Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxslijoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.17K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ምንማማርበት :መዝሙር: ስብከቶች ይተላለፋል !

መንፈሳዊ ትምህርቶች : መንፈሳዊ ጥያቄዎች : ስብከት : መዝሙር : ይቀርብበታል #ጉዞው ገዳማት #ሰማህታት ታሪክ ይቀርባል!
FacebookGroup : ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ይቀላቀሉ ::

#shear

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-04-16 20:56:26 ከትንሣኤ እስከ ዳግም ትንሳኤ ያሉት ዕለታት ስያሜ፡

# ስኞ ፤ # ማዕዶት (መሻገር)፦
ክርስቶስ በሞቱና በትንሣኤዉ ነፍሳትን ከሞት ወደ ህይወት ከስኦል አዉጥቶ ወደ ገነት ማስገባቱን ይታሳባል፡፡
# ማክሰኞ ፤ # ቶማስ ፦
በቅዱስ ቶማስ ጥያቄ መሠረት በሳምንቱ ጌታችን በድጋም የመገለፁ መታሰብያ፡፡
# ረቡዕ ፤ # እልዓዛር ፦
ኢየሱስ ክርስቶስ አልዓዛርን ከሞት ከተቀበረበት ከአራት ቀን በኃላ ማንሳቱ ይታሰባል፡፡
# ሐሙስ ፤ # አዳም ፦
የአዳም ሐሙስ የአዳም ተስፋዉ ተፈጽሞለት ከነ ልጅ ልጆቹ ወደ ቀድሞ የገነት ክብሩ ለመግባቱ መታሰብያ፡፡
# ዓርብ ፤ # ቅድስት ቤተክርስቲያን ፦
ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለ መመሠረቱ ይታስባል፡፡
# ቅዳሜ ፤ # ቅዱሳት እንስት ፦
እስከ ቀራኒዮ ለተከተሉት በሌልት ወደ መቃብር ለገሠገሱት ቅዱሳት እንስት መታሰብያ፡፡
# እሑድ ፤ # ዳግም ትንሣኤ ፦
የትንሣኤ ምሥጥር ለሁለተኛ ጊዜ ለሐዋርያት የተገለጠበት ዕለት፡፡
ለዳግም ትንሣኤና ለብርሃነ ዕርገቱ በሠላም ያድርሰን፡፡
አሜን አሜን አሜን
join @ortodoxslijoch
1.1K viewsedited  17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 02:57:52 መቃብሩ ባዶ ነው ።
~ ~
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ ።
" እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ።"ማቴ28፣6
እልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልል
★ ዛሬ ...."ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ " 1ኛ ቆሮ 15፣54

ከመጀመሪያው ሰው አዳም ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ የሞቱ ሰዎች በመቃብር ውስጥ አሉ ። ወደፊትም የሞትን ጽዋ የሚቀምሱ የሰው ልጆችም እስከ ጌታ ዳግም ምጽአት ድረስ እንዲሁ በመቃብር ወስጥ ይኖራሉ ።

ነብያት ቢሆኑ ሐዋርያት ፣ ጻድቃንም ሰማዕታትም ቢሆኑ ነገሥታትና መኳንንት ሁላቸውም ሟች ናቸው ። በእያአንዳንዳቸው የመቃብር ሥፍራም ብንሄድ በዚያ የአጽማቸውን ቅሪት እናገኛለን ።

ይህንኑ ሲያረጋግጥ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ በበዓለ ኅምሳ ቀን በኢየሩሳሌም ለተሰበሰቡት እንዲህ አለ፤ " ወንድሞች ሆይ፥ ስለ አባቶች አለቃ ስለ ዳዊት እንደ ሞተም እንደ ተቀበረም ለእናንተ በግልጥ እናገር ዘንድ ፍቀዱልኝ፤ መቃብሩም እስከ

ዛሬ በእኛ ዘንድ ነው።" የሐዋ 2፣29
ጨካኞቹ ነገሥታት ፤ ከቀደሙቱ የነፈርኦን ፣ ናቡከደነጾርና ዲዮቅልጥያኖስ ፣ በኋለኛው ዘመንም ከተነሱት እነሒትለርና ሞሶሎኒም ቢሆን ሞተዋል ። የትም ይሁን የት ተቀብረዋልም ።

በተቀበሩበት ሥፍራም አጽማቸውን እናገኘዋለን ።ምስጥም አፈርም ቢበላቸው እንኳ ቅሪታቸው በዚህች ምድር ይኖራል ።
እውነት ነው ፤ በየትኛውም የምድራችን ክፍል ላይ የሚገኙ የመቃብር ሥፍራዎችን ብንጎበኛቸው በሰዎች አጽም የተሞሉ ናቸው ።

ከሰው ወገን ሆነው እስከ አሁን ሞትን ያልቀመሱና ተሰውረው ያሉ አባቶቻችን እንደ ነቢዩ ኤልያስና ቅዱስ ያሬድ የመሳሰሉ ቅዱሳንም ቢሆኑ እንኳ እስከ ጊዜው ድረስ እንጂ የጊዜው ጊዜ ሲደርስ ሞት እንደሁ አይቀርላቸውም ።

ከዘመናት በኋላ የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ ወደዚህች ምድር መጥተው የሞትን ጽዋም ይቀምሳሉ ።

※የኛ ጌታ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የድንግል ማርያም ልጅ አማኑኤልም በዕለተ ዓርብ በቀራንዮ አደባባይ ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ሲል በመስቀል ላይ ተሰቅሎ በክፉዎች አይሁድ እጅ ሞቷል ። ነገር ግን ሞቶ አልቀረም ። የሞት ኃይልም አላሸነፈውም ። ሞትን በሞቱ ድል አድርጎ ተነሥቷል ።

" ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ?" 1ኛ ቆሮ 15፣55 ተብሎ እንደተጻፈ ወደተቀበረበት ሥፍራ ወደ ቀራንዮም ብንሄድ በዚያ የለም ።

ምክንያቱም ሞት ድል በመነሣት ተውጦአልና ፤ መቃብሩም ባዶ ነው ።
ይህንንም እውነት ደግሞ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዲህ እያሉ ያረጋግጡልናል ።

" መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ" 1ኛ ቆሮ15 ፣ 3-4

" ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።" ሉቃ 24፣5

" እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ።" ማቴ 28፣6
" አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል።"1ኛ ቆሮ15፣20

መልካም በአል ይሁንላቹሁ
      Join @ortodoxslijoch
855 views23:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 05:00:15 #ቀዳም_ሥዑር (የተሻረች ቅዳሜ)

የዐቢይ ጾም የመጨረሻዋ ቅዳሜ ብዙ ስያሜዎች አሏት፦

#ቀዳም_ሥዑር፡-
በዚች ዕለች ከድሮው በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረችው ቅዳሜ ትባላለች፡፡ የማትጾመዋ ቅዳሜ ስለምትጾም ስዑር /የተሻረች/ ተብላለች በዓል መሻርን አይመለከትም በቀዳም ሥዑር ሌሊት ሥርዓቱ የሚጀመረው በመኀልየ ሰሎሞን ምንባብ ነው፡፡ ማኀሌቱም እዝሉ እየተቃኘ እየተመጠነ፣ እየተዘመመ እየተመረገደ እየተጸፋ ያድራል፡፡ ጥዋት አቡን መዋሥዕት ውዳሴ ማርያም ዜማ ተደርሶ ወለመልአከ ሕይወትሰ ሰቀልዎ በሚለው ሰላም ይጠናቀቃል፡፡በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው ቃጭል ሲያቃጨሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡

#ለምለም_ቅዳሜ፡-
ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት ስለሆነ በዚህ ተሰይሟል፡፡ ቀጤማውንም ምእመናን እስከ ትንሣኤ ሌሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል፡፡ በቀዳም ስዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ቃጭል /ቃለዓዋዲ/ እየመቱ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ የሚለውን ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር፤ ጌታ በመስቀሉ ሰላምን እንደሰጠን እና ትንሣኤውንም እንደገለጠልን በማብሰር፤ ቄጤማውን ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡ ምእመናኑም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡ ቄጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ ያሠሩበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡

(የቀጤማው አመጣጥና ምስጢርም ከአባታችን ከኖኅ ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ምድር በማየ አይኅ /በጥፋት ውኃ/ በጠፋችበት ወቅት የኖኅ ታማኝ መልእክተኛ ርግብ የውኃውን መጉደል ያበሰረችው ቀጤማ ይዛ በመግባት ነው፡፡ ዛሬም ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች የኃጢአት ውኃ ጐደለ፣ የኃጢአት ውኃ ጠፋ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ነጻነት ተሰበከ ታወጀ በማለት ካህናት ቄጠማ ይዘው ምእመናንን ያበሥሩበታል፡፡)

#ቅዱስ_ቅዳሜ፡-
ቅዱስ ቅዳሜ መባሉ ቅዱስ የሆነ እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ከፈጠረ በኋላ በዚህ ቀን ከሥራው ሁሉ ያረፈበት ነው፡፡ በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ሥራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ፣ በነፍሱ ሲዖልን በርብሮ ባዶዋን አስቀርቷታል፡፡ በዚያ ለነበሩት ነፍሳትም የዘለዓለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ከሌሎቹ ዕለታት የተለየ ዕለት ለማለት ቅዱስ ቅዳሜ ተብሏል፡፡

(ስምዐ ተዋሕዶ የስምዐ ጽድቅ ልዩ እትም ዘሰሙነ ሕማማት ሚያዝያ 2004 ዓም)

     Join @ortodoxslijoch
1.2K views02:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 07:25:46 ሚስጥረ እለተ አርብ ( ስቅለት )

እለተ አርብ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት የሚታሰብበት ቀን ሲሆን ኢየሱስ ክርስቶስ በእለተ አርብ ያያቸው ስቃይና መከራ ለዓይን የሚዘግንኑ ለጆሮ የሚሰቀጥጡ ከባድ ቀንን ለእኔና ለእናንተ ፍቅር ሲል አሳልፏል፡፡

" ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ
እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። " ኢሳ. 53 : 7

13ቱ ህማማተ መስቀል
➊ እራሱን በዘንግ ተመታ ፦ ተፉበትም መቃውንም ይዘው
እራሱን መቱት ።《ማቴ 27÷30》
➋ በጥፊ ተመታ ፦ በጥፊም ይመቱት ነበር።《የሀ 19÷4》

➌ ምራቅ ተፉበት ፦ ተፉበትም መቃውንም ይዘው እራሱን
መቱት።《 ማቴ 27÷30》
➍ የሾክ አክሊል ጎንጉነው በእራሱላይ አቀዳጁት 《ማቴ.27፥29 》

➎ መራራ ሀሞት አጠጡት ፦ በሀሞት የተደባለቀ የወይን
ጠጅ ሊጠጣ አቀረቡለት፤ ቀምሶም ሊጠጣው አልወደደም ።《ማቴ 27÷34 》

➏ ጀርባውን መገረፉ ፦ በዚያን ጊዜም ጲላጦስ እየሱስን ይዞ
ገረፈው ። 《ዩሀ 19÷1》

➐ ጎኑን በጦር መውጋት፦ ነገር ግን ከጭፈራዎቹ አንዱ ጎኑን በጦር ወጋው ወድያውም ደምና ውሃ ወጣ።《የሀ 19÷34 》

➑ ወደ ኃላ መታሰሩ ፦ የሾለቃውና ጭፍሮቹ የአይሁድም ሌሎችም እየሱስን ይዘው አሰሩት። 《ዩሀ.18÷12 》

➒ ሳዶር
➓ አላዶር
➊➊ ዳናት
➊➋ አዴራ
➊➌ ሮዳስ

5ቱ #ቅንዋተ #መስቀል ችንክሮች ሳዶር ፣ አላዶር ፣ ዳናት ፣ አዴራ እና ሮዳስ ይባላሉ።
➊ #ሳዶር ፦ ማለት ቀኝ እጁ የተቸነከረበት
➋ #አላዶር፦ ማለት ግራ እጁ የተቸነከረበት
➌ #ዳናት ፦ ማለት እግሮቹ የተቸነከረበት
➍ #አዴራ ፦ ማለት ደረቱን የተቸነከረበት
➎ #ሮዳስ ፦ ማለት ከወገቡ (እብርቱ) አጣብቆ እንዲይዝ
የተቸነከረበት
መከራን ታገሰ

በህይዋንና በሙታን ላይ የሚፈርድ እርሱን እንደበደለኛ
ተፈረደበት
አለምን ሁሉ በቅፅበት የፈጠረ እርሱ በስጋው ሞተ በመለኮት ህያው ሆነ

ጌታችን_መድኃኒታችን_እየሱስ_ክርስቶስ ከ6-9 ስአት በመስቀል ላይ ሳለ የተናገራቸው 7ቱ የፍቅር ቃላት
ኤሉሄ ኤሉሄ ለማስበቅታኒ (አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ ) ማቴ 27÷46
እውነት እውነት እልሃለሁ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትኖራለህ።
ሉቃ.23÷43
አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ። ሉቃ 23÷43
አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው። ሉቃ.23÷34
እናትህ እንኃት እንሆ ልጅሽ:: ዩሀ 19÷26-27
ተጠማሁ። ዩሀ 19÷28
ተፈፀመ። ዩሀ 19÷30

#ጌታችን_መድኃኒታችን_እየሱስ_ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ
የተፈፀሙ 7ቱ ታአምራት
ፅሀይ ጨለመች
ጨረቃ ደም ለበሰች
ከዋከብት ብርሃናቸውን ነሱ
የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከሁለት ተከፈለ
አለቶች ተሰነጣጠቁ
መቃብራን ተከፈቱ
የሞቱት ተነሱ
ክብርና ምስጋና አምልኮት ውዳሴ ስግደት ዝማሪ ይድረሰ ለአምላካችን_ለመድኃኒታችን_ለእየሱስ_ክርስቶስ

አቤቱ አምላካችን ሆይ በመንግስትህ በመጣህ ጊዜ
አስበን አሜን ፫
መልካም ስግደት

     Join @ortodoxslijoch
3.0K views04:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 19:37:18 ✞ ጌታችን መዳኒታችን እየሱስ ክርስቶስ እመቤታችንን እናት ትሁን ብሎ የሰጠው ለማነው ✞
ሀ//ለያቆብ
ለ//ለእሳያስ
ሐ//ለዮሐንስ
መ//ለዮሴፍ
2.9K views16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 19:34:33 ✞ በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን ያለው ነብይ ማነው ✞

ሀ//ነብዩ ሙሴ
ለ//ነብዩ እሳያስ
ሐ// ነብዩ ዳዊት
መ/ ነብዩ ኤርሚያስ
2.8K views16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 19:31:49 ✞ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሳ በኃላ መጀመርያ የታየው ለማን ነው ? ✞

    ሀ.ለሰሎሜ
    ለ.ለማርያም መግደላዊት
    ሐ. ለቅዱስ ጴጥሮስ
    መ. ለአርማትያሱ ዮሴፍ
2.7K views16:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 19:30:37 ✞ በኢየሱስ ቦታ የተፈታው ወንበዴ ማነው? ✞

ሀ.በርባን
ለ.በርተሌሜዎስ
ሐ.ይሁዳ
መ.በርናባስ
2.6K views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 19:28:09 ✟ ክርስቶስ በተሰቀለበት ዘመን ሊቀ ካህናት የነበረው ማን ነው ? ✞

  ሀ, ሐና
  ለ,  ቀያፋ
  ሐ, ሰጲራ
  መ,  ሐናንያ
2.6K views16:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 19:26:10 መንፈሳዊ ጥያቄዎች  መጠየቅ ልንጀምር ነው ዝግጁ  ናችሁ
2.4K views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ