Get Mystery Box with random crypto!

Christian Tadele Tsegaye

የቴሌግራም ቻናል አርማ marheirgebrye — Christian Tadele Tsegaye C
የቴሌግራም ቻናል አርማ marheirgebrye — Christian Tadele Tsegaye
የሰርጥ አድራሻ: @marheirgebrye
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.97K
የሰርጥ መግለጫ

This channel serves as a platform to reflect political and socio-economic views of Christian Tadele Tsegaye.

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2022-08-29 06:18:46 በአገርና በሕዝብ አይኮረፍም!
****
ጦርነትን ትናንትም፥ ዛሬም፥ ነገም አልደግፍም። ይህ ማለት ግን አገር ሲፈርስ፥ ሕዝብ ሲፈልስ እጆቼን አጣጥፌ እቀመጣለሁ ማለት አይደለም። አገርና ወገን የሌለው ሰው ባይኖርስ ምን ሊቀርበት ነው ዝም የሚለው? የአገርን አንድነት፥ የሕዝብንም ደኅንነት ለመጠበቅ በሚደረግ ውቅያኖስ በሚያህል ርብርብ ውስጥ የድርሻችንን አንዲት ጠብታ ብናዋጣ ክብሩ ለየራሳችን አይደለም ወይ? ደግሞስ ለአገር መስዋእት መክፈልን ማነው የፀጥታ ኃይሎች የብቻ ኃላፊነት ያደረገው?

የመንግስት አመራሮች ብሽቅ ሆነው እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ዜጋ ሁሉ አንጀቴን አሳርረውት ያውቃሉ። አገርንና ዜጎችን የመጠበቅ የቅድሚያ ቅድሚያ ግዴታቸው መሆኑንም እገነዘባለሁ። ይሁንና በብሽቅነታቸው አኩርፌ፥ አገሬና ወገኔ የማንም መፈንጫ እንዲሆኑ በዝምታ ልተባበር አልችልም። አገር ለማፍረስ የመጣ ኃይል፥ ሕዝብን ለመጨረስ የተሰለፈ ኃይል፥ እንኳንስና በዝምታ በዱላም አይመለስም። ደግሞም በአገርና በሕዝብ አይኮረፍም። ድል ለኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት! ድል ለአማራ እና አፋር ልዩ ኃይሎችና ሚሊሻዎች! ድል ከጥንት እስከ ዛሬ ለአገርና ሕዝብ ክብርና ነፃነት ሕይወታቸውን ለመስጠት ለማይሳሱ ፋኖዎቻችን!

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ልጆቿን ይባርክ!
4.4K viewsedited  03:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 21:47:36 የኢትዮጵያ መንግስት በአገር አንድነትና የሕዝብ ደኅንነት ላይ ጦርነት በከፈተው አሸባሪው ትሕነግ ላይ አስፈላጊውን ሁሉ እርምጃ በመውሰድ መንግስታዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ፤ መላው ሕዝባችንም ከአገር መከላከያ ሰራዊትና ሌሎች የፀጥታ ኃይሎች ጎን በመሰለፍ የሽብር ቡድኑን የጥፋት ተልእኮ በመቀልበስ ረገድ የድርሻውን እንዲወጣ መልእክቴን አስተላልፋለሁ።
2.3K views18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 19:33:22 Channel photo updated
16:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 16:43:01 መንግስት እነዶክተር ወንደሰንን ከእስር እንዲለቅ እጠይቃለሁ፤
*
«ፋኖን ለማደራጀት ተንቀሳቅሳችኋል» በሚል ሰበብ ወንድማችንን ዶክተር ወንድወሰንን ጨምሮ በጨነቀለታው ለአገራቸው አንድነትና ለሕዝባቸው ደኅንነት ከመንግስት ጎን ተሰልፈው ደፋ ቀና ሲሉ የነበሩ ወገኖች ባሕር ዳር ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው የሰባታሚት ማረሚያ ቤት በግፍ ከታሰሩ ሰነባበቱ። ጉዳዩን የግፍ ግፍ የሚያደርገው እነዚህ ወንድሞቻችን እስከዛሬ ድረስ በማረሚያ ቤት የሚገኙት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድቤት የዋስ መብታቸውን ካስከበረላቸው በኋላም መሆኑ ነው።

ይኼ ጉዳይ አሳሳቢነቱ እጅግ ከፍ ያለ ነው። ዜጎች በመንግስታዊ ተቋማት በተለይም የፍትኅና የፀጥታ ተቋማት ላይ ያላቸው አመኔታ ከተሸረሸረ ሁሉም በእጁና በየደጁ ፍትኅን ለራሱ እንዲወስድ በር የሚከፍት ይሆናል። የፍርድቤቶች ውሳኔዎች በአስፈፃሚ አካላት ሳይከበሩ ሲቀሩ ዜጎች በሕግ የበላይነት እምነት ሊኖራቸው አይችልም። ይህ ደግሞ በውጤት ደረጃ ማንንም የሚጠቅም አይሆንም። ስለሆነም የሚመለከታችሁ አመራሮች ይህን ጉዳዩ አስቸኳይ መፍትሔ ትሰጡት ዘንድ እጠይቃለሁ።
6.9K views13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 11:50:22
ነገረ ፍረጃ!
6.8K viewsedited  08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 07:45:11

6.8K views04:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 22:02:05 እነዘመነ ካሴን በተመለከተ
****
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የፓርላማ ስብሰባ ጭምር የወንድሞቻችን ጉዳይ ተነስቶ በአዳራሽም ከአዳራሽ ውጭም ብዙ የሀሳብ ልውውጦች አድርገናል። የፌዴራል መንግስት የፖለቲካ እና የፀጥታ አመራሮች ጉዳዩ በሰላም እንዲቋጭ ብርቱ ፍላጎት ነበራቸው፤ አላቸውም። መሰረታዊ ጉዳይ በክልሉ በኩል ማለቅ የነበረባቸው አንዳንድ ጉዳዮች አለመቋጨታቸው ነው። የአማራ ክልል መንግስት ባለፈው የክልሉ ምክርቤት ስብሰባ ወቅት የምሕረት አዋጅ አውጆ እነዘመነን ጨምሮ የሚሳደዱ ወንድሞች ወደ ሰላም እንዲገቡ የሚደረገውን ጥረት በባለቤትነት እንዲመራ ንግግር አድርገን የነበረ ቢሆንም ሳይፈፀም ምክርቤቱም ለእረፍት ተበትኗል።

ጉዳዩ እስካሁን ድረስ እልባት ያላገኘው በክልሉ መንግስት በኩል ባሉ መጎረባበጦች ምክንያት ብቻ መሆኑን መግለጽ እፈልጋለሁ። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ጭምር የመንግስታቸው ምርጫ ሰላም ብቻ መሆኑን አስረግጠው የተናገሩ በመሆኑ፤ በክልሉ በኩል ጉዳዩ ከግል ስሜት ከፍ ባለ መንግስታዊ ትክሻ እንዲያዝ ሁሉም በጎ ጫና እንዲያሳርፍ ማሳሰብ እወዳለሁ። እነዘመነን ጨምሮ መንግስት ሕግ ማስከበር እያለ በሚጠራው ዘመቻ የሚሳደዱ ልጆች የሰላም የመፍትሔ አማራጩን እንደሚቀበሉትም ማረጋገጫ ሰጥተዋል።

ከዚህ አንፃር እንደአንድ የሕዝብ እንደራሴና የወገኖቹ ጉዳይ እንደሚያሳስበው ዜጋ የማደርገውን ጥረት ያልተገባ ስም የምትሰጡ እና እየተደረገ ያለውን ጥረት ለማኮላሸት የምትታትሩ ወገኖች እውነታውን በመረዳት በጎ ሚና እንድትወጡም መልእክቴን አስተላልፋለሁ። የክልሉ አመራሮችን ባልተገባ ሁኔታ ወደ ማሳደድ ዘመቻ እንዲገቡ የወተወታችሁና አብራችሁ መክራችሁ ውሳኔ ያሳለፋችሁ አንዳንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችም በእናንተ የጥፋት ምክር እስካሁን ከሕግ ውጭ የተገደሉ ወንድሞቻችን ጥፋት ይበቃልና ከመሰል ስምሪታችሁ ትታቀቡ ዘንድ ጥሪዬን አቀርብላችኋለሁ።

በዚሁ አጋጣሚ የግፍ እስረኞች እንዲፈቱ ያቀረብነውን ውትወታ ተቀብላችሁ በከፊል ስለፈፀማችሁ በየደረጃው ያላችሁ የፖለቲካና የፀጥታ አመራሮችን እያመሰገንሁ፤ ዛሬም ድረስ ባልተገባ ሁኔታ በእስር የሚንገላቱ ወገኖችንም ከእስር ትፈቱ ዘንድ የተለመደውን ውትወታ አቀርብላችኋለሁ።
7.0K views19:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 10:45:28 ከአብን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልነት መልቀቄን ስለማሳወቅ፤
*
የምወዳችሁ የአብን አባላትና ደጋፊዎች ይህን እስከዛሬ ድረስ በግልጽ ባለመናገሬ እጅጉን አዝናለሁ። ይሁንና ጉዳዩን ከዚህ በላይ ማዘግየት ንቅናቄያችን የተሟላ ሁለንተናዊ ሪፎርም እንዳያደርግ እንቅፋት ስለሚፈጥር እና በለውጥ ፈላጊ ብርቱ አባላትና ደጋፊዎቻችን ዘንድ የተሰነቀውን በጎ ተስፋ ጨርሶ እንዳያጨልም ስጋት ስላደረብኝ ዛሬ የግድ ኃቁን መናገር ይኖርብኛል።

በተጨባጭ ከግንቦት 1፣ 2014 ዓ/ም ጀምሮ እንደሥራ አስፈፃሚ ተወስነው መሰራት የነበረባቸው ጉዳዮች ለውጥ ፈር በሆኑ ጥቂት ግለሰቦች ምክንያት ከስነስርዓት ውጭ እየተወሰኑ በመሆኑ የእኔ በስም ብቻ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ተብሎ መቀጠል ትክክል አለመሆኑን ተረድቻለሁ። የቤት ኅመማችንን በቤት ተነጋግረን እንቀርፋለን በሚል በዝምታ መቆየቴም በየደረጃው ባሉ የመዋቅራችን አባላትና አመራሮች ዘንድም ለምን ኃቁን አትነግረንም የሚል ወቀሳ አድርሶብኛል። ለተቋም ማዕከላዊነትና ወንድማማችነት እሴት በሚል በዝምታ መቆየቴ ድርጅቱን ከማዳን ይልቅ እንዲፈርስ የመተባበር ያህል በመሆኑ እያደር ስጋት ፈጥሮብኛል።

ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ያስቀመጣቸው ሁኔታዎች ተደማምረውበት በተለይም የለውጡ ሂደት የመደናቀፍ ከፍተኛ አደጋ የተጋረጠበት በመሆኑ፤ መላው የንቅናቄያችን አባላትና ደጋፊዎችም ይኸንኑ ተገንዝባችሁ፥ አብንን እንደድርጅት ለማስቀጠልና የሚጠበቅበትን ትግል በማድረግ የቆመላቸውን የፖለቲካ ግቦች ያሳካ ዘንድ፥ የሚቻላችሁን በጎ ሚና እንድትወጡም ጥሪዬን አቀርባለሁ። እንደአብንን መስራች፣ ፓርቲውን ወክሎ የሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባል እንደሆነ ኃላፊነት እንደሚሰማው ግለሰብ እና እንደ አንድ አማራ ንቅናቄያችንን ወደ ቀደመ ሥፍራውና ትክክለኛው የትግል መስመር ለመመለስ በሚደረገው ርብርብ ውስጥ አንዳችስ እንኳን የምቆጥበው ነገር እንደማይኖረኝም ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ።

አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በጉዳዩ ላይ ዝርዝር ጋዜጣዊ መግለጫዎችንም የምንሰጥ ይሆናል።
8.7K views07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 05:47:57 #እረኛዬ

ምድጃ ሥር ባለ ጭስ እያሳበቡ፣
እልፍ አእላፍ እናቶች ስንት ብሶት አነቡ።

ልጆች ሆነን… እረኛ ሳለን… እናናዬ የአፍ ማሟሻ፥ የናፍቆት ማስተንፈሻ ዘፈናችን ነበር። እናናዬ ዘፈን ውስጥ ምስል ከሳች እምቅ ትዝታ አለ። እናናዬ ዘፈን ውስጥ ብርቱ ፍቅር አለ።

በአናናዬ ዜማ ገራርገርነትን፣ ሩህሩህነትን ተፈጥሯዊነትን፣…ድምቀት ሰጥተን አንጎራጉረን አድገናል። ይኸን መሰሉ የልጅነት ስሜት በየጨዋታው ዓይነት መልኩን እና ዜማውን ቀያየሮ በሁላችንም የልጅነት ልብ ውስጥ ታትሞ አለ። ታዲያ ምን ሆነን ነው ስናድግ ክፉ፣ ምቀኛ፣ በጥላቻ የሰከርን የሆንነው? የልጅነት ገነታችንን ማነው ቀምቶ አሁን ወዳለንበት የመጠላላት ሲዖል ያጋዘን?

ከሰሞኑ ጋምቤላ ነበርን። ምድሩ አረንጓዴ የለበሰ፤ በባሮ የረሰረሰ፤ እግዜር የውብ ሕዝብ መኖሪያ ይሆን ዘንድ ውብ አድርጎ የሰራው የመባረክ አብነት ነው። አየሩ ሞቅ ይላል። ገነት እንዲህ ይሞቃል እንዴ ብለን አብረን የነበርን የምክርቤት አባላት ተሳስቀናል። የሄድንበትን ደቋና ወደ ማገባደድ እያለን መንገድ ላይ ሁለት ጉብሎች አየን። በግምት 12 ወይ 13 ዓመት የሚሆናት ልጅ ከጓደኛዋ ጋር ትጓዛለች። አተኩራ ተመለከተችን። ዓይኖቿ ውስጥ ተማጽኖ ነበር። በዓይኖቿ መስኮት ወደ ውስጥ ገባሁ። የተሰበረ ቅስሟ…እንክትክት ያለው ኅልሟ …ብዙ አላራመደኝም። ምልከታችን የግል ሆኖ ስለልጅቷ የምክርቤት አባላት የነበረን መረዳትና ስሜት ግን አንድና ያው ነበር። በተሰበረ ቅስሟ የሁላችንም ስሜት ተረብሿል። ወደ ሌላ ብርቱ ደቋና እየሄድን ስለነበር ልጅቷን አላነጋገርናትም። ስለሁኔታው ያወራነው ቆይተን ስለነበር ድጋሚ ሄደን ለማግኘት እድሉ አልነበረንም።

አንቺ የባሮ ዳር ጉብል ስምሽን አናውቀውም። የሆንሽውን አልነገርሽንም። እንዲሁ ግን ውብ ገጽታሽ፣ ያልነገርሽን ተማጽኖሽ፣ የመንፈስ ስብራትሽ፣ ፣…ከስጋችን ጋራ አዲስ አበባ ገብቷል። ነፍሳችን ፈገግታሽን ከሰረቀው፣ ኅልምሽን ካነካከተው፣…ከሱ ጋር ግን ለምን በሚል እዛው ባሮ ዳር እየቃተተች ነው።

መሪዎችና የእምነት አባቶች የጋራ ወገኖቻችንን የግፍ ጭፍጨፋ በጋራ አዝነን ልስ እንዳናወርድ እርም እያስበሉን ባለበት ወቅት በቴሌቪዥን መስኮት የሚተላለፍ ድራማ ትእይንት በየቤታችን አይተን የሆድ የሆዳችንን እያሰብን ጭምር እንድናለቅስ ሰበብ ስለፈጠራችሁልን የእረኛዬ ድራማ ቡድን አባላትን በሙሉ እናመሰግናለን።

ጥላቻ ገነትን ወደ ሲዖል የመቀየር አቅም አለው!
7.1K views02:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 05:54:18 እምቡቸሬ ከባሮ ወንዝ ዳር
****
እምቡቸሬ እምቡቸሬ
አንጉችልኝ ከዘሬ

ከሽንብራው ጎታ የተረፈውን
ከጤፉ ጉሽጉሻ የተረፈውን
ከበቆሎው ጎታ የተረፈውን
መጁን ወቅረሽ
ቋቱን ጠርገሽ
ተንጎዳጉደሽ አንጉችልኝ
ጅራፍ ልግረፍ ደስ ይበለኝ

እምቡቸሬ እምቡቸሬ
እናቴ የሰጠችኝ የጤፍ ፍሬ

ያልነቀዘው ቀይ ጤፉ
የማይ…ታማው ነጭ ጤፉ
እሱን ፈጭተሽ አንጉችልኝ
ቁስሉ እንዲሽርልኝ

ጥቁር ሽንብራ
ከቂም ተራራ
ጥቁር ዳጉሳ
ከክፋት ጓሳ
ቀይ በቆሎ
ከጓሮ በቅሎ

ሁሉን ፈጭተሽ
ባንድ አንጉተሽ
አቅርቢልኝ
ይሻርልኝ

ግራ ቀኝ
ቀኝ ግራ
ማዶ ተራራ የጮኸው ጅራፍ
ፍቅርን ተክቶ ጥላቻን ያርግፍ
ቀኝ ግራ
ግራ ቀኝ
ከቤቴ ደጃፍ
ምገርፈው ጅራፍ
ጥላቻ ቂምን እንደጠል ያርገፍ

እምቡቸሬ
እምቡቸሬ
ሰላም ይወርድ ለሀገሬ

ጨለማው ተገፈፈ
ጥላቻ ተገረፈ
ቂም ረገፈ
እምቡቸሬ…

(የዘንዶውን ራሶች ቀጠቀጥህ፤ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው። መዝሙር 74: 14)

እንኳን ለእምቡቸሬ/ቡሄ/ ደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ!
6.7K views02:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ