Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxslijoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.17K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ምንማማርበት :መዝሙር: ስብከቶች ይተላለፋል !

መንፈሳዊ ትምህርቶች : መንፈሳዊ ጥያቄዎች : ስብከት : መዝሙር : ይቀርብበታል #ጉዞው ገዳማት #ሰማህታት ታሪክ ይቀርባል!
FacebookGroup : ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ይቀላቀሉ ::

#shear

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-02-06 12:31:26 የተዋህዶ ልጆች የቲክቶክ ቻናላችንን ይቀላቀሉን ድምፃችን ለአለም እናሰማ

https://vm.tiktok.com/ZMF3tx8oJ/
978 views09:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 08:05:02 #እንኳን_ለጾመ_ነነዌ_በሰላም_አደረሳችሁ


" #ምነው_ተኝተሃል ? እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ያስበን እንደ ሆነ ተነሥተህ አምላክህን ጥራ" አለው። ትንቢተ ዮናስ 1:6 ።

#የዚህ ፆም ጊዜ ሶስት ( 3 ) ቀን ብቻ ነው ። ቀኖቹም በየዓመቱ ሰኞ ማክሰኞ ረቡዕ ናቸው ። የነነዌ ፆም በመባጃ ሐሙስ( አቆጣጠር ) ከፍ እና ዝቅ ስለሚል አንድ ጊዜ በጥር አንድ ጊዜ በየካቲት ይሆናል ።

የቤተ ክርስቲያን አባቶች ይህን ፆም የወሰኑት ልትጠፋ የነበረች ነነዌን በፆም ምክንያት እግዚአብሔር ይቅር ስላላት ይህን አምላካዊ ይቅርታውን ለዘለዓለም ለማሰብና ዛሬም በዚህ ዓለም ከነነዌ የከፋ ርኩሰትንና ኃጢያትን ስላለ የነነዌ ሕዝብ ይቅር ያልክ አምላክ ዛሬን ይቅር በለን ለማለት ነው

++ የነነዌ ሰዎችም እግዚአብሔርን አመኑ ለፆም አዋጅ ነገሩ
ከትልቁም ጀምሮ እስከ ትንሾቹም ማቅ ለበሱ ወሬውም ለነነዌ ንጉስ ደረሰ። እርሱም ከዙፋኑ ተነስቶ መጎናፀፊያውን አውልቆ ማቅንም ለበሰ። አመድ ላይም ተቀመጠ አዋጅንም አስነገረ።

++ በነነዌም ውስጥ የንጉሱንና የመኳንቱን ትእዛዝ አሳወጀ እንድህም አለ ሰዎችም እንስሶችም አንዳችም እንዳይቀምሱ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ። ሰወችና እንስሳትም በማቅ ይከደኑ። ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ። ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ። እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይፀፀት እንደሄነ ከፅኑ ቁጣውስ ይመለስ እንደሆነ ምን ያውቃል በማለትም አሳሳበ።

++ እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸውም እንደተመለሱ በስራቸውም አየ። እግዚአብሔር አምላክም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተፀፀቶ አላደረገውም
ት ዮናስ ( ፫ ፤ ፭-፲ )

የነነዌ ህዝብን በምህረቱ የጎበኘ ቸር አባት ለሀገራችንም ለህዝባችንም ምህረትና ቸርነቱን ያብዛልን ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን አሜን ፫
ለመንፈሳዊነት ቅድሚያ እንስጥና የእግዚአብሔርን ብድራት እንጠብቅ፡ እግዚአብሔር ጾማችንን ጾመ ድህነት ጾመ ስርየት ሰይጣንን ድል መንሻ

፣የኃጥያት መደምሰሻ ፣ መንግስተ
ሰማያትን መውረሻ ያድርግልን
ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር
2.5K views05:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 05:12:04 #ተው_ዓለም_ተመለስ

ተው ዓለም ተመለስ ተው ዓለም ተገታ
ተው ዓለም ተመለስ ተው ዓለም ተገታ
በቁጣ መዓቱ ይቀጣሃል ጌታ ይቀጣሃል ጌታ

ትውልዱ ተመታ በታላቅ በሽታ /፪/
ኧረ በልክ ይሁን ጭፈራና ደስታ /፪/
በማዕበል በጎርፍ እያየህ ሲቀጣ/፪/
አሁንም ተመለስ የከፋ ሳይመጣ /፪/
#አዝ
ነነዌን ሊያጠፋ የወረደው እሣት /፪/
አንተን እዳይመታህ ተነሳ ለጸሎት/፪/
ዓለም ብትሰጥኽ አንተ እድትተጋ /፪/
ሀልወተ እግዚአብሔር እንደምን ይዘንጋ
#አዝ
ችግር ለበዛበት እጅግ ለታወከው/፪/
አምላክ መሐሪ ነው ለተንበረከከው/፪/
የዓለም መድሐኒት የዓለሙን ቤዛ /፪/
ጠይቀው ምሕረትን ሠው ሆይ ልብ ግዛ
#አዝ
ተው ዓለም ተመለስ ተው ዓለም ተገታ
ተው ዓለም ተመለስ ተው ዓለም ተገታ
በቁጣ መዓቱ ይቀጥሃል ጌታ ይቀጣሃል ጌታ።

ሊቀ መዘምራን
ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ
2.7K views02:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 18:45:55 ብጹ አቡነ ሺኖዳ ብዙ ሺህ ህዝብ በተገኙበት ጉባኤ እያስተማሩ እያሉ ከግብፅ

ገጠራማ ቦታ የመጣ አንድ ዲያቆን ጥያቄ በወረቀት ጽፎ ላከ፡፡በአካባቢያቸው በአክራሪዎች
ብዙ ክርስቲያኖች እንደሚገደሉ እና መፍትሔ እንዲሠጣቸው ነበር የጠየቀው፡፡
ሺኖዳም ከአስር ሺህ ለማያንሱ ተማሪዎቻቸው
እንዲህ ሲሉ ጠየቁ

# ኢየሱስ ክርስቶስን ትወዱታላችሁ ?
ህዝቡም ለ3 ደቂቃ ያህል በእልልታ አጨበጨበ፡፡
ምን ጥያቄ አለው ብለው መመለሳቸው ነበር፡፡
ጳጳሱም ሌላ ጥያቄ አቀረቡ፡፡

# አብራችሁት ትሞታላችሁ ?
በዚህን ጊዜ ሁሉም ከተቀመጡበት ተነሱ፡፡ለረዥም
ደቂቃዎች አጨበጨቡ፡፡

# ያመኑት ለመኖር ብቻ ሳይሆን ለመሞት እንደሆነ አረጋገጡ፡፡
# ይህ ነው ጥሪያችን !
#ይህ ነው ክርስትና! ትንሣኤ ያለ ሞት የታለ?

••••••ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ
የተጠመቅን ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንድንሆን ዘንድ እንደተጠመቅን አታውቁምን?
ሮሜ 6÷3

ቅድስነታቸው አቡነ ሺኖዳ
በረከታቸው ይደርብን
Join @ortodoxslijoch
Join @ortodoxslijoch
5.5K views15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 19:18:06 ኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጠራው አስቸኳይ ጉባዔ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል፡፡

1. በብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት እና የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች፤ የክፍል ኃላፊዎች፤ ካህናት፤ አገልጋዮች እና ምእመናን ላይ የተፈጸመውንና እና እየተፈጸመ ያለውን ሕገ ወጥ እስር እና ወከባ ቅዱስ ሲኖዶስ በፅኑ አውግዟል፤

2. በጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ከተማ በደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን፤ ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ የወጡት ምዕመናን ላይ ጭካኔ በተሞላ ሁኔታ የተፈጸመው ሕገ ወጥ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና የተፈጸመው አሰቃቂ የሞት ድርጊትን ፍጹም ታወግዛለች፤ ተገቢውን ሲኖዶሳዊ እና ሃይማኖታዊ ጸሎት በማድረግ በሁሉም አጥቢያ ሥርዓተ ፍትሐት እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤

3. ቅዱስ ሲኖዶስ በጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም ባስተላለፈው ውሳኔ እና በሰጠው መግለጫ መላው የቤተ ክርስቲያኒቱ ተከታዮች ጾመ ነነዌን ሙሉ የሱባዔ ጊዜ በማድረግ ጥቁር ልብስ ያለውን ትርጓሜ በመግለጥ እንድንሰነብት መግለጫ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡

3.1. ለዚህም ዝርዝር አፈጻጸም መመሪያ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ከጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 3 ቀናት በመላው ዓለም የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ የምትገኙ ማናቸውም ካህናት እና ምዕመናን ሙሉ ጥቁር ልብስ በመልበስ በየአብያተ ክርስቲያናት እና በገዳማት ያለውን ሥርዓተ ጸሎት እንድትመሩ እና እንድትከታተሉ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤

3.2. በየትኛውም እንቅስቃሴ ይህንን ጥቁር ልብስ በመልበስ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ንቁ በመሆን እንድትፈጽሙ፤ ሆኖም ግን ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን ዓለም አቀፍ የጸሎትና የምህላ መርሐ ግብር ካወጀበት ቀን በኃላ በተለያዩ ከተሞች የጥቁር ልብስን ሆነ ተብሎ ከገበያ እንዲወጣ እየተደረገ መሆኑን በመረዳታችን ምዕመናን ያላችሁን ተመሳሳይ አልባሳት በመጠቀም የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔን በእንቅስቃሴያችሁ ሁሉ እንድትፈጽሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤

3.3. በነዚህ ቀናት ውስጥ አገልግሎቱ በድምጽ ማጉያ እንዲከናወን እና የሙሉ ጊዜ ሆኖ በሰባቱ የጸሎት ሰዓታት እየተጠበቀ በተመሳሳይ ሰዓታት ለአምስት ደቂቃ ያህል በማያቋርጥ ደወል በመደወል የማስተጋባት ሥራ እንዲሠራ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤

3.4. ይህንንም የየአህጉረ ስብከት፤ የወረዳ ቤተ ክህነት እና የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ሰበካ ጉባኤያት በመከታተል እንድታስፈጽሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

3.5. የአኃት አብያተ ክርስቲያናት፤ የኦርቶዶክስ ዓለም፤ እውነቱን የምታውቁና የምትደግፉ ማናቸውም ኃይማኖታዊም ሆነ ማህበራዊ ተቋማት እና ግለሰቦች የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ጥሪ በመደገፍ በአንድነት ትቆሙ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላፋለን፡፡

4. በነዚህ የጸሎትና የምሕላ ጊዜያት የደነደኑ ልቦች ወደ ልቦናቸው ተመልሰው የቤተ ክርስቲያኒቱን ጥሪ ሰምተው የማይፈጽሙ እንደሆነ

4.1. በየካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናት እና ምእመናን ከጠዋቱ 11፡00 ጀምሮ በየአጥብያቸው በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት እስከ ጠዋቱ 1፡30 ድረስ ሥርዓተ ቅዳሴው ከተፈጸመ በኃላ ከጠዋቱ 2፡00 ላይ ሁሉም ገዳማት፣ አድባራት እና አብያተ ክርስቲያናት በተመሳሳይ ሰዓት ደወል በመደወል ምእመናን በሙሉ እስከ ጠዋቱ 2፡30 ድረስ እንዲሰባሰቡ በማድረግ ከየአጥቢያው በመነሳት የጥምቀተ ባህር ወይም የመስቀል አደባባይ ላይ ታቦተ ሕጉን በማክበር፤ በማጀብ በዝማሬ እና በእልልታ በአንድ ቦታ በመሰባሰብ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

4.2. የዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ዝርዝር አፈጻጸም መመሪያን በተመለከተ በአጭር ጊዜ ውስጥ የምናሳውቃችሁ መሆኑን አውቃችሁ ዝግጅት እንድታደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል፡፡ 

5. ማንኛውም የመንግሥት የጸጥታ ኃይል ቤተ ክርስቲያን ያዘዘችውን ሰላማዊ ጥያቄ በሚከወንበት ማንኛውም የአገልግሎት ጊዜ ተግባራቱ ሰላማዊ መሆናቸውን በመገንዘብ ተገቢውን ጥበቃ የማድረግ ግዴታ እንዳለበት አውቆ እንዲያስፈጽም ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል፤

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ
ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
4.0K views16:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 12:44:56 መዝሙረ ዳዊት 45

1. አምላካችን መጠጊያችንና ኃይላችን፥
ባገኘን በታላቅ መከራም ረዳታችን ነው።

ከክፉ ነገር የምንዋጋበት ኃይላችን ብንሸሽም የምንጠጋበት ጋሻችን እግዚአብሔር ብቻ ነው:: በመጣብን ታላቅ መከራም ከእርሱ በቀር ረዳት የለንም::

2፤ ስለዚህ ምድር ብትነዋወጥ፥
ተራሮችም ወደ ባሕር ልብ ቢወሰዱ አንፈራም።

እግዚአብሔርን ረዳታችን መጠጊያችን ኃይላችን ብለን አምነናልና ምድር የተባሉ ሰዎች በቁጣ ቢነሡብን እንደተራራ የገዘፉ ሰዎችም ወደ ዙሪያችን ቢመጡ አንፈራም::

አንድም ተራሮች ወደ ባሕር ልብ ቢወሰዱ አንፈራም

እንደ ተራራ ያከበርናቸው ሰዎች ክብራቸውን ትተው ባሕር ወደ ተባለች ወደዓለም ውስጥ ጭልጥ ብለው ቢገቡና ራሳቸውን ቢያዋርዱ አንፈራም

እንደ ተራራ የገዘፈ የእምነት ጽናት ያላቸው ሰዎች ቢክዱ በባሕር ክህደት ልብ ቢወሰዱ አምላካችን ኃይላችን መጠጊያችን ነውና አንፈራም::

ተራሮች አባቶች ከእምነት ቢናወጹ
ወደ ባሕር ልብ ውስጥ ሸፍተው ቢሔዱ ቀድሞም መጠጊያችን አምላካችን ነውና አንፈራም::


3፤ ውኆቻቸው ጮኹ ተናወጡም፥
ተራሮችም ከኃይሉ የተነሣ ተናወጡ።

ጉልበተኞች በቁጣ ተነሡ መጡ መጡ ሲባል ሰምተን ነበር:: ኃያላን ሁሉ ከእግዚአብሔር ኃይል የተነሣ ፈራርሰዋል::

በየዘመናቱ ብዙዎች በቁጣ ተነሥተውብን ነበረ:: የሚያምንን ሰው ዓይኑን አያሳየኝ ብለው ጮኹ ተናወጡም:: ሆኖም ልባቸው እንደ ተራራ ያበጠ ሁሉ ኃይላችን መጠጊያችን ረዳታችን በሆነው በእግዚአብሔር ተናወጡ::

4: የወንዝ ፈሳሾች የእግዚአብሔርን ከተማ ደስ ያሰኛሉ፤ ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።

መከራ እንደወንዝ ቢፈስስባት የእግዚአብሔር ከተማ ቤተ ክርስቲያን አዝና ተከፍታ አታውቅም::
የመከራ ፈሳሾች ቤተ ክርስቲያንን ደስ ያሰኙአታል::

ልጆችዋን የሚያጠነክርላት ወደ ቤቱ የሚመልስላት
በንስሓ የሚያጸዳላት በሰማዕትነት አክሊል የሚያከብርላት ነውና የወንዝ ፈሳሾች የእግዚአብሔርን ከተማ ቤተ ክርስቲያንን ደስ ያሰኛሉ::

እንደ ወንዝ ከሰማይ ወደ ምድር የሚወርዱ መላእክትም ቤተ ክርስቲያን በጥበቃቸው ደስ ያሰኙአታል::

ልዑል እግዚአብሔር ማደሪያው ቤተ ክርስቲያንን ለየ:: በመከራዋ ደስ የምትሰኝ ስለ ቁስልዋ የምትዘምርና ሐሴት የምታደርግ ቤቱን ከዚህ ዓለም ክፋት ሁሉ ለየ::

5፤ እግዚአብሔር በመካከልዋ ነው አትናወጥም፥
እግዚአብሔርም ፈጥኖ ይረዳታል።

የምትናወጽ የምትበጠበጥ ይመስላል እንጂ ቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔር በመካከልዋ ነውና አትናወጥም::

"ጥበቃዬን አንሥቻለሁ" የማይል አምላካችን እግዚአብሔር አምላክዋ ነውና አትናወጥም:: በእሳት ሠረገላ ዙሪያዋን የሚከብባት በማይተኛ አምላክ የምትጠበቅ ናትና አትናወጥም::

6፤ አሕዛብ ተናወጡ መንግሥታትም ተመለሱ፤
እርሱ ቃሉን ሰጠ፥ ምድርም ተንቀጠቀጠች።

ቤተ ክርስቲያንን የናቁ ሁሉ ከክብራቸው ተዋረዱ
በቁጣ የተነሡባት ሁሉ ወደ ኋላቸው ተመልሰዋል::

ዝም ያለ የሚመስለው አምላክ ስለ ቤተ ክርስቲያን እርሱ ቃሉን ሰጠ፥ ምድርም ተንቀጠቀጠች።

7፤ የሠራዊት ጌታ ከእኛ ጋር ነው፤
የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው።

በምድር ካሉ ሠራዊት ሁሉ የሚበልጡ መላእክት ጌታቸው እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው::
ብንሸሽም መጠጊያችን እሱ ነው::

8፤ የእግዚአብሔርን ሥራ፥ በምድር ያደረገውንም ተኣምራት እንድታዩ ኑ።

እግዚአብሔር በሰማይ ብቻ ያለ ይመስላችሁ እንደሆነ በምድርም የሚሠራውን ድንቅ ነገር ታዩ ዘንድ ኑ::

9፤ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ጦርነት ይሽራል፤
ቀስትን ይሰብራል፥ ጦርንም ይቈርጣል፥
በእሳትም ጋሻን ያቃጥላል።

የምንነደፍበትን ቀስት ሰብሮ የምንወጋበትን ጦር ቆርጦ ከጋሻ ጋር ያቃጥላል:: ጦርነትም ይሻራል:: ኃይላችን እርሱ ነውና ጦር አንሻም:: ጋሻችንም እርሱ ነውና::

10፤ ዕረፉ፥ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ እወቁ፤
በአሕዛብ ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፥ በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ።

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል :- ዕረፉ፥ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ እወቁ፤
በአሕዛብ ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፥
በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ።

11፤ የሠራዊት ጌታ ከእኛ ጋር ነው፤
የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው።

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥር 27 2015 ዓ.ም.
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
1.7K views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 20:28:43 የቲክቶክ ቻናላችንን ይቀላቀሉን

https://vm.tiktok.com/ZMF3tx8oJ/
926 views17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 13:02:50 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፤ ቅዱስ ሲኖዶስ ጾመ ነነዌን በማስመልከት ጾምና ጸሎት አወጀ።

ቅዱስ ሲኖዶስ አዋጁን ያስተላለፈው ዛሬ ከደቂቃዎች በፊት በሰጠው መግለጫ ነው።

ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ በቤተክርስቲያኗ በተከሰተው ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና አስተዳደራዊ መዋቅሮች በጣሰ ሁኔታ መፈንቅለ ሲኖዶስ በማድረግ በሕገወጥ መንገድ ኤጲስ ቆጶስነት ሢመት በሰጡትና በተሾመ ግለሰቦች ላይ ጥር 18 ቃለ ውግዘት ታላልፎ እንደነበር ገልጿል።

" ይሁን እንጂ እነዚህ ሕገወጥ ቡድኖች ከድርጊታቸው ሊታቀቡ አልቻሉም " ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ ከዚህም በላይ በመንግሥት ኃይሎች በመታገዝ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምታስተዳድራቸውን መንበረ ጵጵስናዎችንና ቢሮዎችን በኃይል በመውረርና በመስበር ከፍተኛ ጥፋት እያደረጉ ነው ብሏል።

እንዲሁም የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆችን ፣ ሠራተኞች ካህናትና ምእመናን በማሰርና በማንገላታት ላይ ይገኛሉ ሲል ገልጿል።

ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ መንግሥት ሕግ ከማስከበር ይልቅ ለሕገ ወጥ ቡድኖች ድጋፍ በመስጠት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕግና መብት ሊያስከብር አልቻለም ያለ ሲሆን " ሁሉን ማድረግ ወደሚቻለው አምላካችን በመማፀን ጸሎትና ምሕላ ማድረጉ አስፈላጊ መሆኑን ተረድተናል " ሲል አሳውቋል።

በዚህም " ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ በመላው ዓለም የሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያን #ጥቁር_ልብስ ብቻ በመልበስ በጾምና በጸሎት ምሕላ በመያዝ በቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምሕረት በመገኘት ወደ እግዚአብሔር ጾም፤ ጸሎትና ምሕላ እንድታቀርቡ " ሲል ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪ አስተላልፏል።

" ጥቁር ልብስ  የምንለብሰው በመከራ መጽናት ለመግለጽ ነው " ሲልም አክሏል።
Join @ortodoxslijoch
3.0K viewsedited  10:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 08:01:05 #ፆመ_ነነዌ_ለምን_ይፆማል ?
#መቼ_ይጀምራል ? ………………………………………………
ፆመ ነነዌ ከቤተ ክርስቲያናችን የአዋጅ ፆሞች ውስጥ አንዱ ሲሆን ፆሙ ሶስት ( 3 ) ቀን ብቻ ነው ። ቀኖቹም በየዓመቱ ሰኞ ማክሰኞ ረቡዕ ናቸው ። የነነዌ ፆም በመባቻ ሐሙስ( አቆጣጠር ) ከፍ እና ዝቅ ስለሚል አንድ ጊዜ በጥር አንድ ጊዜ በየካቲት ይሆናል ።

እናም የ2015 ፆመ ነነዌ ጥር 29 ሰኞ ይጀምራል። የቤተ ክርስቲያን አባቶች ይህን ፆም የወሰኑት ልትጠፋ የነበረች ነነዌን በፆም ምክንያት እግዚአብሔር ይቅር ስላላት ይህን አምላካዊ ይቅርታውን ለዘለዓለም ለማሰብና ዛሬም በዚህ ዓለም ከነነዌ የከፋ ርኩሰትንና ኃጢያትን ስላለ የነነዌ ሕዝብ ይቅር ያልክ አምላክ ዛሬን ይቅር በለን ለማለት ነው

የነነዌ ሰዎችም እግዚአብሔርን አመኑ ለፆም አዋጅ ነገሩ ከትልቁም ጀምሮ እስከ ትንሾቹም ማቅ ለበሱ ወሬውም ለነነዌ ንጉስ ደረሰ። እርሱም ከዙፋኑ ተነስቶ መጎናፀፊያውን አውልቆ ማቅንም ለበሰ። አመድ ላይም ተቀመጠ አዋጅንም አስነገረ።

በነነዌም ውስጥ የንጉሱንና የመኳንቱን ትእዛዝ አሳወጀ እንድህም አለ ሰዎችም እንስሶችም አንዳችም እንዳይቀምሱ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ። ሰወችና እንስሳትም በማቅ ይከደኑ።

ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ። ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።
እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይፀፀት እንደሄነ ከፅኑ ቁጣውስ ይመለስ እንደሆነ ምን ያውቃል በማለትም አሳሳበ።

እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸውም እንደተመለሱ በስራቸውም አየ። እግዚአብሔር አምላክም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተፀፀቶ አላደረገውም
ት ዮናስ ( ፫ ፤ ፭-፲ )

የነነዌ ህዝብን በምህረቱ የጎበኘ ቸር አባት ለሀገራችንም ለህዝባችንም ምህረትና ቸርነቱን ያብዛልን ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን አሜን ፫
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
።።። # ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
።።።።። # ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። # ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።
Join @ortodoxslijoch
4.4K viewsedited  05:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 05:29:07 ቤተ ክርስቲያናችን እንደወትሮው ሁሉ አሁንም መከራ አልተለያትም:: በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያ እየተቀበልን ጸንተን መቆም የሚጠበቅብን ሲሆን በሚከተለው መንገድ ደግሞ ቤተ ክርስቲያናችንን እንድናግዛት በአክብሮት እጠይቃለሁ:: (መቼም ጸልዩ ማለት የዲያቆን ሥራ ነው)

የክርስቲያኖች ትልቁ መሣሪያችን እጃችንን ለጸሎት ወደ ሰማይ መዘርጋት ነው:: ዕንባችንም እንደ ራሔል ዕንባ ባሕርን ይከፍላል:: ራሳችንን በንስሓ ካዋረድንና ካለቀስን የማንቀለብሰው ነገር የለም::

የፊታችን ሰኞ የሦስት ቀናቱ ጾም ጾመ ነነዌ ይገባል::

ጾሙ ከመግባቱ አስቀድሞ ኦርቶዶክሳውያን ሁላችን ንስሓ እንግባ:: በመጪዎቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ ይህንን ያያችሁ ወንድሞቼና እኅቶቼ ሁላችሁ ንስሓ አባቶቻችሁን ምስክር አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር ተናዘዙ:: "ጌታ ሆይ ይህ የሆነው በእኔ በደል ነውና ኃጢአቴን ይቅር በለኝ" ብለን አብረን አምላካችንን እንማጸነው::

ከዚህ ንስሓ ጋር የታወጀውን የየነነዌ ጾም ጠዋት በኪዳንና ከሰዓት በቅዳሴ ማታ ደግሞ በጸሎተ ምሕላ በየአጥቢያችን እየተገኘን አምላካችንን እንማጸነው::
የቻልን ሦስቱን ቀናት እስከ ማታ እየጾምንና እየሰገድን የፈጣሪያችንን ምሕረት እንለምን::

በሦስት ቀን ጾም የነነዌን መዓት የመለሰ : በሦስት ቀን ጾም የግብፅን ተራራ ያፈለሰ የነስምዖን አምላክ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ሊመጣ ያለውን እሳት ሁሉ በቸርነቱ ይመልስልን ዘንድ በልባችን ጉልበት እንስገድ::

ከቤተ ክርስቲያን አንድነት የተለዩትን እንዲመልስልን!
በዚህ ምክንያት የሚጠፉ ነፍሳትን እንዲጠብቅልን!
የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መናወጽ የሚሻውን ሁሉ እንዲያስታግሥልን ወደ ፈጣሪያችን በጋራ እንጩኽ::

በየጊዜው ለችግራችን ስእለት እንደምንሣለው አንድ ጧፍ እንኩዋን ስለ ቤተ ክርስቲያን ሰላም ስእለት አድርገን እንጸልይ:: አርከ መሀይምናን (የምእመናን ወዳጅ) ለቤተ ክርስቲያንም ቅን መሪን የሚሠጥ ሰላማዊ ኢየሱስ ክርስቶስ በፊቱ ስለሚማልሉ የዋሃን ብሎ ሰላማችንን ይመልስልን::

"እግዚአብሔር እንዳይቀየማቸው ከመዓትም ተመልሶ ፍጹም ዕረፍትን ይሠጣቸው ዘንድ ስለ በደሉ አባቶቻችንና ወንድሞቻችን እንማልዳለን" በእንተ ቅድሳት

#ነነዌ_ኢትዮጵያ
#ንስሓ_ግቡ
#ትጉና_ጸልዩ
#አንዲት_ቤተ_ክርስቲያን
#አንድ_ሲኖዶስ
#አንድ_ፓትርያርክ
#eotc_one_holy_synod
#one_church
#one_patriarch
#his_holiness_abune_mathias
#oriental_orthodox
3.4K views02:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ