Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxslijoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.17K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ምንማማርበት :መዝሙር: ስብከቶች ይተላለፋል !

መንፈሳዊ ትምህርቶች : መንፈሳዊ ጥያቄዎች : ስብከት : መዝሙር : ይቀርብበታል #ጉዞው ገዳማት #ሰማህታት ታሪክ ይቀርባል!
FacebookGroup : ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ይቀላቀሉ ::

#shear

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-05-21 06:18:43 #ካህኑ_ለምን_በእጁ__ያሳልሙናል ?
የካህኑን እጅ መሳለም አንዳንድ ሰዎች ካህኑ ለምን በእጁ ያሳልመናል ይላሉ።

ነገር ግን ሚስጢሩ ይህ ነው
የካህኑ እጅ እኮ እሳታዊያን የሆኑ መላእክት መንካት
የማይቻላቸውን ቅዱስ ሥጋውን ክብር ደሙን የዳሰሱበት
ነው።

በቅዳሴ ላይ ቅዱስ ሥጋውን መንካት የሚችለው ዋናው ካህን ብቻ ነው ፤ ሁለተኛው ካህን እንኳን መንካት አይችልም።

ቅዱስ ሥጋውን ክብር ደሙን የዳሰሰበት ስለሆነም ካህኑ በእጁ ያሳልመናል እኛም የተቀደሰውን የጌታ ስጋና ደም
የዳሰሱበት እጅ እየተሳለምን አሜን አሜን አሜን እንላለን።

ድንቅ መለኮታዊ ሚስጥር ማለት
እንዲህ ነው
አንሥኡ እደዊክሙ ቀሳዉስ
ዲያቆኑ ይህን በሚልበት ጊዜ ንፍቀ ካህኑ ማሕፈዱን
ከጻሕሉ ላይ ያነሳል ፤ ይህም የጌታ መላአክ የመቃብሩን
ድንጋይ የማከባለሉ ምሳሌ ነው።ከዚህ በኋላ ጌታችን
በምሴተ ሐሙስ ሕብስቱን እንደያዘው ዋናዉ ካህንም
ሕብስቱን ከፍ አድርጎ ይይዘዋል ፤ ይህም የጌታ ትንሳኤ ምሳሌ ነው።

እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ
በእግዚኦታ ላይ ካህኑ ሕብስቱን ይበልጥ ከፍ አድርጎ
ይይዘዋል ይህም የዕርገቱ ምሳሌ ነው።
ከካህኑ ጋር ሆነን
41 ግዜ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ እንላለን ፤ ይህም አርባው እግዚኦታ አይሁድ ጌታችንን 40 ግዜ እንገርፋለን ብለው እያዛቡ ብዙ ጊዜ የመግረፋቸው ምሳሌ ሲሆን በመጨረሻ ካህኑ ብቻውን የሚላት እግዚኦታ ደግሞ የአዳምና የሔዋን የንስሃ ምሳሌ ነው።

12 ግዜ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ ስንል ደግሞ ስለስምህ ብለህ ይቅር በለን ነው። አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ የሚለውን እያንዳንዱን ፊደል ስንቆጥር 12 ይሆናል!!!

እንዲሁም 12 ጊዜ በእንተ እግዚትነ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ ስንልም ደግሞ ስለእናትህ ብለህ ማረን ማለታችን ሲሆን ቅድስት ድንግል ማርያም የሚለውን እያንዳንዱን ፊደል ስንቆጥር 12 ይሆናልና
ወንጌል
የመጀመሪያዉ መልዕክት ሲነበብ ዲያቆኑ ፊቱን ወደ ምዕራብ አዙሮ ያነባል፡

ሁለተኛው ዲያቆን ፊቱን ወደ ሴሜን አዙሮ ያነባል ፡ ንፍቀ ካህኑ ወደ ደቡብ ዙሮ ያነባል የሐዋርያት ሥራ ሲያነብ ዋናው ካህን ደግሞ ወደ ምስራቅ ዙሮ ወንጌል ያነባል ፤ ይህም ግሩም የሆነ ምሳሌ አለው አንድም ወንጌል በአራቱም አቅጣጫ መስበኩን ለመግለጽ ነው አንድም ገነትን የሚጠጡ 4 ወንዞች አሉ ኤፍራጠስ ጤግሮስ ጊዮን (አባይ) እና ፊሶን ናቸው።

ገነትን አጠጥተው ለምለም እንደሚያደርጓት ጌታችንም የተጠማ ቢኖር የህይወት ውሃ በነፃ ይጠጣና ይርካ እንዳለው ወንጌልም እንዲሁ ያለመልማል ሲሉ ነው።

ቤተክርስቲያን ከጣራዋ እስከ መሬቷ ሁሉም ስርዓቷ
ያስተምራል ፤ ባህረ ጥበብ ቤተክርስቲያን እየተናገረች
ታስተምራለች ሳትናገርም ዝም ብላ ታስተምራለች!!!

መልካም እለተ ሰንበት ይሁንላችሁ በቸር ያውለን አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለ ወላዲቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክብር

     Join @ortodoxslijoch
524 views03:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 19:36:50 "አጣቢም በምድር ላይ እንደዚያ ሊያነጣው እስከማይችል በጣም ነጭ ሆነ። "
<ማር 9: 3>

የወንጌላውያን ትሕትና ይደንቃል ፣ ማቴዎስ ማርቆስ ሉቃስ ስለ ደብረ ታቦር ሲጽፉ ዮሐንስ አልጻፈም። ዮሐንስ ተመርጦ የተገኘበትን ታሪክ "ተመርጬ" ብሎ አልጻፈም። የቀሩት ወንጌላውያን ደግሞ "እኛ የሌለንበትን ነገር አንጽፍም" አላሉም። አንድ ወንጌል እየሰበኩ የሚፎካከሩ ፣ የአንድ ቤት ጣሪያ እየሠሩ ቆርቆሮ የሚሻሙ የእኛ ዘመን አገልጋዮች አልነበሩምና እነርሱ ያልተመረጡበትን ታሪክ ለመናገር ተሯሯጡ። እኛን የማያካትት ክብር ፣ እኛን የማይጨምር ድግስ ጉዳይ ሲነሣ ለማይጥመን ፣ እኛ የሌለንበትን ፎቶ እንኳን ለማየት የማንፈልግ ፣ በእኛ በኩል ያለፈን ነገር ብቻ የምናራግብ ፣ የሌለንበትን ነገር ጥሩም ቢሆን እንኳን ለምናጣጥል "በእኔ በቀር ባዮች" ትምህርቱ ድንቅ ነው።

ሌላ ማሳያም አለ ማቴዎስ ወንጌላዊው ስለ ራሱ ታሪክ ሲጽፍ "ማቴዎስ የተባለ ቀራጭ በመቅረጫው ተቀምጦ" ብሎ በኃጢአት ከተዘፈቀበት ሥራ ላይ ወደ ክርስትና እንደተጠራ በግልጽ ሲጽፍ ሌሎቹ ወንጌላውያን ግን በሐዋርያት ዝርዝር ላይ ማቴዎስ ያሉትን ሰው ስለ ቀድሞ የቀራጭነት ሥራው ሲጽፉ ግን ሌዊ የሚል ተለዋጭ ስሙን ተጠቅመዋል። ትሑቱ ማቴዎስ ግን በሌሎች ወንጌላውያን የተሸሸገ የቀድሞ የኃጢአት አኗኗሩን ለእግዚአብሔር ይቅር ባይነት ማሳያ እንዲሆን ስለፈለገ ጭራሽ በሐዋርያት የስም ዝርዝር ላይ "ቀራጩ ማቴዎስ" ብሎ ራሱን ጠርቷል።

የሚገርመው ከቀራጭነት ከተጠራ በኋላ በቤቱ ታላቅ ድግስ ደግሶ ጌታችንን ከኃጢአተኞች ጓደኞቹ ጋር የተቀበለ መሆኑን በሌሎች ወንጌላውያን ሲጽፉ ማቴዎስ ግን ቀራጭነቱን አጉልቶ እንዳልጻፈ ሁሉ የግብዣው ነገር ደጋሹ እርሱ መሆኑን አድበስብሶ በመጻፍ አልፎታል።
★ ★ ★

ቅዱስ ጴጥሮስ "ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው" አለ። "ለእኛ" መልካም ነው የሚለው ቃል ድንቅ ነው። በእግዚአብሔር ቤት መኖራችን መልካምነቱና ጥቅሙ ለእኛ ነው እንጂ ለእግዚአብሔር አይደለም። የማንጠቅም ባሪያዎቹ ስሙን በአሕዛብ ዘንድ ከማሰደብ በቀር ለእርሱ ምን እንጠቅመዋለን። ለዚህም ነው ቅዱስ ባስልዮስ "ጌታ ሆይ የአንተ አምላክነት ለእኔ ያስፈልገኛል እንጂ የእኔ ፍጡርነት ለአንተ አያስፈልግህም" ያለው።
ስለዚህ ጴጥሮስ "ለእኛ መልካም ነው" አለ።

"ብትወድስ ሦስት ዳስ እንሥራ" አለ ፣ ጌታ ካልወደደ እንኳን ሦስት አንድ ዳስ መሥራት አይቻልም ፣ እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ" ስለዚህ "ብትወድስ" አለ።

የዋሁ ጴጥሮስ ለእኔ ልሥራ አላለም ፣ የሐዲስ ኪዳን ሐዋርያ ነኝ ብሎ የብሉይ ኪዳን ነቢያትን ከማክበር ወደ ኋላ አላለም። "አንተ ዓለት ነህ በዚህች ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራታለሁ" በተባለ ማግስት ለነቢያቱ ድንኳን ሊቀልስ የጠየቀ ከጴጥሮስ በቀር ማን አለ?

ከእግዚአብሔር አብ ግን "አትሙት" እስከማለት ለደረሰው ለነጴጥሮስ ንግግር "የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት" የሚል ትእዛዝ መጣ። ሃሳቡ ድንቅ ቢሆንም ቃሉን ሳይሰሙ ዳስ መሥራት መጀመር አይቻልም።

በዚያ ላይ ጌታ የመጣው በደብረ ታቦር ድንኳን አስጥሎ ሊኖር ሳይሆን በቀራንዮ በተሰቀለበት በመስቀሉ ካስማ በደሙ ድንኳን ተክሎ ሊያስጠልለን ነው። ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ "ጴጥሮስ ሆይ ለአንተ የፊቱን ብርሃን እያየህ በዚህ መኖር መልካም ነው ፣ እኛ ግን የምንድነው በተራራው ሲኖር ሳይሆን ወርዶ ፊቱን በጥፊ ሲመታ ነው" ብሎታል።

ጴጥሮስ የዋሁ "በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ" ላለው ለክርስቶስ ድንኳን ሊቀልስ ጠየቀ። በሰማይ "በሰው ሳይሆን በጌታ የተተከለች ድንኳን" ላለችው ሊቀ ካህናት ድንኳን ሊሠራ ለመነ። እዚህ አለ ሲሉት እዚያ ለሚገኘው ፣ በመንፈስ እየተነጠቀ አድራሻውን ለመወሰን ያስቸግር ለነበረው ኤልያስ እንዲቀመጥ ተስፋ አድርጎ ድንኳን ልሥራ አለ። እጅግ የተዋበችና በወርቅ በሐር ያጌጠችን የኦሪት ድንኳን ለሠራው ሙሴ ዓሣ አጥማጁ ጴጥሮስ ድንኳን ልሥራለት አለ። ሐዋርያት ነቢያቱን ሊያስተናግዱ የለመኑባት ደብረ ታቦር ፣ ሐዋርያት ነቢያቱን ለጌታ ቀኝ አዝማች ግራዝማች አድርገው በድንኳን አስቀምጠው እነርሱ እንደ ሎሌ ከደጅ ሊኖሩ የጠየቁ እነ ጴጥሮስ እንደምን ይደንቃሉ? ጴጥሮስ ሆይ አሁን በሰማይ ድንኳኖች ውስጥ እያገለገልህ ይሆንን? ደብረ ታቦርን አይተህ በደስታ "እንኑር" ያልከው ጴጥሮስ ሆይ የገነት ደስታ ስታይ ምን ተሰምቶህ ይሆን?

በእሳት ድንኳን ለመኖር ተስፋ የምናደርግ "በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል" የተባልን እኛስ ምንኛ የታደልን ነን?

★ ★ ★

በታቦር ተራራ ላይ የጌታችን ልብስ እንደ ፀሐይ አበራ ፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "ከፀሐይም በላይ ነው ፣ ፀሐይ አይቶ የወደቀ የለም የጌታችንን ልብስ ሲያዩ ግን የወደቁት ያበራው ከዚያ በላይ ስለሆነ ነው" ይላል።

ከጌታችን በዚያ ተራራ ከሙሴና ኤልያስ ጋር ነበረ። ሙሴ እንደምናውቀው ጽላቱን ተቀብሎ ሲወርድ ሕዝቡ "እባክህን ተሸፈንልን" ብለውት ፊቱን በመጎናጸፊያው ሸፍኖ ነበር። የሙሴ አምላክ ክርስቶስ ግን ደቀ መዛሙርቱ ሲወድቁ አይቶ በልብሱ እንዳይሸፈን ያበራው ፊቱ ብቻ ሳይሆን ልብሱም ነበር።

" አጣቢም በምድር ላይ እንደዚያ ሊያነጣው እስከማይችል በጣም ነጭ ሆነ" ማር 9: 3
የሚለው ቃል ምንኛ የሚደንቅ ነው። በምድር ላይ ያለ አጣቢ ቢፈትግ ቢታገል የዚያን ያህል ሊያነጻው የማይችለው ነጭ እንዴት ያለ ነው? መቼም ሁላችን የምናውቀው ነጭ ነገር ሁሉ በምድር ላይ ባለ አጣቢ የታጠበ ስለሆነ እንዲህ ነው ማለት አንችልም። ብቻ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በምድር ያሉ አጣቢዎች ከሚያነጡት በላይ ልብስን ማንጣት ይችላል።

ይህ ቃል በኃጢአት እድፍ ልብሳችን ላደፈ ሁሉ መጽናኛችን ነው።

መቼም የምድር አጣቢዎች አቅማቸው ውስን ነው።
ቆሽሸን ያዩን ሰዎች ብንታጠብም አያምኑንም ፣ ቢያጥቡልንም በኅሊናቸው የሚያስቀሩብን ቆሻሻ አለ።
በሰው ዓይን አንዴ ቆሽሸህ አትገኝ እንጂ ከተገኘህ መቼም ነጭ አትሆንም። አንተ ግን የደብረ ታቦሩ ብርሃን መድኃኔ ዓለምን ብቻ "እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ" በለው "ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች። " ብሎ በገባው ቃል መሠረት ነጭ ያደርግሃል።

እርሱ ወዳለባት የቅድስት ቤተክርስቲያን ተራራ በንስሓ ከደረስክና በታቦር ያበራውን ብርሃኑን ካበራልህ ነጭ ትሆናለህ። ከዚያ "አጣቢ የማያነጻውን ያህል ትነጻለህ" ከአብ የባሕርይ ልጅ ከብርሃኑ ፀዳል ስትቀርብ አንተም በጥምቀት ያገኘኸው የጸጋ ልጅነትህ ያንጸባርቃል። ነጭ በሆንህ ጊዜ የሚያዩህ ሁሉ "በበጉ ደም ልብስህ መታጠቡን"ና ነጭ መሆኑን አይተው ይደነግጣሉ ፣ ሊሰሙህ ያልወደዱ ሁሉ ለባሕርይ ልጁ "የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት" ብሎ እንዳዘዘለት ለአንተም ጆሮ እንዲሠጡህ ያደርግልሃል።

አንተ ብቻ ከደብረ ታቦር አትቅር ፣ ካልሞትህ እንደ ኤልያስ ፈጥነህ ና ፣ በበደል ከሞትክም እንደሙሴ ተነሥተህ ና። ብቻ ወደ ደብረ ታቦር ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለመምጣት ተስፋ አትቁረጥ ፣ እንደ ሙሴ ትሞታለህ እንጂ ምድረ ርስትን አታይም ብትባል ፣ እንደ ኤልያስ ትኖራለህ እንጂ ሞትን አታይም ብትባል ብቻ አንተ ከደብረ ታቦር አትቅር።

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
1.4K views16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 10:14:20 እንኳን አደረሳችሁ (ከሚካኤል በቀር
የሚረዳኝ ማንም የለም። "ዳን ፲፥፳፩ ")
#ቅዱስ ማለት ልዩ ፥ ክቡር ማለት ነው
#ሚካኤል ማለት ደግሞ « መኑ ከመ አምላጠክ ፥ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው» ማለት ነው።
#ሚካኤል የሚለው ስም ቃሉ የዕብራይስጥ ነው
#ሚ - የሚለው « #መኑ » ማለት ነው፥
#ካ - የሚለው « #ከመ » ማለት ሲሆን፥

➦ኤል - ማለት ደግሞ « #አምላክ » ማለት ነው። ይህን ማለትም የቅዱስ ሚካኤልን ስም በጠራን ቊጥር የምንመሰክረው ስለ እግዚአብሔር ነው ፤ በመሆኑም እግዚአብሔርን በባሕርይ የሚመስለው ፥
በሥልጣንም የሚተካከለው ፥ በምድርም በሰማይም እንደሌለ የሚናገር ልዩ ፥ ክቡር ስም ነው።

➦የነቢያት አለቃ ሙሴ ባሕረ ኤርትራን ለሁለት ከፍሎ ሕዝቡን ያሻገረለትንና ፈርዖንን ከነሠራዊቱ ያሰጠመለትን አምላክ እግዚአብሔርን በመዝሙር ሲያመሰግን ፥ « አቤቱ በአማልክት መካከል ( በስም አማልክት ከሚባሉ ፥ በስመ አማልክት ከሚጠሩ ፥ አንድም አማልክት ዘበጸጋ ከተባሉ ከነቢያት ከካህናት መካከል ) አንተን የሚመስል ማነው? በቅዱሳንም ዘንድ እንደ አንተ የከበረ ማነው? » ብሏል። ዘጸ ፲፭፥፲፩።

➦በያለንበት ቦታ ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ ከክፉ ነገር ሁሉ ይጠብቀን!
አሜን አሜን አሜን
            Join @ortodoxslijoch
2.3K views07:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 13:12:30 ❖የክርስትና ስም ለምን ያስፈልጋል?❖
******
ጥቂት የማን
ባል ሰዎች ከነ መሰየሙም

የክርስትና ስማችንንም የማናስታውስ ልንኖር እንችላለን፡፡

የክርስትና ስም አንድ የሚጠመቅ ሰው በሚያጠምቀው ካህን የሚሰጠው ወይም የሚጸድቅለት ስያሜ ነው፡፡

ይህንን ስም ቤ/ክ ዝም ብላ ለህጻናቱ የምትለጥፍ የሚመስላቸው ሰዎች ቀላል አይደሉም፡፡ በጥምቀት ግዜ ቤ/ክን ልጆቿን ስትቀበል እንዲሁ አይደለም ተገቢ ስም አውጥታ ከመንፈስ ቅዱስ በጥምቀት ዳግመኛ ወልዳ ቅበዐ ሜሮን ቀብታ የሚንከባከብ የክርስትና አባት እናት ሰይማ በመስቀሉ ቃል አስገብታ ቅዱስ ስጋና ደሙን መግባ ነው፡፡

የክርስትና ስም መጽሐፍ ቅዱሳዊ እና ክርስቲያናዊ ትውፊት አለው፡፡

ብዙ ነብያት እና ቅዱሳን ካላቸው መጠሪያ ሰም በተጨማሪ እራሱ አምላካችን አዳዲስ

ስም ሲያወጣላቸው እናያለን ለምሳሌ፡-

አብራምን ☞ አብርሃም
ያይቆብን ☞ እስራኤል
ስምዖንንን ☞ ጴጥሮስ
ሳኦልን ☞ ጳውሎስ እያለ ሲጠራቸው ለምን በአዲስ ስም መጥራት እንደፈለገ አንዳች ነገር ልንገነዘብ ይገባል፡፡

✞ ዓላማውስ ምንድን ነው?

1.ቋሚ የቅዱሳን መታሰቢያ እንዲሆን፡-

በት.ኢሳ 56:5 አምላክ ለቅዱሳን የማይጠፋ ስም እና የዘለዓለም መታሰቢያ እንደሰጣቸው እናነባለን፡፡ስለዚህ በተለያዩ ቅዱሳን ላይ የነበረውን ፀጋ እና በረከት ለመካፈልና እንዲሁም እንደነሱ የበረታን እንድንሆን በስማቸው እንሰየማለን የጌታችንንም ስሙን ዘርፍ በማድረግ እንዲሁ እንጠቀምበታለን፡፡

2.ለተጠማቂውም በረከት እንዲሆንለት፡-

በምሳ 10:6 የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው ይላል፡፡ ስለዚህ በስማቸው በመሰየም ከላይ እንደገለጽነው መታሰቢያቸውን እና በረከታቸውን ለመካፈል ሲረዳን ይህን ጸጋ ለማግኘት በቅዱሳን ስም በመሰየም የክርስትና ስም ይወጣልናል፡፡

3.መጠሪያ ስም ነው፡-

በቀድሞው ስርአት የክርስትና ስም ለሁልጊዜውም መጠሪያ ነበር፡፡ ከግራኝ መሐመድ መነሳት አስቀድሞ የነበሩ ምዕመናን በክርስትና ስማቸው ነበር የሚጠሩት፡፡ነገር ግን መከራው ሲበዛባቸው ከርስታቸው ላለመሰደድ ሲሉ ተለዋጭ ስም በማውጣት መጠቀም ጀመሩ ከዛን ግዜ ጀምሮ ይህ ነገር እየተስፋፋ መጥቶ ከነ ጭራሹ ለመለወጥ በቃ፡፡

☞ የማይገባ የክርስትና ስም
በአምላክ ስም በቀጥታ መጠራት አይገባም ለምሳሌ፡- አማኑኤል፣ኤልሻዳይ፣ኢየሱስ እነዚህ ስሞች ለሠው ልጆች መጠናችን ስላልሆኑ መጠቀም የለብንም፡፡ በዚህ ምትክ ገብረ አምላክ፣ሣህለ ሥላሴ፣ፍቅርተ ክርስቶስ ፣ዘአማኑኤል በማለት መሰየም ይቻላል፡፡

☞በቅዱሳንም ስም በቀጥታም ሆነ ዘርፍ እየተደረለት መሰየም ይቻላል፡፡
ለምሳሌ፡- ዘማርያም፣ዘሚካኤል፣አጸደ ማርያም፣ ተክለ ሐይማኖት ወዘተ...

ስለዚህ ስርአቱን በመጠቀም ከሚገኘው በረከት ተሳታፊዎች እንድንሆን አምላክ ይርዳን፡፡


             Join @ortodoxslijoch
3.2K views10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 06:43:52 እንኳን ለታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ †††
††† ቅዱስ ያሬድ:- ከእግዚአብሔር ያገኘነው አባታችን : ክብራችን : ሞገሳችን ነውና በምን እንመስለዋለን?

*አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም)::
*ልቡናው የቅድስና ማሕደር::
*ሕሊናው የምሥጢራት ሠረገላ ነው::
*እስከ አርያም ተነጥቆ የማይፈጸም ምሥጢርን የተመገበ ማን እንደርሱ!
ሊቀ ሊቃውንት እዝራ ሐዲስ እንደሚሉት:- "ቅዱስ ያሬድ ለኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከራስ ጸጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ : ሙሉ አካሏ ነው::"

††† የሊቁ ዜና ሕይወት በጥቂቱ †††
††† ቅዱስ ያሬድ የተወለደው በ505 ዓ/ም አክሱም አካባቢ ሲሆን እናቱ ክርስቲና (ታኡክልያ) አባቱ ደግሞ ይስሐቅ (አብድዩ) ይባላሉ:: ሊቁ በሕጻንነቱ ምሥጢር (ትምሕርት) አልገባው ብሎ ይቸገር ነበር::

ትምሕርት እንቢ ያለው ሰነፍ ስለ ነበር አይደለም:: በጥበበ እግዚአብሔር እንጂ::
ምን ትምሕርት ባይገባው ጾምና ጸሎትን ያዘወትር ነበር:: ልቡናው ደግሞ በእመቤታችንና በልጇ ፍቅር የታሠረ ነበር:: አንድ ቀን ግን መምሕሩ የነገሩት ቀለም አልያዝሕ አለው:: ሲፈትኑትም ባለመመለሱ ተገረፈ::

ዱላው በጣም ስለ ተሰማው ቅዱሱ ከመምሕሩ ኮብልሎ ማይ ኪራሕ አካባቢ ሲደርስ ደክሞት አርፎ እግዚአብሔር ትጋትንና ተስፋ አለመቁረጥን ከትል አስተማረው::
ትሏ ስድስት ጊዜ ወድቃ በሰባተኛው ፍሬዋን ስትበላት ተመልክቷልና::
ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ መምሕሩ ተመልሶ : ይቅርታ ጠይቆ ትምሕርት ጀመረ:: ሊቁም ትጋትንና ጸሎትን ከሰጊድ ጋር አበዛ:: እግዚአብሔር ደግሞ በድንግል እናቱ አማካኝነት የምሥጢር ጽዋን አጠጣው::

ካህኑ ያሬድ እንዲያ አልገባህ ያለው ምስጢር ተገልጦለት በጥቂት ጊዜ ብሉይ ከሐዲስ ወሰነ:: በምሥጢር ባሕርም ይዋኝ ጀመር::

ያን ጊዜ ሰማያዊ ዜማ አልተገለጠም ነበርና በጸሎት ላይ ሳለ ተደሞ መጣበት:: ሦስት መላእክት በሦስት ወፎች አምሳል መጥተው አነጋገሩት::

ድንገትም ነጥቀው ወደ ሰማያት : ወደ ልዑላኑ መላእክት ዘንድ አደረሱት:: ሊቁ በሰማያት ልዩ ምሥጢር : ልዩ ምስጋናና ልዩ ዜማን አዳመጠ:: ይሕንን ምስጋና ብዙ ቅዱሳን ቢሰሙትም ቅዱስ ያሬድ ግን ይዞት እንዲወርድ ተፈቀደለት::

ሊቁ ወደ ምድር ተመልሶ በታላቅ ተመስጦ አክሱም ጽዮን ውስጥ በሃሌታ አመሰገነ:: ሕዝቡና ንጉሡም ከጣዕሙ የተነሳ አደነቁ:: ቅዱስ ያሬድ ለተወሰነ ጊዜ በአክሱምና ደብረ ዳሞ ሲያገለግል ቆይቶ : ከመሬት ክንድ ከስንዝር ከፍ ብሎ ለእመቤታችን አንቀጸ ብርሃንን ደርሶላት ከሃገሩ ወጣ::

††† ቅዱስ ያሬድ በቀሪ የሕይወቱ ዘመናት:-
1. አምስት ያሕል መጻሕፍትን ጽፏል::
2. በጣና ቂርቆስ : በዙር አባና በሌሎችም ቦታዎች ወንበር ዘርግቶ ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርቷል::
3.በሰሜን ተራሮች አካባቢ በትጋሃ መላእክትና በተባሕትዎ ኑሯል::

††† በ576 (571) ዓ/ም በተወለደ በ71 ዓመቱ በዚህች ቀን ተሰውሯል::
††† አባቶቻችን:-
*ጥዑመ ልሳን
*ንሕብ
*ሊቀ ሊቃውንት
*የሱራፌል አምሳያ
*የቤተ ክርስቲያን እንዚራ
*ካህነ ስብሐት
*መዘምር ዘበድርሳን
*ማኅሌታይ
*ልዑለ ስብከት
እያሉ ይጠሩታል::
††† የቅዱሱ ጸሎትና በረከት ሃገራችንን ከክፉው ሁሉ ይጠብቅልን::
3.5K views03:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 13:35:41 የመፅሐፍ ቅዱስ ስሞች 

1 ባሮክ ፡ ብሩክ ማለት ነዉ
2 ሮቤል፦እነሆ ወንድ ልጅ ማለት ነው።
3 ኤርምያስ፦እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል ማለት ነው።
4 ሮብዓም፦ሕዝብ ይብዛ ማለት ነው።
5 ማራናታ፦ጌታ ሆይ ና ማለት ነው።
6 ቤቴል፦የእግዚአብሔር ቤት ማለት ነው።
7 ቄርሎስ፦የተመረጠ ምርጥ ማለት ነው።
8 እስጢፋኖስ፦አክሊል ማለት ነው።
9 ሳውል/ሳኦል፦ከእግዚአብሔር የተለመነ ማለት ነው።
10 ሴዴቅያስ፦የእግዚአብሔር ጽድቅ ማለት ነው።
11 ፊቅጦር፦ኀዘኔን አራቀልኝ ማለት ነው።
12 ንፍታሌም፦ታጋይ የሚታገል ማለት ነው።
13 ዮርዳኖስ፦ወራጅ ውሃ ማለት ነው።
14 ዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል ማለት ነው።
15 ገነት፦የአትክልት ስፍራ ማለት ነው።
16 ፊልድልፍያ፦የወንድማማች ፍቅር ማለት ነው።
17 ዲና፦ፈረደ ማለት ነው።
18 ማኑሄ፦እረፍት ማለት ነው።
19 መልሕቅ፦ከብረት የተሠራ የመርከብ ማቆሚያ
20 ራማ፦ከፍታ ማለት ነው።
21ቴዎድሮስ፦የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው።
22 ፊላታዎስ፦የአምላክ ወዳጅ ማለት ነው።
23 ሕርያቆስ፦ኅሩይ ምርጥ ማለት ነው።
24 ፊልጶስ፦ወንድም ወዳጅ ማለት ነው።
25 ቶማስ፦ፀሐይ ማለት ነው።
26 ታዴዎስ፦እሸቱ ማለት ነው።(ግብራዊ ትርጓሜ)
27 ማትያስ፦ፀሐይ ወይም ምትክ ማለት ነው።
28 ቀሌምንጦስ፦ግንብ ማለት ነው።
29 አቤል፦በግ ወይም ደመና ማለት ነው።
30 ኖኅ፦ደስታ ማለት ነው።
31 ሴም፦ተሾመ ማለት ነው።
32 ይሥሐቅ፦ደስታ አንድም ይሳቅ ማለት ነው።
33 ሙሴ፦የውሃ ልጅ ማለት ነው
34 አሮን፦የእግዚአብሔር ተራራ ማለት ነው።
35 ጌዴዎን፦እግዚአብሔር ኃያል ነው ማለት ነው።
36 እሴይ፦ዋጋየ ማለት ነው።
37 አሚናዳብ፦መንፈስቅዱስ ማለት ነው።
38 ዳዊት፦የተወደደ ልበ አምላክ ማለት ነው፣
39 ዕንባቆም፦ጠቢብ አዋቂ አስተዋይ ማለት ነው።
40 ሄኤሜን፦ምኞቴን አገኘሁ ማለት ነው።
41 አሞጽ፦እግዚአብሔር ጽኑ ነው ማለት ነው፣
42 ዮናስ፦ርግብ ማለት ነው።
43 ሐጌ፦የእግዚአብሔር መልእክተኛ ማለት ነው።
44 ራኄል፦በግዕት ማለት ነው።
45 ዕዝራ፦ረዳቴ ማለት ነው።
46 ሔርሜላ፦ከክብር ዘመድ የተገኘች ማለት ነው።
47 መርቆሬዎስ፦የአባት ወዳጅ ማለት ነው።
48 ኤጲፋንዮስ፦ምስጢር ገላጭ ማለት ነው።
49 ሜሮን፦የተባረከ ሽቱ ማለት ነው።
50 ሱላማጢስ፦ሰላማዊት ማለት ነው።
51 ሶምሶን፦ፀሐይ ማለት ነው።
52 ብንያም፦የቀኝ እጄ ልጅ ማለት ነው።
53 ማርታ፦እመቤት ማለት ነው።
54 ሊዲያ፦ፈራሂተ እግዚአብሔር ማለት ነው።
55 ኤፍሬም፦ፍሬያማ ፍሬው ማለት ነው።
56 ኤፍራታ፦ክብርት የተከበረች ማለት ነው።
57 ታዴዎስ፦ተወዳጅ ወይም ፍቁር ማለት ነው።(ቃላዊ ትርጓሜው)
58 ኢየሩሳሌም፦የሰላም ሀገር ማለት ነው።
59 ሄኖስ፦ሰው ማለት ነው።
60 ሰሎሜ፦ሰላም ማለት ነው።

ማስታወሻ፦ከላይ ከጻፍኳቸው ውስጥ አንዳንድ ስሞች ከ81ዱ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የማይገኙ ከሌሎች የታሪክ እና የገድል መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ስሞች መሆናቸውን ማሳወቅ እፈልጋለሁ።

            
#ሼር

    Join @ortodoxslijoch
1.1K viewsedited  10:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 06:46:50 «በሚያልፍ ዓለም ውስጥ የማያልፈውን አምላክ_
*_ተስፋህም፣ መከታህም አድርገው_ !*
♡አቤቱ ጌታዬ ሆይ፥

➊.በጥበቤ እንዳልመካ ጥበቤ ይዘነጋኛል፣

➋.በጉልበቴ እንዳልመካ ጉልበቴ ይከዳኛል፣

➌.በሀብቴ እንዳልመካ ሀብቴ እንደ በረዶ ይሟሟል፣

➍.በዝናዬ እንዳልመካ ተረኛ ዝነኛ ይነጥቀኛል፣

➎.በኃይሌ እንዳልመካ ኃይሌ ይዝልብኛል፣

➏.በሰራዊት እንዳልመካ ይበተንብኛል፣

➐.በውበቴ እንዳልመካ ውበቴ ይበላሽብኛል፣

➑.በፍቅሬ እንዳልመካ ፍቅሬ በጥላቻ ይለወጣል፣

➒.በአገልግሎቴ እንዳልመካ የገነባሁትን ላፈርሰው እችላለሁ፣

➓.በወዳጅ እንዳልመካ ከስፍራው አጣዋለሁ፣

➊➊.በትላንት እንዳልመካ አልፎ ተረት ይሆንብኛል፣

➊➋.በዛሬ እንዳልመካ ባሰብሁበት መዋል ያቅተኛል፣

➊➌.በነገ እንዳልመካ ቀን የሚያመጣውን ማወቅ ያቅተኛል፣
:
➊➍.በቅድስናዬ እንዳልመካ ,አንዱን ስደፍን አንዱ ያፈስብኛል።

የምመካበት ያሳፈረኝን የምመካበትን የፈራሁትን፣ የምመካበት ያጣሁትን እኔን ልጅህን ትምክሕት የሆንከኝ ጌታዬ ሆይ ተመስገን።
♡አቤቱ ፈጣሪዬ ሆይ፥

➊.ጽድቅ ለሌለኝ ጽድቅ ፣ ቅድስና ለሌለኝ ቅድስና ፣ ጥበብ ለሌለኝ ጥበብ
የሆንከኝ አንተ ነህ።

➋.ቤዛ ማቅረብ ለማልችል ቤዛ የሆንከኝ ፣ ከሞትም ያዳንከኝ ፈጣሪዬ ሆይ ምስጋናዬ ይድረስህ።

➌.ከሚያባርረኝ ጠላት ፣ ከሚያሳድድ ሕሊና የተማጸንሁብህ የደኅንነቴ ቀንድ አንተ ነህ።

➍.የማትደፈር ምሽግ ሁነህ ከሁሉ የምታድነኝ አንተ ነህ።

➎.የዘራሁት ሲመክን ፍሬን የምትሰጠኝ ፣ የሠራሁት ሲፈርስ አዲስ ገንብተህ የምታኖረኝ አንተ ነህ።

➏.አንተ ትምክሕቴ ነህ። የደኅንነቴም ራስ ነህ። ለሚያልፈው ዓለም ብቻ ሳይሆን ለማያልፈው ዓለምም እሻሃለሁ።

➐.አንተ ካላቅኸኝ የሚያሳንሰኝ ፣ አንተ ከወደድከኝ ከንቱ የሚለኝ ማንም የለም። ቢኖርም ሐሰተኛ ነው።

ዛሬን ያየሁብህ ትምክሕቴ ሆይ ተመስገን።
:
♡አቤቱ ፈጣሪዬ ሆይ፥

➊.በአንተ ላይ እደገፋለሁ፣ በአንተ ላይ እደላደላለሁ፣ የማትነቃነቅ ምሰሶዬ አንተ ነህ።

➋.ከስፍራህ አትታጣም። ስደገፍህ የማትሰበር ምርኩዜ አንተ ነህ።

➌.ስጠጋህ የማትሸሸኝ ወዳጄ አንተ ነህ።

➍.ከፍ የምልብህ ደብሬ አንተ ነህ።
♡አቤቱ አምላኬ ሆይ፥

ካንተ አግኝቻለሁና ከሰው አጣሁ ብዬ አላዝንም። ባንተ ተክሻለሁና ከሰርሁ ብዬ አላጉረመርምም።
:
➊.የቤቴ ብርሃን ፣ የትዳሬም ዘውድ አንተ ነህ።

➋.በረታው ሲደክም፣ የተሾመው ሲሻር አንተ ግን በዘመናት ያው ሁነህ አይሃለሁ።

➌.ያለመድኩት ጠባይህ፣ ይህ ብቻ ነው ብዬ ያልገለጥሁት ማንነትህ የተመሰገነ ይሁን።
:
♡አቤቱ ጌታዬ ሆይ፥

አንተ ልዑል ስትሆን የምረገጥ ጭቃ የሆንሁት እኔ አመሰግንህ ዘንድ መፍቀድህ በእውነት በመደነቅ እንዳመሰግንህ ያደርገኛል።

➊.የገዛ አቅሜ ሲከዳኝ በእርጅናዬ የማትጥለኝ ጓዴ አንተ ነህ።

➋.እስከ ማታ ይቆያል ያሉት በጥዋቱ ሲያልቅ አንተ ግን እንደ በዛህ ትኖራለህ።
:
➌.በክፉ ቀን ይቆምልኛል የምለው ራሱ ክፉ ቀን ሲሆን አንተ ግን በፍቅር ቅላፄ ታናግረኛለህ።
:
➍.ያየኸው እንጂ የገላመጥኸው ማንም የለም። ፊትህን ስትመልስ እደነግጣለሁ ፣ ስምህን ስጠራ ወዲያው አይዞህ ትለኛለህ።

➎.ደስታዬን ፈውሰህ ባንተ እንድደሰት ስለረዳኸኝ ፣ ነፍሴ ከእውቀት ተራቁታ እንዳታስቸግረኝ በብዙ ትምህርት የደገፍከኝ አንተ እንደሆንህ አውቃለሁ።
:
➏.በዚህ ዘመን ስላስነሣሃቸው አባቶችና ካህናት ምስጋና አቀርብልሃለሁ።
Join @ortodoxslijoch
1.8K views03:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 05:55:43 ስለምን ይጨነቃሉ?

፩•ስለ ኃጢአትዎ?-አይጨነቁ "ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች።" ይላል (ኢሳ ፩÷፲፰)- " እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና።"(ማቴ 11÷28)

፪• ስለ ሞት?-ምንም አያስቡ " ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤ሕያው የሆነም የሚያምንብኝም ሁሉ ለዘላለም አይሞትም፤ ይህን ታምኚያለሽን? አላት።* (ዮሐ 11÷26) -" ሰው ከሞት ወጥመድ ያመልጥ ዘንድ የጠቢብ ሰው ትምህርት የሕይወት ምንጭ ነው።" (ምሳ 13÷14)

፫• ስለ ፍርድ ቀን? ፣በጭራሽ " ስለዚህ እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና።" ይላል ( ማቴ24÷44) - "ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።" ተብሏል(ዮሐ 6÷40)

፬• ስለ መከራ? ፣ አያስቡ ቅዱስ ጳውሎስ "እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን ክፉም ደጉም ለበጎ መሆኑን ያስታውሱ።" ፣ብሎዎታል (ሮሜ 8÷28)

፭• ስለ ጤንነትዎ ? "ምን በወጣዎት " ልብሱን ብቻ የዳሰሰው እንደሆነ እድናለሁ ያለችውን ሴት ያስታውሱ ••• ልብ ይበሉ ።" የኢየሱስንም ወሬ ሰምታ በስተኋላው በሰዎች መካከል መጥታ ልብሱን ዳሰሰች። ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ እድናለሁ ብላለችና። ወዲያውም የደምዋ ምንጭ ደረቀ ከሥቃይዋም እንደዳነች በሰውነትዋ አወቀች።ወዲያውም ኢየሱስ ከእርሱ ኃይል እንደ ወጣ በገዛ ራሱ አውቆ በሕዝቡ መካከል ዘወር ብሎ። ልብሴን የዳሰሰ ማን ነው? አለ።" ( ማር 8÷27-30)

፮•ስለ ሀብት?: የሚያሳስብዎ አይሁን! " ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም። የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው።እናንተ፥ ይህ ሕዝብ ሁሉ፥ እኔን ሰርቃችኋልና በእርግማን ርጉሞች ናችሁ። በቤቴ ውስጥ መብል እንዲሆን አሥራቱን ሁሉ ወደ ጎተራ አግቡ፤ የሰማይንም መስኮት ባልከፍትላችሁ፥ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስስላችሁ በዚህ ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።፤ ስለ እናንተ ነቀዙን እገሥጻለሁ፥ የምድራችሁንም ፍሬ አያጠፋም፤ በእርሻችሁም ያለው ወይን ፍሬውን አያረግፍም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።የተድላ ምድር ትሆናላችሁና አሕዛብ ሁሉ ብፁዓን ብለው ይጠሩአችኋል፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።"( ት•ሚል፫÷፯-፲፪)

፯• ስለ ሥልጣን? አይቸገሩ " በእናንተስ እንዲህ አይደለም፤ ነገር ግን ማንም ከእናንተ ታላቅ ሊሆን የሚወድ የእናንተ አገልጋይ ይሁን፣ ከእናንተም ማንም ፊተኛ ሊሆን የሚወድ የሁሉ ባሪያ ይሁን፤ እንዲሁ የሰው ልጅም ሊያገለግልና ነፍሱን ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም።" ፣የሚለውን ልብ ያስታውሱ ( ማር 10÷43-44)

፰• ስለትዳር ፣? ሐሳብ አይግባዎ ።" የሰማይ አምላክ እግዚአብሔር፥ እርሱ መልአኩን በፊትህ ይሰድዳል፥ ከዚያም ለልጄ ሚስትን ትወስዳለህ።"፣(ዘፍ 24÷7) ብሎ ባሪያዎቹን የላከ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ መልካም ሚስት እንዳገኘለት አይዘንጉ።ስለዚህ ለእርሰዎም እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ አጋዥ ያገኛሉ እርሰዎ ግን በጸሎት ይትጉ! ጠቢቡ ሰሎሞን " ቤትና ባለጠግነት ከአባቶች ዘንድ ይወረሳሉ፤ አስተዋይ ሚስት ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ናት።"ይላል ( ምሳ ፲፱÷፲፬)

፱•ስለ ቤተሰብዎ ? ችግር የለም ። -በጸሎት በምልጃ ከምሥጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አቅርቡ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ" ይላል ( ፊልጵ ፬÷፮)

፲• ስለ ሰዎች? በፍጹም አይጨነቁ::ጳውሎስ ቅዱስ " በእምነት የደከመውንም ተቀበሉት፥ በአሳቡም ላይ አትፍረዱ።ሁሉን ይበላ ዘንድ እንደ ተፈቀደለት የሚያምን አለ፥ ደካማው ግን አትክልት ይበላል።የሚበላ የማይበላውን አይናቀው የማይበላውም በሚበላው አይፍረድ፥ እግዚአብሔር ተቀብሎታልና።አንተ በሌላው ሎሌ የምትፈርድ ማን ነህ? እርሱ ቢቆም ወይም ቢወድቅ ለገዛ ጌታው ነው፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ሊያቆመው ይችላልና ይቆማል።ይህ ሰው አንድ ቀን ከሌላ ቀን እንዲሻል ያስባል፥ ያ ግን ቀን ሁሉ አንድ እንደ ሆነ ያስባል፤ በገዛ አእምሮው አጥብቆ ይረዳ።"ይላል ሮሜ ፲፬÷፩-፭)
       በመ/ር ተመስገን ዘገዬ
3.1K views02:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 20:54:14 የቅድስት አርሴማ ታሪክ በአጭሩ

እናታችን ቅድስት አርሴማ እግዚአብሔርን በቅንነት ያገለግሉ ከነበሩ ከከበሩ ካህናት ወገን ከሆኑ ከቅዱስ ቴዎድሮስና ከእናቷ ቅድስት አትናሲያ በስዕለት ተወለደች፡፡

ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ብሉይን ሐዲስን ተምራ እያነበበች እንዲሁም በተግባር እየተረጎመች ዘወትርም በጸሎት ትተጋ እንደነበር ገድሏ ይተርካል፡፡ በዚህ ዘመን ድርጣድስ የሚባል በአርመን የነገሠ አረማዊ ንጉሥ ለጣዖት የሚሰግድ' ፀሐይንም የሚያመልክ' ክርስቲያኖችንም እኔ ለማመልከው አምላክ መስገድ አለባችሁ በማለት መከራ ያጸናባቸው ነበር፡፡
እናታችን ቅድስት አርሴማም ተጋድሎዋን የጀመረችው የዚህ ጨካኝ ንጉሥ አገልጋይ ወይም ሹም ፳፯ ክርስቲያኖችን እንደልማዱ እየደበደበ' እየገረፈና ልዩ ልዩ ስቃይ እያደረሰባቸው ሲወስዳቸው በማየቷ ነበር፡፡

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‘‘ለእነርሱና ለአሕዛብ ምስክር እንዲሆን ስለኔ ወደገዢዎችና ወደ ነገሥታት ትወሰዳላችሁ፡፡’’ (ማቴ. ፲፡፲፮፡፲፱)፡፡

ያለውን በማሰብ ቅድስት አርሴማም ገና በሃያ ዓመቷ የዚህን ዓለም ንጉሥ እኩይ ግብሩን በመንቀፍ ስለ ክርስቶስ ከሚሰቃዩ ወገኖቿ ጋር ግንባር ቀደም በመሆን ትመሰክር ጀመር፡፡ የንጉሡም አገልጋይ በደም ግባቷና በንግግሯ ማማር ተደንቆ በዚች በፈቃዷ ልትሠዋ በወደደች ሴት ምንም ሊያደርግባት ስላልወደደ ወደ ንጉሡ ወደ ድርጣድስ ከሃያ ሰባቱ ክርስቲያኖች ጋር ወሰዳት፡፡ ንጉሡም ብዙ የተነገረላትን ወጣት ሲያይ በውበቷና በንግግሯ ተማርኮ ለዓለማዊ ደስታውና ፍላጎቱ ተመኛት፡፡ ለእርሱም ሙሽራ እንድትሆን ብዙ ወተወታት፡፡ ቅድስት አርሴማ ግን ናቀችው ‘‘እኔ የሰማያዊው ንጉሥ የክርስቶስ ሙሽራ እንጂ የዚህን ዓለም አላፊ ጠፊ የሆነውን ገንዘብና ደስታ የምሻ አይደለሁም፡፡’’ በማለትም መለሰችለት፡፡

ንጉሡም ይህንን ከእርሷ በመስማቱ እጅግ ተቆጣ፤ በመናቁም ተበሳጨ፤ አሽከሮቹንም ጠርቶ በቤተ መንግሥቱ የታሰሩትን አንበሶች እንዲለቀቅባቸው አዘዘ፡፡ አንበሶቹ ግን ይደሰቱ ነበር፡፡

በኋላም ፊታቸውን ወደ ንጉሡና አገልጋዮቹ በማዞር ሩጠው እስኪደበቁ ድረስ አሳደዷቸው፡፡ ንጉሡ ይበልጥ ነደደው ክርስቲያኖቹ በረሃብ እንዲያልቁ እንዲታሰሩ አዘዘ፡፡ እግዚአብሔርም በአምስተኛው ቀን በብርሃን ቤቱን ሞልቶት የሚበሉትን በመሶብ የሚጠጡትን በጽዋ ከሰማይ አወረደላቸው፡፡ ንጉሡም ይህንን በማየቱ ከዚያ አውጥቶ በእሳት ውስጥም አስገባቸው፡፡ ሠለስቱ ደቂቅን የጠበቀ አምላክ እነርሱንም አዳናቸው፡፡ በሌላም በብዙ መንገድ ሊያጠፋቸው እንደሞከረ ገድሏ ይተርካል፡፡ በመጨረሻም ከአማካሪዎቹ ጋር ተማክሮ በሰይፍ እንዲያልቁ ይወስናሉ፡፡

እያንዳንዳቸውን ተራ በተራ ሲሰይፋቸው ቅድስት አርሴማ ለሚሰየፉት ሁሉ የድል አክሊል ከሰማይ ሲወርድላቸው ትመለከት ስለነበር የእርሷን ተራ በጉጉት ትጠብቀው ነበር፡፡ በመደሰቷም እየጸለየች አይዟችሁ ጽኑ ትላቸው ነበር፡፡
በመጨረሻም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጽናቷን ተመልክቶ ቃል ኪዳን ይገባላታል፡፡

ንጉሡም ሌሎቹን አሰይፎ ሲያበቃ ወደሷ ዞሮ በቁጣ እየጮኸ አንቺን እንደ ባልንጀሮችሽ በቀላሉ አልገልሽም ስቃይሽን አጸናብሻለሁ ብሎ ለአገልጋዮቹ ትእዛዝ በመስጠት አይኗን አስወጥቶ በእጇ ያሲዛታል፤ ጡቷን ያስቆርጣል፤ በኋላም አንገቷን ያሰይፋታል በዚሁ ሁኔታ እናታችን ሰማዕትነትን ተቀበለች፡፡
ይህንን ሁሉ መከራ ስለአምላኳ ስትል እራሷን አሳልፋ የሰጠች ድንቅ ሰማዕት ናት፡፡

ነቢዩ ዳዊት በመዝሙሩ ‘‘ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ’’ (መዝ.) እንዳለ ለእናታችንም የገባላት ቃል ኪዳን ‘‘በእኔ ስም አምነሽ የዚህ ዓለም ተድላና ደስታ ሳያታልልሽ አንገትሽን ለሰይፍ ሰጥተሽ ተሰይፈሻል፤ የሰማዕትነት ተጋድሎ ፈጽመሻልና ስምሽን የጠራ፤ በዓልሽን ያከበረ፤ ዝክርሽን የዘከረ፤ ገድልሽን የጻፈና ያጻፈ፤ የሰማና ያሰማም እስከ ፲፪ ትውልድ ድረስ እምርልሻለሁ’’ ሲል ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡

በዚህም መሠረት በሷ አማላጅነት አምኖ እገዳሟም ሄዶ በጸሎት የተማጸናት ሁሉ ለችግሩ መፍትሄ አግኝቶ እንደሚመለስ እሙን ነው፡፡ የቅድስት አርሴማ ረድኤት በረከት ጸሎትና ምልጃ ከእኛ ጋር ይኑር፡፡

አሜን አሜን
አሜን የእናታችን በረከቷ ይደርብን!!!!
ወስብሓት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር አሜን
     Join @ortodoxslijoch
4.7K views17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 07:45:45 በስርአተ ተክሊል ለማግባት መስፈርቱ ምንድነው?

መልስ።ተክሊል ማለት ክብር ማለት ሲሆን ቃሉም ከለለ አከበረ ጋረደ ከሚለው ግስ የወጣ ዘር ነው።በተክሊል ወንድ «የባሏ ክብር ናት»የተባለች ረዳቱን በፅኑ ኪዳን ወይም በመንፈስ ውል የሚቀበልበት ስለሆነ የተክሊል ጋብቻ የከበረ ነው።ለሴቷም እንዲሁ።እንዲሁም በእግዚአብሄር ስለሚቀደስና ስለሚከበር የተክሊል ጋብቻ ቅዱስ ነው። ዕብ1÷12
የመጀመሪያው ጋብቻ በእግዚአብሄር ፈቃድ በኤደን ገነት እንደተመሰረተ ሁሉ ዛሬም ስርአተ ተክሊል በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይፈፀማል።

ዘፍ1÷22 በመሆኑም ስርአተ ተክሊሉ የተሞላ የሚሆነው ፀሎት ተክሊሉ ተፈፅሞ ወጣቶች ቅዱስ ስጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበሉ ብቻ ነው።ለዚህ ክብርና የተቀደሰ ጋብቻ ለመብቃትም የሚያስፈልጉ ነገሮች።

1.የሀይማኖት አንድነት
ወጣቶች በሀይማኖት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች መሆን አለባቸው።

2.ድንግልና
የተክሊል ስርአት የሚፈፀምላቸው ወጣቶች ራሳቸውን ከዝሙት ጠብቀው በድንግልና የፀኑ መሆን አለባቸው።

3.መፈቃቀድ:
የሚጋቡት ወጣቶች አንዳቸው ሌላውን ሊፈቅዱ ሊወዱ ያስፈልጋል።የሁለቱ መፈቃቀድ ሳይኖር በወላጆች ተፅእኖ ብቻ ስርአተ ተክሊል ጋብቻ ሊፈፀም አይችልም ።
ለዚነው በስርአቱ ላይ አንደኛው ሌላውን «ወድጀ ፈቅጀ የምቀርበው»አንዳንድ ግዜ ለምንድነው ወደ ቤተ-ክርስቲያን ተቀብያታለው ወይም ተቀብየዋለው ብለው ቃል የሚገቡት።

4.እድሜ
የሚጋቡት ወጣቶች እድሚያቸው ትዳር የሚጠብቀውን ሀላፊነት ለመወጣት ብቁ ሊሆኑ ያስፈልጋል ለዚህም አስቀድሞ በፍትሀ ነገስት እንደተገለፀው ሴቷ 15ወንዱ ደግሞ 18አመት የሞላቸው መሆን አለባቸው ።እንደዚህም ሁኖ ሌሎች ነገሮች ካልተሟሉ ከዚህ በላይ ቢሆን መልካም ነው።

5.የንስሀ አባት ምስክርነት
ስርአተ ተክሊል የሚፈፀምላቸው ወጣቶች አስቀድመው ንስሀ እየገቡ ንፅህናቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ የግድ የንስሀ አባት ሊይዝ ያስፈልጋል።ለንስሀ አባታቸውም ስለጋብቻቸውም ሆነ ስለ ማንኛውም ህይወታቸው ሊያማክሩ ይገባል ።
በዘመናችን አልፎ አልፎ እንደሚታየው «ገንዘብ ከፍየ ወይንም ደብረ ሊባኖስ ሂጀ አገባለው»እያሉ ተደብቆ ስርአተ ተክሊል መፈፀም አይቻልም።ተጋቢወች ካላይ የተጠቀሱትን ማሟላታቸውን በንስሀ አባት ሊረጋገጥና ይህም ሊመሰከርላቸው ያስፈልጋል።በመሆኑም የተጋቢወች መንፈሳዊም ሆነ ስጋዊ ኑሮ በንስሀ አባታቸው ፊት የተገለጠ ሊሆን ይገባል።

6.ሁለቱም ተጋቢወች ወይንም ከሁለቱ አንዱ ወገን ራሱን የቻለ ሊሆን ያስፈልጋል ።የኢኮኖሚ አቅማቸውም ቤተሰቡን ለማስተዳደር በቂ መሆኑ ሊረጋገጥ ይገባል

7.ስለ ትዳር ማወቅ (በቂ ግንዛቤ)
ተጋቢወች ከመጋባታቸው በፊት ስለ ትዳርና አጠቃላይ ስለ ተክሊል ጋብቻ በሚገባ ሊያውቁ ይገባል።

ትዳር በሶስተኛው ሰው ግፊት የሚፈፅምና ለጥቅማጥቅም ተብሎ ካልሆነም ለሙከራ የሚገባበት ሳይሆን ከልብ በመነጨ ፍቅርና ለትዳር ባለወ ግንዛቤ ስለትዳር በቂ እውቀት መኖር ግድ ይላል ስለተክሊም ቢሆን ከ አባቶችና በሰንበት ትምህር ቤት በቂ እውቀት ሊኖር ይገባል
እንግህ ተጋቢወች ከዚህ በላይ የተጠቀሱትን ነጥቦች ካሟሉ የተቀደሰውን የስርአተ ተክሊል ጋብቻ ሊፈፀምላቸው ይችላል።በተረፈ ከአፅዋማት ቀን በቀር ይፈጽልማ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለዘላለም ትኑር
ወስብሓት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር አሜን
     Join @ortodoxslijoch
1.4K views04:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ