2023-01-19 21:19:43
ቃና ዘገሊላ ምንድን ነው ?
ቃና ዘገሊላ በቀጥታ ትርጉም የገሊላዋ ቃና ማለት ነው ።
እንደ
ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን አስተምሮ በጥምቀት
በአል ማግስት ጥር12 ቀን የቃና ዘገሊላ በአል ይከበራል ።ይህ
በዓል ከጌታ ጥምቀት በዓል ጋር ተያይዞ በድምቀት የሚከበር
መፀሀፍ ቅዱሳዊ በዓል ነው ።በዓሉ ቃና ዘገሊላ የሚል ስያሜ
ያገኘው ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስየገሊላ ሀገር ክፍል
በምትሆንቃና በተባለች ቦታ በፈፀመው ተአምር መነሻነት ነው ።
ቃና ዘገሊላ ምን ተፈፀመ ?
ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ክፍል በምትሆን
በቃና በዶኪማስ ቤት ሠርግ ላይ ከእናቱ ከድንግል ማርያም
ጋርተገኝቶ ነበር ። "ወሀለወት ህየ እሙ ለእግዙእ ኢየሱስ" የጌታ
የኢየሱስ እናትም በዚያ ነበረች "እዳለ ቅዱስ ዮሐንስ 2፥1 ።
እመቤታችን ለሠርገኞቹ ዘመድ ነበረችና ከልጃ ከወዳጃ ከኢየሱስ
ክርስቶስ ጋር በሠርጉ ላይ ታድማ ነበር ።
እናትን ጠርቶ ልጅን
መተው ሥርአት ሥላልሆነ፤በተጨማሪም ደግሞደቀመዛሙርቱን
ከጌታ ጋር ታድመዋል ። ይህም መምህርን ጠርቶ ደቀ መዛሙርቱን
መተው ሥርአት ሥላልሆነ ነው ።
የሠርጉ ስነ ስርአት በሰመረ ባማረ ሁኔታ እየተከናወነ ሳለ ድንገት
የወይን ጠጅ አለቀ ።
አስተናባሪዎቹ በጭንቀት ባህር ስጥመው
ምን እንደሚያደርጉ ግራ በገባቸው በጠበባቸው ጊዜ የችግር ጊዜ
ደራሽ የሀዘን ጊዜ አፅናኝ የሆነችው የአምላክ እናት ድንግል
ማርያም ቅድስ ገብርኤል እንደተናገረ በፀጋ የተሞላች ናትና ሉቃ
1፥28 ማንም ሳይነግራት የልቦናቸውን ጭንቀት አይታ ጎዶላቸውን
ተመልክታ ወደ ልጃ ወዳጃ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘወር ብላ "ወይንኬ
አልቦሙ " "ወይን ጠጅ እኮ አልቆባቸዋል" አለችው ። እርሱም
መልሶ "አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም
"አላት ።እመቤታችንም ለአገልጋዮቹ "የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ "
አለቻቸው ።
ጌታም በቦታው የነበሩትን ስድስት ጋኖች ውሀ
ሞልተው እዲያመጡ አዘዛቸው ። ውሀውንም ወደ ወይን ለውጦ
ለሊቀ ምርፋቃት( ለአሳዳሪው) እዲሰጡት አዘዘ ። አሳዳሪውም
ወደ ወይን የተለወጠውን ውሀ በቀመሰ ጊዜ አደነቀ ።
ከወዴት
እደመጣ ስላላወቀ ሙሽራውን " ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን
የወይን ጠጅ ያቀርባል ከሰከሩም በኅላ መናኛውን ያቀርባል አንተ
ግን መልካሙን እሰከ አሁን አቆይተሀል"አለው ። ወይኑም በስው
እጅ ያይደል በሰማያዊው አባት የተዝዘጋጀ ሰለነበር ጣፋጭ እና
ልብን የሚያስደስት ነበር ።
"አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ ?" ይህንን የጌታችንን ንግግር
ብዙዎች በዘመናችን ሣሣቱበት ይታያንል ። ክብር ይግባውና
አምላካችን ይህንን የተናገረው እናቱን ሊያቃልል ሽቶ አይደለም ።
ስለሆነም ከመፀሐፍ ቅዱስ አንፃር ይህንን አረፍተ ነገር መመልከቱ
በጣም ጠቃሚ ነው ። በተናጥል ስንመለከት "አንቺ ሴት " ሴት
የሚል ቃልየፆታ መጠሪያ ነውና በፆታዋ አክብሮ ሲጠራት ነው ።
በሌላ በኩል ደግሞ ሔዋን ከአዳም በተፈጠረች ጊዜ አዳም
እንዲህ ሲል ተናግሮ ነበር "ይህቺ አጥንት ከአጥንቴ ናት ስጋዋም
ከስጋዬ ናት እርሳም ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል "ዘፍ.2፥23
በመሆኑም ጌታችን አንቺ ሴት ማለቱ ከስጋዋ ስጋ ከነፍሳ ነፍስ
መንሳቱን ለማጠየቅ ነው ።
" ከአንቺ ጋር ምን አለኝ ?"የሚለውን አረፍተ ነገር የንቀት
ሰለመስለን ብቻ የዳቦ መልክ የያዘ ድንጋይ ፤ ዳቦ ነው እደማይባል
የንቀት ንግግር ነው ልንል አይገባም ። ጌታም እዲህ ሲል
ውሀውን ወይን እድርግላቸው ብትይኝ አላደርግም እልሽ ዘንድ
ከአንቺ ጋር ምን ፀብ አለኝ ማለቱ ነው።
ድንግል ማርያም አማላጅነት በገሊላ ቃና ጌታችን መድሀኒታችን
ኢየ�ሱስ ክርስቶስ በሠርግ ቤት ሳለ የወይኑን ማለቅ
የማይመለከት ሆኖ አይደለም ። ነገር ግን የእናቱን የድንግል
ምርይምን አማላጅነት ሊገልጥ ስለ ወይኑ ማለቅ እስክትነግረው
ድረ�ስ አንዳች ነገር አላደረገም ። ኅላ ግን የጭንቅ አማላጅ
ድንግል ማርይም ስለ ወይኑ አስብች ልጃ ወዳጃን ለመነች ።
እር�ሱም የእናቱን ልመና ተቀብሎተአምራቱን ፈፀመ ።
እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሳይነግራት በልብ ያለውን
የምታቅ የምትመረምር እናት ናትና የሰርጉ አስተባባሪዎች ይህ
ጎደለ ሳይላት የልቦናቸውን ሀዘን ተመልክታ ከልጃ ከወዳጃ
አማልዳ የጎደላቸውን ሞልታለች ።
ያሰጨነቃቸውንም አርቃለች
በችግራቸውም ደርሳላቸዋለች ። ታዲያ ሳይነግራት የልቦናን አይታ
ከማለደች ስሟን ጠርተው ለሚለምኗትማ እንዴት አብልጣ
አታማልድ ?
ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤቷን
በረከቷንያሳድርብን አሜን !!!
join @ortodoxslijoch
1.3K viewsedited 18:19