Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxslijoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.17K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ምንማማርበት :መዝሙር: ስብከቶች ይተላለፋል !

መንፈሳዊ ትምህርቶች : መንፈሳዊ ጥያቄዎች : ስብከት : መዝሙር : ይቀርብበታል #ጉዞው ገዳማት #ሰማህታት ታሪክ ይቀርባል!
FacebookGroup : ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ይቀላቀሉ ::

#shear

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-02-01 06:16:56 #ጥር ፪፬ አቡነ #ተክለሃይማኖት

. ጥር 24 የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሐይማኖት ስባረ አጽማቸው ነው፤ በረከታቸው ይደርብን፡፡

የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው ፥ እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል፡፡ 《መዝ 34፣19》

ጥር 24 የኢትዮያዊው ጻድቅ ብጹእ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ስባረ አፅማቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በታላቅ ድምቀት አክብራ የምትውልበት ታላቅ ቀን ነው።

አባታችን ኢትዮጵያዊው ፃድቅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለ22 ዓመታት ደብረ ሊባኖስ በሚገኘው ደብረ አሰቦ ዋሻ ውስጥ ሲፀልዩ ከመቆም ብዛትም እግራቸውን አጥተዋል።

ለዓመታት ከቆሙበት ሳይቀመጡ ከፊት ከኋላ ከጐን እና ከጐን ምንም ሳይደገፉ በአንድ ቦታ በመወሰን ለ22 ዓመታት ደብረ ሊባኖስ በሚገኘው ደብረ አስቦ ዋሻ ውስጥ ሲፀልዩ ከመቆም ብዛትም እግራቸውን አጥተዋል።

ከዚያም ለ7 ዓመታት በአንድ እግራቸው ቆመው ፀሎታቸውን ቀጠሉ። ስለ ክብራቸውም ከእግዚአብሔር ክንፍ ተሰጥቷቸዋል። በአጠቃላይ ለ29 ዓመታት በጸሎት ቆይተዋል።
ዕረፍታቸውም በተወለዱ በ99 ዓመት ሲሆን ቀኑም ነሐሴ 24 ቀን ነው።

በዚህም መሠረት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ለዕረፍታቸው በእግዚአብሔር ፊት ለከበረና ብዙ ክብር ለተሰጣቸው አባታችን በየዓመቱ ነሐሴ 24 ቀን በዓለ ዕረፍታቸውን ታህሳስ 24 ቀን በዓለ ልደታቸውን ዛሬ ጥር 24 ደግሞ ስባረ አፅማቸውን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች።

የአባታችን የፃድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ጸሎታቸው እና አማላጅነታቸው ቤተክርስቲያናችንን አገራችንን ኢትዮጵያን እና እኛን ህዝቦቿን ከፈተና ይጠብቀን ዘንድ በቃልኪዳናቸው ያስቧት አሜን!!!

ወስበሐት ለእግዚአብሔር
ወወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
Join @ortodoxslijoch
3.5K viewsedited  03:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-31 06:08:12 ትምህርት ሃይማኖት (የሃይማኖት ትምህርት)
በሁለት ይከፈላል፡፡

ይኸውም፦
1ኛ፡- ዶግማ
2ኛ፡- ቀኖና በሚል ነው፡፡
#ዶግማ ፡- ቃሉ የግሪክ ሲሆን ፍችውም እምነት ማለት ነው፡፡
#ቀኖና ፡- ደግሞ ቃሉ የግሪክ ሲሆን ሥርዓት ማለት ነው፡፡

#ዶግማ ወይም እምነት ስንል ምንም ነገር አይጨመርበትም ፤ አይቀነስበትም፤
አይሻሻልም፤ ችግርና ፈተናም ቢመጣ እስከ ሞት ድረስ አጥብቀን የምንይዘው
ነው፡፡

#ለምሳሌ
ያህል ይህን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የፈጠረ፤ ቢመረምር እንጂ
የማይመረመር ሁሉን
ቻይ አምላክ፤ የሚሳነው ነገር የሌለ ፈጣሪ፤ የሰማይና የምድር ባለቤት
የሠራዊትጌታ ሕያው #እግዚአብሔር ነው፡፡ #እግዚአብሔር (ፈጣሪ) የአካል
ሦስትነት አለው፡፡

በመለኮት፣
በመፍጠር፣
በሥልጣን፣
በአገዛዝ፣ በፈቃድ ግን አንድ ነው፡፡
#በሦስትነቱ
አብ፤
ወልድ፤
መንፈስ
ቅዱስ ሲባል
#በአንድነቱ አንድ # መለኮት አንድ እግዚአብሔር ይባላል፡፡

በአዳም ምክንያት ከመጣው የዘለዓለም ሞትና ከዲያብሎስ ባርነት ነጻ
የወጣነው ከሦስቱ አካላት በአንደኛው አካል ማለትም በወልድ በኢየሱስ
ክርስቶስ ነው፡፡ ይህ #ዶግማ ወይም እምነት ይባላል፡፡

#ቀኖና ግን በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ያደጉ ክርስቲያኖች
የሚመሩበት ሥርዓት ስለሆነ፤ በሃይማኖት #አባቶች ወይም # በቅዱስ
#ሲኖዶስ አማካኝነት እንደጊዜው ሁኔታ #የሚሻሻል በመሆኑ የሚጨመርበት፤
የሚቀነስለት ነው፡፡

#ለምሳሌ
1ያህል እኛ ኦርቶዶክሳውያን የምንጠመቀው ሴት በሰማንያ ወንድ በአርባ
ቀናችን ነው፡፡

የተወለዱ ሕጻናት ሴቷ ሰማንያ ወንዱም አርባ ቀን ሳይሞላቸው
#ቢታመሙና በሽታው አስጊ ከሆነ በ10፣ በ20፣ በ30…ቀናቸው #መጠመቅ
#ይችላሉ ቀኖና ነውና፡፡

2በቤተ ክርስቲያናችን የቀዳስያን ብዛት መነሻው አምስት ነው፡፡ ምናልባት
ከአምስቱ አንዱ፤ ሁለቱ፤ ሦስቱ ቢታጡና ሌላም ተፈልጎ እስከ መጨረሻ
የማይገኝ ከሆነ ከአቅም በላይም የሆነ ችግር ከገጠመ ሁለቱ ወይም አንዱ ብቻ
ቀድሰው ማቁረብ ይችላሉ፡፡ #ቀኖና ነውና፡፡

3በቤተ ክርስቲያናችን
ታቦት ሲከብር ቤተ ክርስቲያኑን የሚዞረው ሦስት ጊዜ ነው ችግር ካለ አንድ
ጊዜ ብቻ ዑደት ተፈጽሞ ሊገባ ይችላል። #ቀኖና ነውና።

#ስለቀኖና ( # ስለሥርዐት )
#ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ እንዲህ ሲል ጽፏል።

፩. ‹‹ነገር ግን ሁሉን በአግባብና በሥርዐት አድርጉ፡፡›› 1ኛ ቆሮ. 14፥40፡፡

፪. ‹‹ወንድሞች ሆይ በሠራንላቸው ሥርዐት ሳይሆን በተንኮል ከሚሄዱት
ወንድሞች ሁሉ ትለዩ ዘንድ #በጌታችን #በኢየሱስ # ክርስቶስ ስም
እናዝዛችኋለን፡፡

#እኛን ልትመስሉ እንደሚገባችሁ እኛም በእናንተ መካከል ያለ ሥራ እንዳልኖርን
ራሳችሁ ታውቃላችሁ›› 2ኛተሰ. 3፥6-7››

#ቀኖና (ሥርዐት) የሚወሰነው በሃይማኖት አባቶች እንደሆነና
#ወንጌልን
የሚስተምር ሰው ለሚያስተምራቸው ክርስቲያኖች በሃይማኖት አባቶች የተወሰነ
ቀኖና ማስተማርና መሰጠት እንዳለበት #መጽሐፍ #ቅዱስ እንዲህ ሲል
ያስረዳል፡፡

በየከተማውም ሲሄዱ፥ ሐዋርያትና ቀሳውስት በኢየሩሳሌም ያዘዙትን /
የወሰኑትን/ ሥርዐት አስተማሯቸው፡፡
#አብያተ ክርስቲያናትም በሃይማኖት ጸኑ ዕለት ዕለትም ቁጥራቸው ይበዛ
ነበር፡፡›› ይላል የሐዋ. 16፥4-5፡፡

በዚህ #የእግዚአብሔር ቃል መሠረት ቅዱስ #ጳውሎስ ደርቤንና ልስጥራን
በተባሉ ቦታዎች ለነበሩ ክርስቲያኖች ወንጌልን ከሰበከ በኋላ #ሐዋርያት
የወሰኑትን #ቀኖና (ሥርዐት) እነደሰጣቸው እንረዳለን፡፡

ስለዚህ ቀኖና ወይም ሥርዐት ቤተክርስቲያንን ይጠቅማል እንጂ አይጎዳም፡፡

በመሆኑም #ዶግማንና #ቀኖናን ወይም እምነትንና ሥርዓትን ጎን ለጎን ይዞ
መጓዝ ሐዋር
Join @ortodoxslijoch
4.3K views03:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-30 06:44:36 ​​እንኳን ለቅዱስ ዑራኤል አመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳቹ አደረሰን!

መልዐኩ ቅዱስ ዑራኤልና አገልግሎቱ በጥቂቱ

ዑራኤል የሚለው ስም "ዑር"እና ኤል ከሚለው ሁለት ቃላት የተመሰረተ ነው ። ትርጉሙም ብርሃነ ጌታ አምላክ ብርሃን ነው። ማለት ነው።

ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ መብረቅና ነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው።በመሆኑም መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበቁ ነጓድጓድ ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። (መጽሐፈ ሄኖክ ፮፥፪)

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከእየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግብጽ ስትሰደድ መንገድ እየመራ፤ ከእስራኤል ወደ ግብጽ ከዚያም ከእመቤታችን ጋር በሀገራችን ኢትዮጵያ እየመራ ያመጣት መልአክ ነው።

ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሆኖ በተሰቀለበት ጊዜ፥ክቡር ደሙ በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃን ነሳንስ የረጨው እሱ ነው።

ለነብዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ልቦና ያጠጣው፥ጥበብን ማስተዋልን የሰጠው የጠፉ መጽሓፍት በቃሉ አስታውሶ እንደገና ያጻፈው የረዳው መልአክ ነው።(ዕዝ፲፫፥፴፱)

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ትዕዛዝ ብዙ ድርሰት የደረሱት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ጽዋ ህይወት ስላጠጣቸው ነው።

በዓላቱም በዓመት 3ናቸው።
፩...ጥር። 22 በዓለ ሲመቱ፤
፪....መጋቢት 27 የጌታችንን ደም በዓለም የረጨበት፤
፫...ሐምሌ 21 እና 22 ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ።

በጸሎቱ የተማጸነ ከእግዚአብሔር አምላክ በረከትን ፣ምህረትን የሚያሰጥ አዛኝ ጠባቂ ና የዋህ መልአክ ነው።በተለይም ህጻናትን የሚጠብቅ የሚለምኑትን ሁሉ የሚሰማ ፥ኃጢአተኞች ካሉበት ቦታ እኔን ላከኝ እያለ አምላኩን የሚማጸን አዛኝ የዋህ መልአክ ነው።

ይህ አለም በአማላጅነቱ አምኖ በእምነት ጸበሉን ቢጠጣ ፥ዝክሩንም ቢዘክር ከክፉ በሽታው እንደሚድን፤ እንደሚፈውሰው ቃል ኪዳን ተሰጥቶታል ።

ቅዱሳን መላዕክት እግዚአብሔርን በሚፈሩ ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራሉ ከመከራም ያድኑዋቸዋል።(መዝ ፴፫÷፯) የአባታችን የጠባቂያችን የአማላጃችን የመልአኩ የቅዱስ ዑራኤል ቃል ኪዳን አይለየን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
join @ortodoxslijoch
5.4K views03:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-28 07:00:05 ነገ ጥር 21 አስተርዮ # ማርያም ባአለ እረፈት # ለማርያም

# እመቤታችን በ64 አመቷ # ጥር21 በ49 ዓ-ም ያረፈችበት እለት መታሰብያ ክብረ ባአል ነዉ
ተናገራ÷እዝራ ተናገራ ዳዊት ዘመራ /2/
እዝራ በመሰንቆ ዳዊት በበገና እያጫወቷት
ሳታቀዉ አረፈች ያንን መራራ ሞት ዳዊት ዘመራ

# ጌታችን ለእናታችን # ለቅድስት ድግል # ማርያም ብዙ ቃልኪዳንን ከገባላት ቡኃላ ቅድስት ነፍሷን ከክብር ስጋዋ ለይቶ በቃለ አቅርን በዝማሬ አሳረጓት ደቀ መዛሙርቱን ምከያሉበት ዳመና ጠቅሶ እመቤታቹሁን ቅበሩ አላቸዉ በአጎበር አድርገዉ እናትና አባቷ ወደተቀበሩበት ወደተጌ ሴማኒ ሲወስዶት አይሁዱ አይተዉ ልጇ ተነሳ አረገ እያሉ ሲአዉኩን ኖሩ አሁን ደግሞ እሷ ተነሳች አረገች እያሉ ሊአዉኩን አይደለምን ? ንዑ ናአዉያን ሥጋሃ ለማርያም

# ስጋዋን # እናቃጥልባቸዉ # ብለዉ # ተነሱ
ለዚሁም ተመካከላቸዉ ታዉፋኒያ የተባለዉ የጎበዝ አለቃ መረጡ እሱም ያልጋዉን ሾንኮር ሊአቃጥል ሲይዝ የታዘዘመላክ መጥቶ ሁለት እጁን በሰይፍ ቆረጠዉ
በድያለሁ ማረኝ ብሎ ቢማፀናት እራሷን ዘንበል አድርጋ ቅዱስ ጴጥሮስን እደነበረ አድርግለት ብላ አዘዘችዉ እርሱንም እጁን አድኖለታል

ከዚህ ቡኃላጌታችን ከመካከላቸዉ ነጥቆ ከገነት ከዕፀ ህይወት ስር አኑራታል! ሀዋርያት የቀበሯት ግን ከ6 ወር ብኃላ በነሀሴ 14 ነዉ ሞት በጥር ነኃሴ መቃብር እዲሉ

ጊዜ ዕረፍት ለሶሊያና ለሶልያና( ለማርያም)
ወረደ ወልድ ዲበ እምዲበ ልዕልና ወረደ
ሶልያና የእመቤታችን የማርያም ሌላስሟነዉ

የእመቤታችን እረፍት ሊቁ ቅዱስ ያሪድም ሞትስ ለመዊት ይደሉ÷ ሞት ለማርያም የአጽብ ለኩሉ÷ ሞት ለሚምት ሰዉ ሁሉ የተገባ ነዉ የማርያም ምትግን ሁሉን ያስደንቃል
የቅድስ ድግል ማርያም ምልጃዋ በረከቷ ይደርብን አሜን
# ፍርስዬ # ገነተ # ኢየሱስ # ወይብላ # ማርያም # ዛሬ

# ከመንበሯ # ወታ # ፅበል # አድራ # ነገ # በደመቀ # መልክ
# ትመለሳ # የስፍሬ # ደብር # እንኳን # አደርሳችሁ # አደርስን
ባለ ፀጋ እመቤት ባለ ፀጋ እናት አፍሰናል ከደጅሽ
ብዙ በረከት ወጀቡን ቀዝፈናል ብለን ማርያም
እንዘምራለን እስከ ዘላለም!! እናቴ ምልጃዋ
አይለየን ጥሩ ነገር የምንሰማበት
ቀን ታርግልን
አሜን + አሜን + አሜን
Join @ortodoxslijoch
8.4K viewsedited  04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 22:12:39 +++ +++
ሁኑ!
--------------------------------------------------------------

★ " እንግዲህ የሰማይ አባታችሁ ፍጹም እንደሆነ እናንተ ፍጹማን ሁኑ " ( ማቴ 5:48) ።

★ " ስለዚህ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ " ( ማቴ 10:16) ።

★ " ከእናንተ ታላቅ ሊሆን የሚወድ የእናንተ አገልጋይ ይሁን፣ ከእናንተ ማንም ፊተኛ ሊሆን የሚወድ የሁሉ ባርያ ይሁን " ( ማር 10:44) ።

★ " አባታችሁ ርኀሩኀ እንደሆነ ርኀሩኆች ሁኑ" ( ሉቃ 6:36) ።

★" በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ " ( ሮሜ 12:11) ።

★ " ለጸሎት ትተጉ ዘንድ ተስማምታችሁ ለጊዜው ካልሆነ በቀር እርስ በእርሳችሁ አትከላከሉ ።ራሳችሁን ስለአለመግዛት ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ ፣ [ለባልና ለሚስት] ( 1ኛ ቆሮ 7:5) ።

★ " የሚያለቅሱም እንደማያለቅሱ ፣ደስ የሚላቸውም ደስ እንደማይላቸው ፣የሚገዙም ምንም እንደሌላቸው፣ በዚህ ዓለም የሚጠቀሙ በሙሉ እንደማይጠቀሙባት ይሁኑ ፣ የዚህች ዓለም መልክ አላፊ ነውና "( 1ኛ ቆሮ 7:31) ።

★ " ወንድሞች ሆይ :- በአእምሮ ሕፃናት አትሁኑ ፣ለክፋት ነገር ሕፃናት ሁኑ እንጂ ፣በአእምሮ የበሰሉ ሁኑ " ( 1ኛ ቆሮ 14:20) ።

★" እንግዲህ ወንድሞች ሆይ: - ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፣ የማትነቃነቁም ፣የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ! " ( 1ኛ ቆሮ 15: 58 ) ።

★ " ስለዚህም ጌታ :- ከመካከላቸው ውጡና የተለያችሁ ሁኑ ፣ ርኩስንም አትንኩ ይላል " ( 2ኛ ቆሮ 6: 17 - 18) ።

★ " በቀረውስ ወንድሞች ሆይ :- ደህና ሁኑ ።ፍጹማን ሁኑ ፣ ምክሬን ስሙ ፣ በአንድ ልብ ሁኑ ፣በሰላም ኑሩ፣ የፍቅርና የሰላም አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል " ( 2ኛ ቆሮ 13:11) ።

★ " ወንድሞች ሆይ :- እናንተ ለአርነት ተጠርታችኋልና ፣ብቻ አርነታችሁ ለሥጋ ምክንያትን አይስጥ ፣ነገር ግን በፍቅር እርስ በእርሳችሁ እንደባሪያዎች ሁኑ " ( ገላ 5: 13) ።

★ " እርስ በርሳችሁም ቸሮችና ፣ ርኀሩሆች ሁኑ ፣ እግዚአብሔር ደግሞ በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ ይቅር ተባባሉ "( ኤፌ 4:32) ።

★ " እንግዲህ እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ " ( ኤፌ 5:1) ።

★ " ለእያንዳንዳችሁ በክርስቶስ ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ " ( ኤፌ 5:21) ።

★" በቀረውስ በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ! " ( ኤፌ 6:10)።

★" ወንድሞች ሆይ :- እኔን የምትመስሉ ሁኑ ፣ እኛም ምሳሌ እንደምንሆንላችሁ እንዲሁ የሚመላለሱትን ተመልከቱ "( ፊሊ 3:17)።

★ " በአንድ አካልም የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ ፣ የምታመሰግኑም ሁኑ! "( ቆላ 3:15) ።

★ " እርስ በርሳችሁ በሰላም ሁኑ " ( 1ኛ ተሰሎ 5:13) ።

★ " ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምታደርጉ ብቻ አትሁኑ " ( ያዕ 1:22) ።

★ " ዳሩ ግን:- እኔ ቅዱስ እንደሆንሁ ቅዱሳኑ ሁኑ ተብሎ ስለተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ "( 1ኛ ዼጥ 1:15 - 16) ።

★ " አርነት ወጥታችሁ እንደ እግዚአብሔር ባሪያዎች ሁኑ እንጂ ያ አርነት ለክፋት መሸፈኛ እንዲሆን አታድርጉ " ( 1ኛ ዼጥ 2:15 -16)።

★ " በመጨረሻው ሁላችሁ በአንድ ልብ ሁኑ ፣ የሌላው መከራ ለእናንተ እንደሚሆን አድርጉ ፣ እንደ ወንድሞች ተዋደዱ ፣ርኀሩኆችና ትሑታን ሁኑ " ( 1ኛ ዼጥ 3:8) ።

★ " በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያት ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ ፣ነገር ግን በየዋሕትና በፍርሃት ይሁን " ( 1ኛ ዼጥ 3:15 )።

★ " ለመንጋው ምሳሌ ሁኑ እንጂ ማኀበሮቻችሁን በሃይል አትግዙ " ( 1ኛ ዼጥ 5:3) ።

★" እስከ ሞት ድረስ የታመንህ ሁን ፣ የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ " ( ራእ 2:10 ) ።
Join @ortodoxslijoch
6.4K views19:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 16:18:16 + አቤቱ ቅጣኝ ነገር ግን እንዳታዋርደኝ! +

እግዚአብሔር ፍቅር ነው ፣ መሐሪ ነው ፣ ይቅር ባይ ነው፡፡ ፍቅር ይቆጣል ወይ? ይቅር ባይስ ይቀጣል ወይ? ብዙዎቻችን ስለ ክርስቶስ ሲነገረን መሐሪነቱና ፍቅሩ ብቻ ቢነገረን አንጠላም፡፡ ጨርሶ የማንፈራው እግዚአብሔር እንፈልጋለን፡፡ እንዲህ አታድርግ! የሚለን ሲመጣ ‘አትፍረድ’ እንላለን ፤ ቆይተን ግን የሰማዩን ዳኝም አትፍረድ ማለት ይቃጣናል፡፡ ቅጣት የሌለበት ክርስትና እንሻለን፡፡

ይህ ዓይነቱን ክርስትና ‘ጣፋጭ ክርስትና’ {የስኳር ክርስትና ይሉታል} ምንም ምሬት የሌለበት ሁሌም ማር ማር የሚል ሕይወት አድርገው ክርስትናን የሚሰብኩም ብዙ ናቸው፡፡ ‘አይዞህ ብትታመም ትፈወሳለህ ፣ ቤትህ ይሞላል ፣ ቀዳዳህ ይደፈናል ፣ ብትበድልም አትቀጣም’ ብቻ የሚሉ ስብከቶች የስኳር ክርስትና ስብከቶች ናቸው፡፡ ይህንን ብቻ የሚያጮሁ ሰዎች ክርስቶስ ‘የምድር ጨው ናችሁ’ ያለውን ትተው የምድር ስኳር ለመሆንና ዓለምን ለማስደሰት የሚፈልጉ ናቸው፡፡
በእርግጥ እግዚአብሔር ይቆጣል ወይ? አዎን ይቆጣል! እንዲህ ይላል መጽሐፉ

‘እግዚአብሔር ቀናተኛና ተበቃይ አምላክ ነው እግዚአብሔር ተበቃይና መዓትን የተሞላ ነው እግዚአብሔር ተቃዋሚዎቹን ይበቀላል፥ ለጠላቶቹም ቍጣውን ይጠብቃል። በቍጣው ፊት የሚቆም ማን ነው? የቍጣውንም ትኵሳት ማን ይታገሣል? መዓቱ እንደ እሳት ይፈስሳል፥ ከእርሱም የተነሣ ዓለቶች ተሰነጠቁ’ ናሆ 1፡1፣6
‘‘ከቍጣው የተነሣ ምድር ትንቀጠቀጣለች አሕዛብም መዓቱን አይችሉም’’ ኤር 10፡10
‘‘እኛ በቍጣህ አልቀናልና፥ በመዓትህም ደንግጠናልና’’ መዝ. 90፡7

እግዚአብሔር በተቆጣ ጊዜ የሚመልሰው የለም፡፡ ቅዱሳን የቁጣውን መጠን ስለሚያውቁ በትሕትና ይለምኑታል፡፡

ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር ቁጣ ደጋግሞ ቢነግረንም አንድ ሌላ ደስ የሚያሰኝ ነገርም ነግሮናል፡፡ የእግዚአብሔር ቁጣው ለዘላለም አይደለም፡፡ "ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" ይላል እንጂ "ቁጣው ለዘላለም ነውና" አይልም:: የእግዚአብሔር ቁጣ ጊዜያዊ ነው፡፡

‘መሐሪ ነኝና ለዘላለም አልቆጣም’ ኤር 3፡12
‘ቁጣው ለጥቂት ጊዜ ሞገሱ ግን ለሕይወት ዘመን ነው’ መዝ 29፡5
‘ጌታ ለዘላለም አይጥልም ቢያሳዝንም እንደ ምሕረቱ ብዛት ይራራል ፤ የሰው ልጆችን ከልቡ አያስጨንቅም አያሳዝንምም’ ሰ.ኤር 3፡31

የፈጣሪን የነነደ የቁጣ እሳት ማጥፋት የሚቻለን በዕንባ ነው፡፡ በደላችንን አምነን ቅጣት ይገባናል ነገር ግን መሐሪ ነህና ማረን ማለት ይገባል፡፡ ንጉሥ ዳዊት ‘አቤቱ በቁጣህ አትቅሠፈኝ በመዓትህም አትገሥፀኝ’ ብሎ የፈጣሪን ቁጣ አበረደ፡፡ /መዝ 38፡1/ ነቢዩ ኤርያስም ‘አቤቱ ቅጣኝ ነገር ግን እንዳታዋርደኝ በመጠን ይሁን እንጂ በቁጣ አይሁን’ ብሎ ተለማመጠ፡፡ ኤር 10፡24

አንድ ሠዓሊ በጣም ብዙ ደክሞ የተጠበበትን ሥዕሉን የፈለገ ቢበሳጭ ለረዥም ጊዜ ያንን ሥዕል ለመሳል የተጠበበትን ጥበብ አስቦ ሥዕሉን ወደ እሳት አይጨምረውም፡፡ አባ ጊዮርጊስ እንዲህ ሲል ይለምናል ‘ሠዓሊ ሥዕሉን ያጠፋል ወይ? [ጌታ ሆይ እኔን ስትፈጥር የተጠበብክበትን] የቀደመ ጥበብህን አስብ እንጂ! አስበህም ማረኝ! [ያጠፋዖኑ ለሥዕሉ ሠዓሊ ፤ ኪነተከ ዘትካት ኀሊ]

ይቅርታውን በንስሓ ለሚለምኑ ሁሉ ምሕረቱ ቅርብ ነው፡፡ በቀኝና በግራው ወንበዴዎች በተሰቀሉበት በዕለተ አርብ የግራው ወንበዴ ሲሰድበው ጌታ መልስ አልሠጠም፡፡ የቀኙ ወንበዴ ማረኝ ሲለው ግን ከአፉ ተቀብሎ በገነት ትሆናለህ አለው፡፡ ቁጣው የራቀ ምሕረቱ የበዛ እርሱ የራበው ሰው ለምግብ የሚቸኩለውን ያህል ይቅር ለማለት ይቸኩላል፡፡ ‘ምሕረትን ይወድዳልና ቁጣውንም ለዘላለም አይጠብቅም ተመልሶ ይምረናል ፤ ክፋታችንንም ይጠቀጥቃል ፤ ኃጢአታችንንንም በባሕሩ ጥልቅ ይጥለዋል’ ሚክ 7፡18

ልጆች ሳለን ጥፋት ስናጠፋ ከወላጆቻችን እንደበቃለን፡፡በተደበቅንበት ሰዓት ውስጣችን በፍርሃት ይርዳል፡፡ ‘ዛሬ ገደለኝ’ ‘ዛሬ መሞቴ ነው’ ብለን እንጨነቃለን፡፡ የሚደርስብንን ቅጣት እጅግ አጋንነን ከመፍራታችን የተነሣ መሬት ተሰንጥቃ ብትውጠን አንጠላም፡፡ በዚያ ሁሉ ጭንቀት ውስጥ ግን ወላጆቻችንም እስኪያገኙን ይጨንነቃሉ፡፡ እግዚአብሔርም እንዲህ ነው፡፡ አጥፍቶ በገነት ዛፎች መካከል የተሸሸገ አዳምን ወዴት ነህ ብሎ የፈለገ እርሱ እኛንም ይፈልገናል፡፡ አዳም ከገነት ሳይባረር ገነት ውስጥ እንደጠፋ ፈጣሪ ሳያባርረን ራሳችንን በኃጢአት ተሸማቅቀን ያባረርን እኛን ይፈልገናል፡፡ እርሱ ስለመጥፋትህ ይጨነቃል አንተ ‘ዛሬስ አይምረኝም’ ትላለህ፡፡

የሚገርመው በጥፋታችን ከተደበቅንበት ወላጆቻችን ካገኙን በኋላ ሁለተኛው ዙር ጭንቀታችን ‘ምን አጥፍተህ ነው የተደበቅከው’ መባል ነው፡፡ ጥፋታችንን ሲያውጣጡን እንንቀጠቀጣለን፡፡ ያጠፋነውን ስለምናውቀው ስንት እንደሚያስገርፈንም እናውቀዋለን፡፡ ‘ብትናገር ይሻላል? ግዴለህም!’ ብለው አግባብተውም አስፈራርተውም ወላጆቻችን ጥፋታችንን ያውጣጡናል፡፡ እየፈራን ያጠፋነውን ጥፋት ስንናዘዝ ግን ወላጆቻችን በጥፋታችን ቅጥል ብለው ‘አልመታህም ተናገር’ ያሉንን ረስተው የዱላ ዝናም ያዘንቡብናል፡፡ እግዚአብሔር ግን ጥፋትህን ስትነግረው ቁጣው የሚገነፍል አባት አይደለም፡፡
’’ኃጢአታችንን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነፃን የታመነና ጻድቅ ነው’ 1ዮሐ 1፡9

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
5.5K views13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 07:40:52 ☞ ሱባዔ_ምንድ_ነው ?

ሱባኤ በሰዋሰው ትርጉሙ "ሰባት"ማለት ሲሆን በመንፈስ አተረጋጎም አንድ ሰው ከዚህ ቀን እስከ ዚህ ቀን በጸሎት ከፈጣሪየ ጋር እገናኛለሁ ብሎ የሚያቅደው መንፈሳዊ ዕቅድ ነው ፡፡ ሰባት ቁጥር በእስራኤላውያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው፡፡ ለምሳሌ ፦ ፈጣሪ አለማት እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፋጥረትን ከመፋጠር ማረፋ ፥ለጸሎት የሚተጉ ምዕመናን በቀን ለሰባት ጊዜ ማመስገናቸው የሰባት ቁጥር ፋጹምነት ያመለክታል ፡፡ [ዘፍ 2*2 , መዝ 118*164 ] አንድ ሰው 7 ቀናት ቢጾም "አንድ ሱባኤ ጾመ" ይባላል ፡፡

☞ ሱባኤ መቼ ተጀመረ ?

የተጀመረው ከውድቀት በሓላ በመጀመርያው ሰው በአዳም ነው፡፡ ቅዱሳን መላእክት አዳምን ጸሎት እንዳስተማሩት የቤተ ክርስቲያናችን መዛግብት ያስረዳሉ በምላሹም ከልጅ ልጅህ ተወልጄ ስጋን ለብሼ ከ 5 ቀን ተኩል በኋላ አድንሃለሁ የሚለውን ቃል ኪዳን የሰማው ሱባኤ በመግባቱ ነው፡

☞ ሱባዔ_ለምን?

የሰው ልጅ ሓጢአት በሚስማማው የሥጋ ሰውነቱ ዘወትር ፈጣሪውን ይበድላል ፡፡ በፈፀመው በደል ኀሊናው ይወቅሰዋል ይጸጸታል ፡፡በመጀመርያ ደፋሮ በሰራው ሀጥያት በኋላ ይደነግጣል ይህ በማንኛውም ሰብአዊ ፋጥረት ኀሊና ውስጥ የሚፈራረቅ ክስተት ነው ፡፡ በዚህ ግዜ የፈጣሪውን ይቅርታ ለማግኝት ያስባል ይተክዛል፡፡ ሰው በደፋርነቱ የኃያሉን አምላክ ትእዛዝ ተላልፎ አለም ሲያስጨንቀው ሸክሙን የሚያቃልልበትና የሚያስወግድበት መንፈሳዊ ጥበብ ከቸሩ ፈጣሪ ተሰጥቶታል፡፡ ይህውም በጥቂት ድካም ሥጋ ያልተወሰነ ጸጋ እግዚአብሔር የሚያገኝበት ሥርዓት ሱባኤ ነው፡፡
➊ እግዚአብሔርን_ለመማጸን ፦
ማንኛውም ሰው ሱባኤ ሲገባ በቁርጥ ወደ ፈጣሪው የሚያቀርበው ተማፅኖ ሊኖረው ይገባል ፡፡ ምንም የምንጠይቀው ( የምንማፀነው) ነገር ሳይኖር ሱባዔ ብንገባ የምናገኝው መልስ አይኖርም ፡፡ ስለዚህ ሱባኤ ከመግባታችን በፊት ፦ሱባዔ የምንገባው ለምንድን ነው ? በማለት እራሳችንን መጠየቅ ይኖርብናል ፡፡
➋ የቅዱሳንን_በረከት_ለመሳተፍ
ቅዱሳን አባቶችና እናቶች የተጋደሉትን ተጋድሎ በማዘከር ቃል ኪዳን በተሰጣቸው ገዳማትና አድባራት የሚገባ ሱባኤ የቅዱሳን በረከት ተካፋይ ያደርጋል፡፡ በጾመ ነብያት የነብያትን ፤ በጾመ ሀዋርያት የሀዋርያትን ፤በጾመ ፋልሰታ የእመቤታችንን በረከት ለመሳተፋ ሱባኤ መግባት የነበረ ነው፡፡

☞ የሱባኤ_አይነቶች

1 የግል ሱባኤ ( ዝግ ሱባኤ) ፦ አንድ ሰው ብቻውን አመች ቦታ ማንም ሳያየው በግሉ የጸሎት በአቱን ዘግቶ በሰቂለ ኀሊና ሆኖ ፈጣሪው ብቻ እንዲያየው በኀቡዕ የሚፈፅመው ሱባኤ ነው ፡፡
2 ,የማህበር ሱባኤ ፦ ካህናት ምዕመናን ወንዶች ሴቶች ሽማግሌወች ፤ወጣቶች ፤በአንድ ሆነው በቤተ ክርስትያንና አመች በሆኑ ቦታወች ሁሉ ተሰብስበው የሚገብት ሱባዔ ነው፡፡
3 , የአዋጅ ሱባዔ ፦ በሀገር ላይ ድንገተኛ አደጋ ፤ አባር ቸነፈር ጦርነት ሲነሳ እንዲሁም በማህበረ ምዕመናን ላይ አስጊ የሆነ መቅሰፋት ሲከሰት እግዚአብሔር መዓቱን በምህረት ቁጣውን በትዕግስት እንዲመልስ የሚያዝ የሱባዔ አይነት ነው፡፡

☞ቅድመ_ዝግጅት
ሱባኤ ከመግባታችንም ሆነ ከገባን ግዜ እንዲሁም ከጨረስን በኋላ ምእመናን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ይገባናል ፡፡
➊ ሱባኤ_ከመግባት_አስቀድሞ
፩ በመጀመርያ ሱባዔ የምንገባበትን ምክንያት ለይቶ ማወቅ ያስፈልጋል ፡፡
፪ ሱባኤ ለመግባት የወሰንበትን ምክንያት ከለየን በኋላ ምክንያታችንን ይዘን የንስሃ አባታችንን ማማከር ያስፈልጋል፡፡
፫ ለምን ያህል ቀናት መቆየት እንዳለብን መወሰን ያስፈልጋል ፡፡ሱባኤ ከዚህ እስከዚህ እቆያለሁ ብለን ዕቅድ የምንይዝበት ነው፡፡
፬ ወቅትና ቦታ መምረጥ ተገቢ ነው፡፡በቤተ ክርስቲያናችን በአብዛሀኛው ግዜ ሱባኤ የሚገባው በአጽዋማት ወቅት በመሆኑ ይህንን መለየት ነው ፡፡ምክንያቱም በጾም ወቅት ብዙ አባቶች ጸሎት የሚይዙበት ስለሆነ ፀሎታችን ከእነርሱ ጋር አብሮ ያርግልናልና ነው፡፡ እዚህ ላይ በማንኛውም ግዜ ሱባኤ አይያዝም ለማለት አይደለም በማንኛውም ግዜ ፈተና ያጋጠመው ሰው ሱባዔ ሊይዝ ይችላል፡፡
➋ በሱባኤ_ግዜ
ሀ. በጸሎት ሰአት ዓምድና ግድግዳ ሳይደገፉ መቋሚያ ሳይዙ በሁለት እግር ቀጥ ብሎ በመቆም መጸለይ ይኖርብናል፡፡ እንዲሁም ፊትን ወደ ምስራቅ መልሶ መቆም ወደ ግራ ወደ ቀኝ አለመዟዟር በሰቂለ ህሊና ኾኖ መጸለይ ይገባል፡፡
ለ . በቅደም ተከተል መፀለይ ይገባል በመጀመርያ አአተብ ከሚለው ተጀምሮ አቡነ ዘበሰማያትን ጠቅሶ ጸሎተ ሀይማኖትን መጨረስ ፡፡ሰግዱ እና ስለ መስቀል በሚያነሳው ላይ እየሰገዱና እያማተቡ መጸለይ ፡፡ በማስቀጠል አቡነ ዘበሰማያት ፤መዝሙረ ዳዊት ውዳሴ ማርያም ሌሎችንም ማስከተል ከዚያ 41 ግዜ ኪራላይሶ ይባላል ፡፡
ሐ. በሱባዔ ግዜ ከተሐራሚው የሚጠበቀው ነገር ሐጢአቱን እያሰበ ማዘን ማልቀስ ለእያንዳንዱ በደል ማልቀስ ማዘን ይገባዋል ፡፡
መ. በመጨረሻም ሱባዔ የገባው ሰው ሱበዔውን ሳይጨርስ ወይም አቋርጦ ከማንኛውም ሰው ጋር ፈፅሞ መገናኝት የለበትም ፡፡
➌ ከሱባዔ_በኋላ
ላቀረብነው ተማፅኖ እግዚአብሔር የሚያደርግልንን ነገር መጠበቅ ይኖርብናል ፡፡ "ሱባዔ" የገባ ሰው ሁሉ ራዕይ ላያይ ይችላል፡፡ምክንያቱም የእግዚአብሔር መልስ አሰጣጥ ለማንም ግልጽ አይደለም ፡፡ ከሱባዔ በኋላ መጀመሪያ የምናገኝው የህሊና ሰላም ነው ፡፡ ይህ ትልቅ የአምላክ ስጦታ ነው ፡፡ ከዚህ ባሻገር ሱባኤ ገብተን ያሰብነውን ካላገኝን ዳግመኛ ተዘጋጅተን እስከ መጨረሻው ሰዓት በመማፀን መጽናት ይኖርብናል፡፡፡

Join @ortodoxslijoch
5.8K views04:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-25 22:01:13 #አጥንቱ_የተበተነበት_ደሙ_የፈሰሰበት

70 ነገስታት ያፈሩበት እለት ነው
ጥር 18 " ዝርወተ ዓጽሙ " ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት ይህቺ ዕለት ለሰማዕቱ 'ዝርወተ አጽሙ' ትባላለች::

በቁሙ 'አጥንቱ የተበተነበት' እንደ ማለት ነው:: ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዘመናት በብዙ ስቃያት ሲያስጨንቁት ኖረው በጽናቱ አሸነፋቸው:: 70 ነገሥታትን ከነ ሠራዊታቸው ከማሳፈሩ ባሻገርም በርካታ (በመቶ ሺ የሚቆጠሩ) አሕዛብን ማርኮ ለሰማዕትነት አበቃ:: በዚህ የተበሳጨ ዱድያኖስም ኮከበ ፋርስ ቅዱስ ጊዮርጊስን እንዲቆራርጡት አዘዘ:: ወታደሮቹም ቅዱሱን ቆራርጠው: በብረት ምጣድ ላይ ጠበሱት:: ያለ ርሕራሔም አካሉን አሳረሩት:: ቀጥለውም ፈጭተው አመድ አደረጉት::

በአካባቢው ወደ ነበረው ትልቅ ተራራ ጫፍ (ደብረ ይድራስ) ወጥተውም በነፋስ በተኑት:: "ሐረድዎ ወገመድዎ: ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ዓመድ "እንዲል:: እነርሱ ይህንን ፈጽመው ዘወር ሲሉ ግን የቅዱሱ ዓጽም ባረፈባቸው ዛፎች: ቅጠሎችና ድንጋዮች ሁሉ "ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት" የሚል ጽሑፍ ተገኘ:: ስለዚህም ይሕቺ ዕለት ቅዱሱ አለቅነትን የተሾመባት ናት ማለት ነው:: ወዲያው ግን ኃያል ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተበተነበት ተነስቶ ወታደሮችን አገኛቸውና "በክርስቶስ እመኑ" ብሎ: አስደንቆ ወደ ሕይወት መራቸው:: 70ው ነገሥታት ግን አፈሩ:: የሊቀ ሰማዕታት ቅ/ጊዮርጊስ በረከቱ ይደርብን ሼር በማድረግ ላላወቁት አሳውቁ

ቅዱስ ጊዮርጊስ ፈጥኖ ደራሹ በመከራ ግዜ ፈጥኖ ይድረስልን
አጥንታችንን ለመፍጨት ደማችንን ለማፍሰስ የተነሱትን ቅዱስ ጊዮርጊስ ያፍዝዝልን ሀገራችንን ሰላም ያርግልን
join @ortodoxslijoch
8.8K viewsedited  19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-25 06:28:19 #አስርቱ_ትዕዛዛት እና #ስድስቱ #ቃላተ- #ወንጌል

1/ ከኔ በቀር ሌላ አምላክ አይኑርህ። (ዘፀ 20÷1_6)
2/ የ አምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ። ( ዘፀ 20÷7)
3/ በባልንጀራህ ላይ በሀሰት አትመስክር። (ዘፀ 20÷8)
4/ የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ። ( ዘፀ 20 ÷12)
5 / አባትና እናትህን አክብር። (ዘፀ 20÷13)
6/ አትግደል። (ዘፀ 20÷4)
7 / አታመንዝር። (ዘፀ 20÷15)
8/ አትስረቅ። (ዘፀ 20÷16)
9/ ባልንጀራህን እንደ እራስህ ውደድ። ( ዘፀ 20÷17)
10/ የባልንጀራህን ሚስት አትመኝ። ( ዘለዌ 19÷18)

ስድስቱ ቃላተ-ወንጌል

1/ ለተራበ ማብላት፣ ማቴ( 25÷35)
2 /የተጠማ ማጠጣት፣ ማቴ(25 ÷3)
3 / እንግዳ መቀበል፣ ማቴ( 25 ÷ 35)
4 / የታረዘ ማልበስ፣ ማቴ ( 25_ 35)
/የታመመን ማየት፣ ማቴ( 25÷36)6/ የታሰረ መጠየቅ፣ ማቴ(25÷36)

ስድስቱ ህግጋተ-ወንጌል

1/ በወንድምህ ላይ በከንቱ አትቆጣ። (ማቴ 5÷22_17
2/ ወደ ሴት አትመልከት በልብህም አታመንዝር። ( ማቴ5÷27)
/ ሚስትህን ካለ ዝሙት ምክንያት አትፍታ። ( ማቴ 5÷32)
4/ ፈፅመህ አትማል። ማቴ (5_÷34)
5/ ክፉን በክፉ አትመልስ። (ማቴ_ 5÷39)
6 / ጠላትህን ውደድ። ማቴ(5÷45) እግዚአብሔር የህጎቹ ጠባቂ ያድርገን፣
ቃሉ ወራሽ ከሳሽ እንዳይሆንብን በልቦናችን ፅላት ያሳድርልን አሜን።
Join @ortodoxslijoch
7.4K views03:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 20:31:45 ኪዳነ ምህረት

ኪዳነምህረት ስንል የምህረት ቃልኪዳን ማለት ነው፡፡በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው፡፡


እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምድራዊ ቆይታዋ ዘውትር ወደ ክርስቶስ መካነ መቃብር ጎለጎታ እየወረደች ትፀልይ ነበር፡፡ ልጇ እና ወዳጇ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገችው ልመናና ፀሎት ተመልክቶና ሰምቶ የምህረት ቃል ኪዳን ገባለት ፡፡


እንኳን የእናቱን ፀሎት እና ልመና ቀርቶ ዘውትር በሀጥያት የምንዘፈቀውን እኛን ክፉዎቹን የሚሰማ አምላክ ስለ አንቺ ፣ ስለ እናቴ ክብርና ፀጋ ስል ይኸው ቃሌ ብሎ ቃልኪዳን አደረገ፡፡
« ከመረጥሁት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ። … » መዝ, 89 : 3 እንዲል መፅሐፉ፡፡

ስሟን ለሚጠሩ፣ በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት ቃልኪዳን ሰጥቷታል ፡፡

ታላቁ መፅሐፍ እንዲህ ይላል፦
". . . ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ። " ኦሪት ዘፍ. 9 : 16

በዚህም መሠረት ቃልኪዳኗን ምክንያት በማድረግ ኪዳነ-ምህረት እያልን እንጠራታለ

እንኳን ለ«ኪዳነምህረት» አደረሳችሁ። የእመቤታችን ምህረት እና ረድዔት፤በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን!!!
@ortodoxslijoch
@ortodoxslijoch
10.3K views17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ