸው ‹‹ከእናንተ አንድ በግ ያለው በሰንበትም በጉ በጉድጓድ ቢወድቅበት ይዞ የማያወጣው ማን ነው? እንግዲህ ሰው ከበግ እንደምን አይበልጥም? ስለዚህ በሰንበት መልካም ሥራን መሥራት ተፈቅዷል›› ብሏል።

ማቴ12-10-13 ክርስቲያን ሰንበትን ሲያከብር እንደጌታችን ትምህርት መንፈሳዊ ሥራን በመሥራት ይገባል እንጂ ልክ እንደ አይሁድ ያጠፈውን ሳይዘረጋ የዘረጋውን ሳያጥፍ ሊያሳልፍ አይገባም፤ሰንበት ስለ ሰው ተፈጥሯል።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር!!!
    Join @ortodoxslijoch
6.1K views07:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-14 12:40:37 ሚስጥረ ስላሴ

ምስጢረ ሥላሴ፦ስለ ስላሴ ምስጢር የሚናገር ትምህርት ማለት ነው። እግዚአብሔር አንድነቱ ሦስትነቱን ሳይጠቀልለው፤ ሦስትነቱ አንድነቱን ሳይከፋፍለው በአንድነትና በሦስትነት የሚመሰገን አንድ ሕያው አምላክ ነው።

<= >የእግዚአብሔር ሦስትነት ስንል፦ እግዚአብሔር የማይለያይና የማይቀላቀል ፍጹም የሆነ ሦስትነት አለው ማለታችን ነው። የእግዚአብሔር ሦስትነት በስም በግብር  በአካል ነው።

<= >እግዚአብሔር በስም ሦስት ነው ስንል ሦስት የተለያዩ ስሞች አሉት ማለታችን ነው። እነዚህም፦ #አብ #ወልድ መንፈስ ቅዱስ  የሚባሉት ሲሆኑ እርስ በርሳቸው አይወራረሱም፤ አንዱ በሌላው ስም አይጠራም።  "ዘፍጥረት1፡ 2 "  "ምሳሌ30፡4" ።

>እግዚአብሔር በግብር ሦስት ነው፦ ስንል ሦስት የተለያዩ የአካል ሥራዎች አሉት ማለት ነው።  እነሱም፦
መውለድና ፤ማስረጽ የአብ
መወለድ፡ የወልድ
መስረጽ፡ የመንፈስ ቅዱስ ፤ የሚሉት ሲሆኑ የአካል ግብር ይባላሉ። "መዝሙር2፡7"
<=>እግዚአብሔር በአካል ሦስት ነው ማለት ደግሞ 
ለአብ፤ ፍፁም መልክ፤ ፍፁም ገጽ፤ ፍፁም አካል አለው። 

ለወልድ፤ ፍፁም መልክ፤ ፍፁም ገጽ፤ ፍፁም አካል አለው ።

ለመንፈስቅዱስ፤ፍፁም መልክ፤ ፍፁም ገጽ፤ ፍፁም አካል አለው ማለታችን ነው። <=>የሦስቱ የእግዚአብሔር ስሞችትርጉም

አብ፦ ማለት አባት ማለት ሲሆን የሚወልድ፤የሚያሰርጽ ወይም የሚያስገኝ ያለ እናት ወልድን የወለደ፤ መንፈስ ቅዱስን ያሰረጸነው።

ወልድ፦  ልጅ ማለት ሲሆን የሚወለድ ወይም ያለ እናት ቅድመ ዓለም፤ ያለ አባት ድህረ ዓለም  የተወለደ ነው። "መዝሙር2፡7" መንፈስቅዱስ፦ ረቂቅ፤ ልዩ፤ ንፁህ; ከፍጡራን መናፍስት ሁሉ የተለየ  ማለት ነው። "ኢዮብ26፡13"


የቅድስት ስላሴ እረድኤት
በረከታቸው አይለየን አሜን

አ       አ         አ
  ሜ        ሜ       ሜ
      ን        ን           ን

ሼር....ሼር...
              Join @ortodoxslijoch
8.8K views09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-03 19:57:16 ግንቦት 27 እንኳን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡

ቃሉ የግሪክ ሲሆን ትርጓሜውም አፅናኝ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው፡፡
☞ይህ በዓል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተነሣ በሃምሳኛው
በዐረገ በአሥራኛው ቀን በድምቀት ይከበራል፡፡
☞ለሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ የወረደው ከጠዎቱ ሦስት ላይ ነበር፡፡

☞ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ሐዋርያት በተናገረው
አምላካዊ ቃል መሠረት"ኃይልን እስክትለብሱ በኢየሩሳሌም ቆዩ" ብሏቸው ነበር
ሰዓቱ ሲደርስ የሚያጽናኑበት ብርታት የሚሆናቸው የዕውቀት፤ የኃይል መንፈስ
ቅዱስ ሰደደላቸው፡፡
☞"በዓለ ሃምሳም የተባለው ቀን በደረሰ ጊዜ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው
ሳሉ ድንገት እንደሚቃጠል ዐውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምጽ መጣ በሁሉም መንፈስ

ቅዱስ ሞላባቸው መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሠጣቸው በሌላ ልሣኖች ይናገሩ
ጀመር"(የሐዋርያት ሥራ 2፥1-11)
☞ይህችንም ዕለት ሊቃውንት የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን በማለት ይጠሯታል፡፡
☞ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "መንፈስ ቅዱስ በበዓለ ሃምሳ ባይወርድ ኖሮ
ቤተክርስቲያን በኮሰሰች ነበር"በማለት የበዓሉን ታላቅነት መስክሯል፡፡

☞" እግዚአብሔር ይላል በመጨረሻም ቀን እንዲህ ይሆናል እንዲህ ይሆናል
ሥጋ በለበሱ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ወንዶችና ሴቶች ልጆችሁም ትንቢት
ይናገራሉ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ ሽማግሌዎቻችሁ ሕልም ያልማሉ ደግሞም
በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎቼ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለለሁ የሚል

ትንቢት ይናገራሉ"(ትንቢተ ኢዮኤልምዕራፍ 2ከቁጥር 28)
☞መንፈስ ቅዱስ ለምን ይወርዳል?
☞መንፈስ ቅዱስ ሊያጽናና ሊረጋጋ እንደሚወርድ በወንጌል ተነግሯል፡፡
☞"አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነ አጽናኝ እርሱ ሁሉን
ያስተምራቸው እኔም እኔ የነገረሸኅችሁን ሁሉ ያሳስባችኃል፡፡(ዮሐ 14፥25)
☞ - - - እኔ ግን እውነት እነግራችኀለሁ፤ እኔ እንድሔድ ይሻላችኅል፡፡

እኔ
ባልሔድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣም፤እኔ ብሔድ ግን አርሱን እልክላችኀለሁ፡፡
(ዮሐ 16፥7)
☞ከዐረገ በኃላ መንፈስ ቅዱስ ሊያጽናናቸው እንሚመጣ ተናገረ፡፡
☞መንፈስ ቅዱስ ምሥጢር ሊገልጥ ይወርዳል፡፡
☞"የምነግራችሁ ገና ብዙ አለኝ ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም ግን
እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኅል፡፡(ዮሐ
16፥12-13)

☞"እንዲህ አላቸው ወደ ዓለሙ ሁሉ ሒዱ ወንጌልን ለፍጥረት ስበኩ(ማር
16፥15)ብሎ በዓለም ሁሉ ያለውን ቋንቋ እንዲያውቁ አድርጎ ወንጌልን ለአለም
እንዲሰብኩ ልኳቸዋል፡፡
☞ለሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ በወረደበት እለት የተለያዩ ቋንቋ ተገልጦላቸዋል፡፡
(ሐዋ 2፥3)
☞እኛም ጰራቅሊጦስ ለዋርያት መንፈስ ቅዱስ የወረደበት፤ የቤተክርስቲያን
ልጆች መሠረት የተጣለበት ቀን በመሆኑ መንፈስ ቅዱስ ያጸናን፤ ይቀድሰን፤
ምሥጢሩን ይገልጥልን ዘንድ በማሰብና በመማፀን በዓሉን እናከብራለን፡፡

(ከመድበለ ታሪክ መጽሐፍ የተወሰደ)
☞ጰራቅሊጦስ የወርቅ ሐር ግምጃ የቅዱሳን የጌጣቸው ልብስ ነው፡፡
☞ጰራቅሊጦስ የጻድቃን የባለሟል ነታቸው የራስ ወርቅ ነው፡፡
☞ጰራቅሊጦስ ሐዋርያትን በሀገሩ ሁሉ ቋንቋ ያናገረ ነው፡፡
☞ጰራቅሊጦስ ሐዲስ ወንጌልን ያስተማረ ዘንድ ጳውሎስን የጠቀሰ የሕይወት
መብረቅ ነው፡፡
☞ጰራቅሊጦስ ሐዋርያትን የወይን ጠጅ ሳይጠጡ ያሰከረ ነው፡፡

☞ጰራቅሊጦስ በጽዮን አደባባይ በቶማስ ላይ በቅዱስ ነቢይ ፊት የበራ ነው፡፡
☞ጰራቅሊጦስ ፍጹም የከበረ የአብና የወልድ የባሕርይ ሕይወት ነው፡፡
☞ጰራቅሊጦስ የማይዳሰስ የእሳት ነበልባል ነው፡፡
☞ጰራቅሊጦስ መጉደል ወይም መጨመር ሳይኖርበት በህልውናው አምላክ
ነው፡፡
☞ጰራቅሊጦስ እንደ አብና እንደ ወልድ በሰማያትና በምድር ሁሉ ላይ መንግሥቱ
የመላ ነው፡፡

☞ጰራቅሊጦስ አሸናፊ ነው ለሰማዕታት መመኪያ የተሰበሩትን የሚጠግን ነው፡፡
☞ቅድመ ዓለም ለነበረ ፍጹም አንድነቱ ለሱ ስግደት ይገባል ዛሬም ዘወትርም
ለዘላለሙ አሜን፡፡(የሀሙስ ሰይፈ ስላሴ)
☞ለእኛም ወደ አንተ የሚወሰደውን ቀናውን መንገድና የሀይማኖት ጽናቱን እና
ማስተዋል ግለጽልን፡፡መልካም በዓል ይሁንላችሁ፡፡
4.5K views16:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 06:05:59 ክፍል 2 #ሼርርርርርርርር

1 ሩሐማ፦ምሕረት ማለት ነው።
2 ዮዳሔ፦እግዚአብሔር ያውቃል ማለት ነው።
3 ቴዎፍሎስ፦የእግዚአብሔር ወዳጅ ማለት ነው።
4 ኑኃሚን፦ደስታየ ማለት ነው።
5 ናትናኤል፦የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው።
6 አዛሄል፦እግዚአብሔር ያያል ማለት ነው።
7 ኢዮስያስ፦እግዚአብሔር ይደግፋል ማለይ ነው
8 ኢዩኤል፦እግዚአብሔር አምላክ ነው ማለት ነው።
9 በርናባስ፦የመጽናናት ልጅ ማለት ነው።
10 ሶፎንያስ፦እግዚአብሔር ሰውሯል/ጠብቋል ማለት ነው።
11 ሕዝቅኤል፦እግዚአብሔር ብርታትን ይሰጣል ማለት ነው።
12 ኬልቅያስ፦እድል ፈንታየ እግዚአብሔር ማለት ነው
13 ሳሙኤል፦እግዚአብሔር ሰማኝ ማለት ነው።
14 ሚኪያስ፦ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው! ማለት ነው።
15 ሆሴዕ፦እግዚአብሔር ያድናል ማለት ነው።
16 ሔዋን፦የሕያዋን ሁሉ እናት ማለት ነው።
17 ሕዝቅያስ፦እግዚአብሔር ኃይሌ ነው ማለት ነው።
18 መልከጼዴቅ፦የሰላም ንጉሥ ማለት ነው።
19 ሚልኪያስ፦መልእክተኛየ ማለት ነው።
20 ሣራ፦ልዕልት ማለት ነው።
21 ስምዖን፦ሰማ ማለት ነው።
22 ብንያም፦የቀኝ እጄ ልጅ ማለት ነው።
23 ናሆም፦መጽናናት ማለት ነው።
24 ናታን፦ እግዚአብሔር ሰጥቷል ማለት ነው።
25 አልዓዛር፦እግዚአብሔር ረድቷል ማለት ነው።
26 አስቴር፦ኮከብ ማለት ነው፣
27 አቤሜሌክ፦የንጉሥ አገልጋይ ማለት ነው።
28 አቤሴሎም፦አባቴ ሰላም ነው ማለት ነው።
29 አብድዩ፦የእግዚአብሔር አገልጋይ ማለት ነው።
30 አብራም፦ታላቅ አባት ማለት ነው።
31 አብርሃም፦የብዙዎች አባት ማለት ነው
32 አኪያ፦እግዚአብሔር ወንድሜ ነው ማለት ነው።
33 አክዐብ፦የአባት ወንድም ማለት ነው።
34 ባሮክ፦ቡሩክ ማለት ነው።
35 አዳም፦መልካሙ ማለት ነው።
36 ኢሳይያስ፦ እግዚአብሔር ደኅንነት ነው ማለት ነው።
37 ባርቅ፦መብረቅ ማለት ነው።
38 ኢያሱ፦እግዚአብሔር አዳኝ ነው ማለት ነው።
39 ኢዮሳፍጥ፦እግዚአብሔር ፈርዷል ማለት ነው።
40 ኢዮራም፦እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ ማለት ነው።
41 ኢዮርብዓም፦ሕዝቡ እየበዛ ይሄዳል ማለት ነው።
42 ቤተልሔም፦የእንጀራ ቤት ማለት ነው።
43 ኢዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል ማለት ነው።
44 ኢዮአቄም፦እግዚአብሔር አቆመ ማለት ነው።
45 ኢዮአብ፦እግዚአብሔር አባት ነው ማለት ነው።
46 ኢዮአታም፦እግዚአብሔር ፍጹም ነው ማለት ነው።
47 ኢዮአካዝ፦እግዚአብሔር ይዟል ማለት ነው።
48 ኤልሳዕ፦እግዚአብሔር ደኅንነት ነው ማለት ነው።
49 ኤልያስ፦እግዚአብሔር አምላክ ነው ማለት ነው።
50 ኤልያቄም፦እግዚአብሔር ያስነሳል ማለት ነው።
51 ኤዶም፦ቀይ ማለት ነው
52 እስራኤል፦ከእግዚአብሔር ጋር ይታገላል ያሸንፍማል ማለት ነው።
53 ኤልሳቤጥ፦እግዚአብሔር መሐላየ ነው ማለት ነው።
54 ኤልሻዳይ፦ሁሉን ቻይ አምላክ ማለት ነው።
55 ሀሌሉያ፦እግዚአብሔርን አመስግኑ ማለት ነው።
56 ሰሎሞን፦ሰላማዊ ማለት ነው።
57 ኬብሮን፦ኅብረት ማለት ነው
58 አዛርያስ፦እግዚአብሔር ረድቷል ማለት ነው።
59 ኤደን፦ደስታ ማለት ነው።
60 ዖዝያን፦እግዚአብሔር ኃይሌ ነው ማለት ነው።
61 ዘካርያስ፦እግዚአብሔር ያስታውሳል ማለት ነው።
62 ይሳኮር፦ ዋጋዬ ማለት ነው
63 ይዲድያ፦በእግዚአብሔር የተወደደ ማለት ነው።
64 ዮሐናን፦እግዚአብሔር ጸጋ ሰጪ ነው ማለት ነው።
65 ዮሐንስ፦እግዚአብሔር ጸጋ ነው ማለት ነው።
66 ዮሴፍ፦ይጨምር ማለት ነው።
67 ዮናስ፦ርግብ ማለት ነው።
68 ዮናታን፦እግዚአብሔር ሰጥቷል ማለት ነው።
69 ዮአኪን፦እግዚአብሔር ያቆማል ማለት ነው።
70 ዮካብድ፦እግዚአብሔር ክብር ነው ማለት ነው።
71 ምናሴ፦ማስረሻ ማለት ነው።
72 ዮፍታሔ፦እግዚአብሔር ይከፍታል ማለት ነው።
73 ዲቦራ፦ንብ ማለት ነው።
74 ዳንኤል፦እግዚአብሔር ፈራጅ ነው ማለት ነው።
75 ጎዶልያስ፦እግዚአብሔር ታላቅ ነው ማለት ነው።
76 ጽዮን፦አምባ ማለት ነው።
77 ጳውሎስ፦ብርሃን ማለት ነው።
78 ሴት፦ምትክ ማለት ነው።
79 ጴጥሮስ፦አለት ማለት ነው።
80 ሄኖክ፦ታደሰ ማለት ነው።
81 ኄራኒ፦ሰላም እና ፍቅር ማለት ነው።
91 ሐና፦ጸጋ ወይም ስጦታ ማለት ነው።
92 ሮቤል፦እነሆ ወንድ ልጅ ማለት ነው።
93 ኤርምያስ፦እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል ማለት ነው።
94 ሮብዓም፦ሕዝብ ይብዛ ማለት ነው።
95 ማራናታ፦ጌታ ሆይ ና ማለት ነው።
96 ቤቴል፦የእግዚአብሔር ቤት ማለት ነው።
97 ቄርሎስ፦የተመረጠ ምርጥ ማለት ነው።
98 እስጢፋኖስ፦አክሊል ማለት ነው።
99 ሳውል/ሳኦል፦ከእግዚአብሔር የተለመነ ማለት ነው።
100 ሴዴቅያስ፦የእግዚአብሔር ጽድቅ ማለት ነው።
           join @ortidoxslijoch
4.3K views03:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ