Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxslijoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.17K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ምንማማርበት :መዝሙር: ስብከቶች ይተላለፋል !

መንፈሳዊ ትምህርቶች : መንፈሳዊ ጥያቄዎች : ስብከት : መዝሙር : ይቀርብበታል #ጉዞው ገዳማት #ሰማህታት ታሪክ ይቀርባል!
FacebookGroup : ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ይቀላቀሉ ::

#shear

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-04-05 06:24:45 #መድሃኒአለም ማለት የአለም ሁሉ መድሃኒት ማለት ነዉ
ስጋዉን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ለኛ ሲል ህይወቱን የሰጠ

፨ አሮንና ልጆቹን ....... ለክህነት የመረጠ
፨ ኤልያስን ....... በአዉሎ ነፋስ የነጠቀ
፨ እዮብን ....... በባእድ ሀገር ከፍ ከፍ ያደረገ
፨ ሎጥን ........ ከእሳት ያወጣ
፨ ለሳምሶን ........ ሀይልን የሰጠ
፨ አዛርያን አናንያን ሚሳኤልን ....... ከእሳት የታደገ
፨ ጥበብና ማስተዋልን ....... ለሰለሞን የሰጠ
፨ ያዕቆብን ....... በመንገዱ የጠበቀ እና የባረከ
፨ እስራኤልን ....... ከግብፅ ባርነት ያወጣ
፨ ለሙሴ ....... ጽላት የሰጠ
ለኪሩቤል ላይ የተቀመጠ ክብሩንም የገለጠ ስጦታዉ የማያልቅበት

#ቸሩ_መድሃኒአለም_ይክበር
_ይመስገን_አሜን /፫/
#መድኃኒአለም _የገዢዎች ሁሉ ገዢ
#መድኃኒአለም ____ የነገስታት ሁሉ ንጉስ
#መድኃኒአለም ____ የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ ነዉ
ኃይሌን ጉልበቴን ታድሳለህ
ቀና ቀና እንድል ታደርጋለህ
መድኃኒአለም መድኃኒቴ

መ ____ መሃሪ ይቅር ባይ አምላክ
ድ ____ ድካሜን ተመልከት ስለዉ ተበርክኬ
ኃ ____ ኃያላት የማይችሉህ የኃያላን ኃያል
ነ ____ ነፍሴ ትልኃለች ጌታዬ ይረዳኛል
አ ____ አለምን ለማዳን መስቀል ላይ የዋለ
ለ ____ ለዘላለም ፍቅር ነህ ሁሌ የማትቀየር
ም ____ ምህረትህ የበዛ
#የድንግል_ማርያም_ልጅ_ቸሩ_መድኃኒአለም_አንተ_ነ
ህ_አባቴ !!

ቸሩ መድኃኒአለም በያላቹሁበት ይጠብቃችሁ ወጥቶ ከመቅረት ከድንገተኛ አደጋ ይጠብቃችሁ አሜን/፫/
የሚያኖረን ሰዉ ሳይሆን የአለም መድኃኒት የሆነዉ ለእኛ ሲል የእሾህ አክሊል የደፈዉ ቸሩ መድኃኒአለም ነዉ።
ቸሩ መድኃኒአለም ሃገራችን ይጠብቅልን
የዲያብሌስ ስራ እጅግ ተስፋፍቶብን
የሰዉኛ ዘይቤዉ ከእኛ ዘንድ ጠፍቶብን
ምግባራችን ከፍቶ ትዛዝህን ሽረን
..... በበደል ጨቂተን

ዉስጣችን ሲያነባ ካንተ ተሰዉረን
ለሰዉ ልጅ ነዉና ደምህ የፈሰሰዉ
በምህረት እጆችህ እንባችን አብሰዉ
ምስጋና ይሁን ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ጥንት ለነበረ አሁንም ላለ ኋላም የሚኖር ስሙ የተመሰገን ይሁን አሜን
፫ 
         Join @ortodoxslijoch
65 views03:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 07:13:42 በጾም ወቅት ለምን የእንስሳት ውጤት አንመገብም?
ለምን የአትክልት እና ጥራጥሬ ውጤቶችን ብቻ እንጠቀማለን?

በመጀመሪያ ደረጃ ሁሉም ሊያውቀው የሚገባ ነገር በቤተክርስቲያናችን ጾም ማለት "ከእንስሳት ውጤት ከሆኑ ምግቦች ታቅቦ ቀኑን ሙሉ አትክልት፣ ሽሮ፣ የጾም ፍርፍር እየበሉ ሳይጾሙ እና ሳይጸልዩ ፈቃደ እግዚአብሔር ያልሆኑ ነገሮችን እየፈጸመው መዋል አይደለም!
ይህ መታወቅ አለበት!

ለኛ ጾም ማለት ምንም ነገር ከመብላት ከተወሰነ ሰዓት በመታቀብ እና በመጸለይ መቆየት ነው ባጠቃላይ ሰጋን በፈቃደ ነፍስ ማስገዛት ከዛ የአትክልት ውጤት የሆኑ ምግቦችን (ከእንስሳት ውጤቶች ነጻ የሆኑትን) በመጠኑ መመገብ ነው!"
=> አባቶቻችን እንደተማርነው ከእንስሳትና ከእንስሳት ውጤቶች፣ እንዲሁም ከሌሎች ለሥጋ እጅግ ከሚመቹ ምግቦች እንርቃለን፤
ዳንኤል፥ በዚያም ወራት እኔ ዳንኤል ሶስት ሳምንት ሳዝን ነበርሁ። ማለፊያ እንጀራ አልበላሁም፣ ሥጋና ጠጅም በአፌ አልገባም። ሶስቱም ሳምንት እስከፈጸም ድረስ ዘይት አልተቀባሁም" /ዳን. 10-3/። እንዲል
ዳዊት፥ ሥጋዬ ቅባት በማጣት ከሳ፣ ጉልበቶቼም በጾም ደከሙ"/ መዝ. 108-24/።
እንዲል
ለምን የአትክልት ውጤቶች ብቻ?
1.የአትክልት ምግቦች እግዚአብሔር ለአዳም እና ለሔዋን በገነት እያሉ እንዲበሉ የሰጣቸው ምግብ ነው።
(እግዚአብሔርም አለ። እነሆ መብል ይሆናችሁ ዘንድ በምድር ፊት ሁሉ ላይ ዘሩ በእርሱ ያለውን ሐመልማል ሁሉ፣ የዛፍን ዛሬ የሚያፈራውንና ያለውንም ዛፍ ሁሉ ሰጠኋችሁ ዘፈ 1:29)
ሁሉም እንስሶች አትክልት ብቻ እንዲመገቡ የእግዚአሔር ትዕዛዝ ነበር (ለምድርም አራዊት ሁሉ፥ ለሰማይ ወፎች ሁሉ ሕያው ነፍስ ላላቸው ለምድር ተንቀሳቃሾችም ሁሉ የሚበቅለው ሐመልማል ሁሉ መብል ይሁንላቸው፣ እንዲሁም ሆነ ዘፍ 1:30
አዳም እና ሔዋን ሀጥያት ሰርተው ከገነት ከተሰደዱም በኋላ እግዚአብሔር አትክልት (ተክል) እንዲመገቡ የሰጣቸው የተክልን ውጤት ነው (የምድርንም ቡቃያ ትበላለህ
ዘፍ 3:18

2.እንስሳት መብላት እስከ ጥፋት ውሃ ድረስ ክልክል ነበር!
ከጥፋው ውኃ በኋላ እግዚአብሔር ለኖህ እንስሳትን እንዲመገብ ፈቀደለት
(ሕይወት ያለው ተንቀሳቃሽ ሁሉ መብል ይሁናችሁ፣ ሁሉን እንደ ለመለመ ቡቃያ ሰጠኋችሁ። (ዘፍ 9:3)

3.እግዚአብሔር ህዝቦቹ ወደ ሲና ምድረበዳ ሲጓዙ ሳሉ ከሰማይ ያወረደላቸው ምግብ (መና) የተክል ዘር ነው መናውም እንደ ድንብላል ዘር ነበረ፣ መልኩም ሙጫ ይመስል ነበር። ሕዝቡም እየዘሩ ይለቅሙ ነበር፣
በወፍጮም ይፈጩት ወይም በሙቀጫ ይወቅጡት ነበር.....
ዘኀ 11:7
እግዚብሔር ሥጋን ለጊዜው አልሰጣቸውም ነበር በዚህም ምክንያት ያንጎራጉሩ ያኮርፉ እግዚአብሔር ያወረደውን ሥጋ ሲበሉ ተቀጡ
ሥጋውም ገና በጥርሳቸው መካከል ሳለ ሳያኝኩትም የእግዚአብሔር ቁጣ በሕዝቡ ላይ ነደደ እግዚአብሔርም ሕዝቡን በታላቅ መቅሠፍት እጅግ መታ። ዘኀ 7:33

4.ዳንኤል እንዲሁም አናንያ ሚሳኤልና አዛርያ ጥራጥሬ እና ውሃ ብቻ እየበሉ ነበር የጾሙት ግን ስጋ እና ጥሩ የሚባሉ ምግቦች ከተመገቡት በላይ አምሮባቸው እና ወፍረው ታዩ (ዳን፤ 12-15
ዳዊት ሲጾም እንደት እንደሆነ ሲነገር ጉልበቶቼ በጾም ደከሙ ሥጋዬም ቅቤ በማጣት ከሳ" ብሏል መዝ 109-24

* ቤተክርስቲያን የእንስሳት ውጤትን ባጠቃላይ አትመገቡ አትልም፣ ለጾም ወቅት ብቻ እንጂ። እግዚአብሔር ከፈጠረው መብል እንዲርቁ ሰዎችን አታዝም። እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም ነውና በስርዓቱ እና ለመንፈስ በማድላት የሥጋን ፍላጎት በመቀነስ እንድንጠቀም ትመክረናለች።

ቤተክርስቲያን የእንስሳት ውጤቶች እርኩስ እና የተረገሙ ምግቦች ናቸው ብላ አታስተምረም እንደዛ ብታስተምርም ኖሮ የጾም ቀናቶች ሲገባደዱ ባለተመብናቸው ነበር። ለጥቂት ጊዜ ከእንስሳት ውጤቶች እነ ቅዱስ ዳንኤል፣ ዳዊት ርቀው ነበር ግን ርኩስ ምግቦች ናቸው ብለው አልነበረም!
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት
የሲኦል ደጆች አያናውጧትም
ቤተክርስቲያን አ ት ታ ደ ስ ም!
ፀልዩ በእንተ ሰላማ ቤተክርስቲያን አሐቲ ቅድስት ጉባኤ እንተ ሐዋርያት ርትዕት በኅበ እግዚአብሔር! የሐዋርያት ጉባኤ ስለሆነች ስለአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም እንማልዳለን! (መጽሐፈ ሚስጢር)
ቤተክርስቲያን
መሰረቷ ጉልላቷ እርሱ ነው
ሙሽራው መስቀል ላይ የሞተው
ዛሬም ነገም ያው ነው ለዘላለም
አትንገሩን አዲስ ጌታ የለም
ወሰብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን፫ ይቆዬን።
   
2.4K views04:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 08:28:05 እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን የአብይ ፆም ሰባተኛው ሳምንት
"ኒቆዲሞስ" ይባላል።
              ◄◉►ኒቆዲሞስ◄◉►

ኒቆዲሞስ ማለት :- በቤተክርስቲያን ሰባተኛው የዐቢይ ጾም ሳምንት ኒቆዲሞስ ይባላል።

ትርጓሜው የአይሁድ መምህር ወይም ደሞ የጌታችን ደቀ መዝሙር የሌሊቱ ተማሪ ማለት
ነው።

ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ ነው።ዮሐ 3:1
ኒቆዲሞስ የአይሁድ አለቃ ነው።ዮሐ 3: 1
ኒቆዲሞስ መምህረ እስራኤል ነው።ዮሐ 3:10
ኒቆዲሞስ ምሁረ ኦሪት ነው።የሐ 7:51

ኒቆዲሞስ በኢየሩስ አሌም በሀብት በእውቀት ዝና በስልጣን የታወቀ ነው።ኒቆዲሞስ ስለ ሶስት ነገር ሌሊት ሌሊት እየሄደ ከጌታ እግር ስር ይማር ነበር።

1 አይሁድ ፈርቶ:-በዛን ሰአት በአይሁድ ህግ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር የሆነ ሀብት ንብረቱ ስለ ሚቀማ ከነሱ ለመሸሽ ሌሊትን መረጠ።
2,ውዳሴ ከንቱን ሽቶ:-በወቅቱ የነበረ እውቅ ሊቅ ነበርና
እንዴት ከመምህር ስር ይማራል እንዳይሉት።
3 ልቡናው እንዲሰበሰብ:-ከቀን ይልቅ ሌሊት የአይምሮ
እረፍ ስላላት እሱን ሽቶ ነው።

ኒቆዲሞስ ከጌታ እግር ስር ቁጭ ብሎ ስለ ምስጢረ ጥምቀትና ዳግመኛ ልጅነት የፅድቅ ስራ በሰፊው ተምሮአል።ዮሐ ም 3፡ 1-12
ወስብሐት ለ እግዚአብሔር

   Join @Ortodoxslijoch
2.9K views05:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 16:58:05 አንብቡት
#ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሊያውቀውb የሚገባ ግደታ
ይህን ያውቁ ኖሯል???
አሐዱ ተብሎ ቅዳሴ ከተገባ በኋላ (በቅዳሴ ሰዓት)
አንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መዘዋወር፣ ቅዳሴ አቋርጦ መውጣት
የግል ጸሎት ማድረግ፣ የጸሎት መጽሐፍትን ማንበብ፣
ሳቅ ወሬ፣ ሞባይል ማስጮህና ማነጋገር
ምግብ ይዞ ወደ ቤተ መቅደስ መግባት
ወደ አውደ ምሕረት አካባቢ መጠጋት
እህቶች ሱሪ አድርገው መምጣት እንዲሁም ፀጉርን በሚገባ ሳይከናነቡ ለቅዳሴ ጸሎት መቆም
ልጆችን ያለ ነጠላ ማቁረብ
ቅዱስ ቁርባን በሚሰጥበት ግዜ ስነ~ ስርዓቱን በቪዲዮ ፎቶ ካሜራ እና በሞባይል መቅረጽና ማንሳት ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑን ያውቃሉ።
በተጨማሪ ህፃናትን ማቁረብ ሲያስቡ በተቻለን መጠን ካህናት ቅዳሴ ከመግባታቸው በፊት ይዘዋቸው ወደ
ቤተ መቅደስ ቢደርሱ መልካም ነውና ዘወትር ይህንን ተግባራዊ ያድርጉ።
ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምታደርጉ፣ የምታደርጉትን ሁሉ በትጋት አድርጉ።
         
3.0K views13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 06:38:11 ኪዳነ ምህረት

ኪዳነምህረት ስንል የምህረት ቃልኪዳን ማለት ነው፡፡በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው፡፡


  እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምድራዊ ቆይታዋ ዘውትር ወደ ክርስቶስ መካነ መቃብር ጎለጎታ እየወረደች ትፀልይ ነበር፡፡ ልጇ እና ወዳጇ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገችው ልመናና ፀሎት ተመልክቶና ሰምቶ የምህረት ቃል ኪዳን ገባለት ፡፡


እንኳን የእናቱን ፀሎት እና ልመና ቀርቶ ዘውትር በሀጥያት የምንዘፈቀውን እኛን ክፉዎቹን የሚሰማ አምላክ ስለ አንቺ ፣ ስለ እናቴ ክብርና ፀጋ ስል ይኸው ቃሌ ብሎ ቃልኪዳን አደረገ፡፡
« ከመረጥሁት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ። … » መዝ, 89 : 3 እንዲል መፅሐፉ፡፡

ስሟን ለሚጠሩ፣ በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት ቃልኪዳን ሰጥቷታል ፡፡

ታላቁ መፅሐፍ እንዲህ ይላል፦
". . . ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ። " ኦሪት ዘፍ. 9 : 16

በዚህም መሠረት ቃልኪዳኗን ምክንያት በማድረግ ኪዳነ-ምህረት እያልን እንጠራታለ

እንኳን ለ«ኪዳነምህረት» አደረሳችሁ። የእመቤታችን ምህረት እና ረድዔት፤በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን!!!
         @ortodoxslijoch
         @ortodoxslijoch
1.4K views03:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 06:34:07 የተስፋ ቃላት

እኛ ዛሬ ወደፊት የምንኖርባት #የእግዚአብሔር ሀገር በተስፋ ዓይኖቻችን ልንመለከት እንጂ ይሁን ሁካታና ግርግር የበዛበት ዓለም ልንመለከት አይገባም።

ለእኛ በጣም አስቸጋሪ መስሎ የሚታየን ችግር #በእግዚአብሔር ዘንድ መፍትሔ አሉትም። ማንኛውም የተዘጋ በር ለመክፈት በእግዚአብሔር ዘንድ ያለው ቁልፍ አንድ ብቻ ሳሆን ብዙ ቁልፎች ናቸው። በእንደዚህ ዓይነት መንገድ የተከፈተውን ማንም ሊዘጋው አይችልም ፡፡ ራዕ 3፥7።

ተስፋ ፍርሀትን ጭንቀትን ግራ መጋባትን በመከላከል ዕረፍትን ይሰጣል።ተስፋ ዕረፍትን ከመጠቱ በላይ በተስፋ ደስ እንዲለን ተነግሮናል። ሮሜ 12፡2

መጥፎውን ወደ በጎ መቀየር የሚቻለውን #የእግዚአብሔር አሠራር ሳትይዝ ወደ ችግሮችህ ብቻ አትመልከት።

#እግዚአብሔር ሁሉም አጋጣሚዎች እርሱ በወደድው መንገድ ማስኬድ ይቻለዋል።

በሰዎች ድካም ሊደረግ የማይቻለው ሁሉ #በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ይቻላል። የሰዎች ጥበብ ሊወጣው ያልቻለውንም #የእግዚአብሔር ጥበብ ያመጣዋል።

ምንጊዜም በመለከታዊ ዕርዳታ የተከበብክ ስለሆንህ ብቻህን ላለመሆንህ እርግጠኛ ሁን፡፡
የሰማያት ወዳጆቻችንና ቅዱሳን ሁሉ በአንተ ዙርያ ሁነው ስለ አንተ እንደሚማልዱም እወቅ።

join @ortodoxslijoch
3.2K views03:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 19:46:43
የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሕገ ወጡን “ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት” እንደማትቀበልና ቤተ ክርስቲያንን የመክፈል ሙከራን እንደምታወግዝ አስታወቀች፡፡

ከስድስቱ ኦሬንታል እህት አብያተ ክርስቲያናት አንዷ የሆነችው የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በፓትርያርኳ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ አግናጢዎስ ኤፍሬም ፪ኛ በኩል ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በጻፈችው ይፋዊ ደብዳቤ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ በለየው ሕገ ወጥ ቡድን የተፈጸመውን “ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት” በማውገዝ ከቅድስት ሐዋርያዊት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጎን መቆሟን ገልጻለች፡፡

የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ሕጋዊ እና ሐዋርያዊ ቅዱስ መሪነት ብቻ የምትቀበል መሆኑን በመግለጽ ቤተ ክርስቲያኗ ላይ የተከሰተው ፈተና እንዲያልፍ በጸሎት እንደምትለምን ገልጻለች፡፡
4.4K views16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 06:35:06 + እኔንም አስበኝ +

ዮሴፍ በበደል ላይ በደል የበዛበት ሰው ነው:: ሆድ ብሶታል:: ከሀገሩ የወጣው ፈልጎ ሳይሆን የገዛ ወንድሞቹ ሸጠውት ነበር:: ከመሸጡ በላይ በሥጋ ወንድሞቹ መጠላቱ ልቡን አቁስሎታል:: ዐሥር ወንድሞቹ ጨክነው ተስማምተው መሸጣቸውን ማሰብ ደግሞ በጣም ከባድ ነበር::

ባይተዋሩ ዮሴፍ እንደተከፋ ወደ ግብፅ ሲወርድ እግዚአብሔር ከዮሴፍ ጋር አብሮ ተሸጠ እንጂ ብቻውን አልተወውም:: በመከፋቱ አብሮት ተከፋ:: ስለኀዘኑም አብሮት አዘነ::

ዮሴፍ ጲጥፋራ በተባለ ሰው ቤት ባሪያ ሆነ:: በአባቱ ተወዳጅ ሆኖ ላደገው ቅምጥሉ ዮሴፍ በሰው ቤት ባሪያ መሆን እጅግ ከባድ ነበር::
ሆኖም በሰው ቤት ባሪያ በሆነ ጊዜ ግን የጌቶች ጌታ የሆነው እግዚአብሔር አብሮት ነበረ:: በጌታው ፊት ሞገስ ሠጥቶት ስለነበር የቤቱ አዛዥ ናዛዥ ሆኖ ተሾመ::

እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ከሆነ ባሪያ ሆነህ ብትሸጥም ባለ ሥልጣን ትሆናለህ::

እረፍት አልባው ዮሴፍ በተሾመበት ቤት ብዙም ሳይቆይ ግን የጌታው ሚስት ለዝሙት አስቸገረችው:: እግዚአብሔር ን ፈርቶ አሻፈረኝ ሲላት ራስዋ ገርፋ ራስዋ ጮኻ እስር ቤት ጣለችው::

መከረኛው ዮሴፍ እስር ቤት ወረደ:: የታሰሩ ሁሉ ወንጀለኞች አይደሉም:: የአንዳንዶችን ኃጢአት ለመሸፈን የሚታሰሩ ንጹሐን ብዙ ናቸው::

ዮሴፍ ያለ በደሉ ሲታሰርም ብቻውን አልሆነም::
እግዚአብሔር ከዮሴፍ ጋር አብሮ ታሰረ:: በበደል ላይ በደል ደርሶበት በገባበት ወኅኒ ቤት "እግዚአብሔር ከዮሴፍ ጋር ነበረ ምሕረትንም አበዛለት፥ በግዞት ቤቱም አለቃ ፊት ሞገስን ሠጠው" ዘፍ. 39:21

እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ከሆነ እስር ቤት ውስጥም ትሾማለህ:: ዮሴፍ የወኅኒው ባለ ሥልጣን ሆነ::

ከዚህ በኋላ ዮሴፍ በወኅኒው ለሁለት ሰዎች ሕልም ይፈታላቸው ጀመር:: የአንዱ ሕልም ፍቺ "ተሰቅለህ ትሞታለህ" የሚል ሲሆን የሌላኛው ሕልም ፍቺ ደግሞ "በፈርኦን ፊት ዳግመኛ ትሾማለህ" የሚል ነበር::

ወደ ፈርኦን ቤተ መንግሥት ተሹሞ የሚሔደውን ሰው ዮሴፍ እንዲህ አለው :-

"ነገር ግን በጎ ነገር በተደረገልህ ጊዜ እኔን አስበኝ ምሕረትንም አድርግልኝ የእኔንም ነገር ለፈርዖን ነግረህ ከዚህ ቤት አውጣኝ:: እኔን ከዕብራውያን አገር ሰርቀው አምጥተውኛልና፤ ከዚህም ደግሞ በግዞት ያኖሩኝ ዘንድ ምንም አላደረግሁም።" ዘፍ. 40:14

ዮሴፍ "እኔንም አስበኝ ምሕረት አድርግልኝ" ብሎ የተማጸነው የፈርኦን ጠጅ አሳላፊ ግን "ዮሴፍን አላሰበውም፥ ረሳው እንጂ" ዘፍ. 40:23

ከዚህ በኋላ ዮሴፍ ለሁለት ዓመታት በእስር ቆየ እንጂ ምንም የተፈጠረ ነገር የለም::

ባሪያ ሆኖ ሲሸጥ አብሮት የተሸጠው እግዚአብሔር
እስር ቤት ሲገባ አብሮት የታሰረው እግዚአብሔር
አሁን ግን ዮሴፍን ዝም አለው::

ለምን?

ዮሴፍ "እኔንም አስበኝ ምሕረት አድርግልኝ" ብሎ የለመነው የጠጅ አሳላፊውን ነበር:: በግፍ ከሀገሩ እንደወጣ ያለ በደሉ እንደታሰረ ያስረዳው ለፈርኦን ቤት ሹመኛ ነበር:: ስለዚህ እግዚአብሔር "ዮሴፍ ሆይ ጠጅ አሳላፊውን አስበኝ አልክን? በል እሱ ያስብህ" ብሎ ተወው::

በሕይወትህ ሰውን አደራ ያልክ ቀን እግዚአብሔር ይተውሃል:: "አውጣኝ" ያልከው ሰውን ከሆነ ፈጣሪ የሰውን ነገር እንድታይ ዝም ይልሃል::

ሁላችንም አደራ አስበኝ ብለን የተማመንንባቸው ጠጅ አሳላፊዎች አይጠፉም:: እንደ ዮሴፍ ቤተ መንግሥት ውስጥ ሰው አለኝ ብለን ተስፋ የጣልንባቸው ፣ ዘመድ አለኝ ብለን የሙጥኝ ያልናቸው ሰዎች አይጠፉም:: "በአንድ ስልክ ልጨርሰው እችላለሁ እኮ" ብለን የተመካንባቸው ሰዎች አናጣም::

ወዳጄ እመነኝ ሰው አደራ በላ መሆኑ አይቀርም:: ቃል የገባልህ ሰው ወደ ሹመቱ ሲገባ አያስታውስህም::
ሥጋ ለባሹን አደራ ብለህ ከፈጣሪህ አትጣላ::

ሰውን በቤተ መንግሥት አስበኝ ከማለት ፈጣሪን በመንግሥትህ አስበኝ ማለት ይሻላል::

"በሰው ከመታመን ይልቅ በእግዚአብሔር መታመን ይሻላል። በገዦች ተስፋ ከማድረግ ይልቅ በእግዚአብሔር ተስፋ ማድረግ ይሻላል" መዝ. 118:8

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥቅምት 6 2015 ዓ.ም.
ዲላ ኢትዮጵያ

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን አጥብቃችሁ ስለ እኔ ጸልዩልኝ!
በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ [ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ] ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)

ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
5.4K views03:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 14:14:26 መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ:
"ከሞት ወዲያ መብራት አለ ።
ከመቃብር በላይ ብርሃን አለ ።"



ታላቁ ሊቅ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይላል … ‹ሰው እግዚአብሔር ሲለየው፤ ጠባዩ እንደ አራዊት፤ አመጋገቡ እንደ እንስሳ፣ ሆኖ መልኩ ብቻ የእግዚአብሔር ሆኖ ይቀራል›።

በጣም ቀለል ባለ አገላለጽ ሲም ካርዱ የወጣ ሞባይል ማለት ነው። ጥሪ የማይቀበል…....እኔ በዕውነቱ ከተማው ፈርሶ እየተሰራ ነው እየተባለ ዐይናማዎቹ ሲያወሩም ሲያስወሩም እሰማለው። ፈርሶ መሰራት ያለበት ግን የሰዉ አስተሳሰብ ነው።... የሰዉ አስተሳሰብ ፈርሶ ካልተሰራ፤ የተሰራ ከተማ ይፈርሳል። ጃፓንና ቻይና ሀገራቸውን ያለሙት መጀመሪያ አስተሳሰባቸውን አልምተው ነው።

ቤታችሁ ገብታችሁ እንድታጤኑት ነው  እንደምታዩኝ እኔ ዐይነ ስውር ነኝ። ቀላል አይደለም.... እንክዋን ዘውትር ዓይን አጥቶ አንድ ቀን መብራት ሲሄድ ስንት እንደምታማርሩ ታውቅታላችሁ።

እኔ ግን ዓይኔ ባለማየቱ አንድ ቀን እንኳን አልቅሼ አላውቅም። ከሞት ወዲያ መብራት አለ። ከመቃብር በላይ መብራት አለ።
 
ወደ መቃብር ሲወርድ ማንም ዓይነ ስውር ነው። ማንም ዐይኑ እያየ የተቀበረ የለም።

ተስፋችን ግን ምንድን ነው?

ከሞት ወዲያ ሕይወት አለ። ከሞት ወዲያ ብርሃን አለ...

አንድ አንድ ጊዜ እመኛለሁ የማይረባ ነገር ስናይ (ዓይናችንን) የሚያጠፋ ቆጣሪ ቢኖር... መልካም ነገር እስክናይ ድረስ ለጊዜው የሚያጠፋ ቆጣሪ ቢኖር።

አሁን እንደው ጆሮ በካርድ የሚሰራ ቢሆን ሐሜት እንሰማ ነበር? የምንፈልገውን (ብቻ) አውርተን ስዊች ኦፍ እናደርገው ነበር። ችግሩ ብዙ ነው፡፡ ስንት ዞማ ጸጉር ይዞ አስተሳሰቡ የከረደደ አለ።

እባካችሁ ሰው እንሁን… የንጉሠ ነገሥቱ የክርስቶስ አልጋ ወራሾች ነን... የደስታችሁ ልኬት የደስታችሁ ሚዛን ምግብና መጠጥ አይሁን፤ መኪናና ቤት ዝናንም አታርጉ።

እኛ መለኪያችን ጽድቅ ነው።
መከኪያችን መንግሥተ ሰማያት ነው።
ያ የምንገባበት ቤት ደግም የተዋበ፣ የደመቀ፣ መብራት ውሀ የማይሄድበት፤ 24 ሰዓት ክርስቶስ የሚያበራበት፤ 24 ሰዓት የሕይወት ውሀ የሚጠጣበት፤ ሀብታም፤ ደሀ፣ ተራ ሰው የማይባልበት፣ እገሌ ግባ እገሌ ውጣ የማይባልበት ቦታ
ነው።

ሁላችንንም የመንግስቱ ወራሽ ያድርገን ፣ አሜን።

በመጋቤ ሐዲስ እሸቱ
6.7K views11:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 16:01:11 ቤተክርስቲያኗ መንግስት በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቃት እንዲሁም ህገወጥ ናቸው ስትል የፈረጀቻቸው አካላት እየፈፀሙት ነው ላለችው ህገወጥ ድርጊት እገዛ ከመስጠት እንዲታቀብ አሳሰበች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በትላንትናው ዕለት መንግሥት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን በተመለከተ የሰጠውን መግለጫ እንደማትቀበለው አሳውቃለች።

ቤተክርስቲያኗ ትላንት መንግስት መግለጫውን ሲያወጣ ፤ " በሻሸመኔ ከተማ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች የተፈጸመውን ሕገ ወጥ፤ አስነዋሪ እና ጭካኔ የተሞላበት የአደባባይ ግድያ እና የሕዝብ ፍጅት ያልጠቀሰና ሐዘኑን እንኳን መግለጽ ያልቻለበትና ያላወገዘ መሆኑን አንስታ ይህም " የመንግሥትን ግልጽ ሚና በቀላሉ ለመረዳት እንድንችል ያደርገናል " ብላለች።

" መንግሥት ሕገ ወጥ አካላትን ድጋፍ ከመስጠት እና የእነርሱ ልሳን ሆኖ በመቅረብ የቤተ ክርስቲያንን ክብር እና ልእልና ከሚያንኳስስ ሕገ ወጥ ድርጊት እንዲታቀብ እናሳስባለን " ያለችው ቤተክርስቲያኗ ፤ " ሕገ ወጡ ስብስቦች እየፈጸሙ ላሉት ድርጊትም የሰጠውን ድጋፍ እና እገዛ በይፋ ቤተ ክርስቲያንን ይቅርታ በመጠየቅ ያቁም " ስትል አሳስባለች።
3.4K views13:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ